Posts

ሰሞኑን ኢትዮጵያ የቢ ፕላስ ደረጃን ማግኘቷ ተገጿል ለመሆኑ ስለተቀሩ ኣገራት ምን ያህል ያውቃሉ?

Image
ኢትዮጵያ በኢኮኖሚ እድገትና ኢንቨስትመንትን በመሳብ የቢ ፕላስ ደረጃን አገኘች   አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 6፣ 2006 ( ኤፍ.ቢ.ሲ ) ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የኢኮኖሚ እድገትና ኢንቨስትመንት መስህብ አለም አቀፍ ደረጃ እንደወጣላት የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትሩ አቶ ሶፈያን አህመድ ተናገሩ። ኢትዮጵያ አስካሁን ያስመዘገበችው እድገት ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት የተሻለ መሆኑ በ3 አለም አቀፍ ገለልተኛ ተቋማት መረጋገጡንም ገልፀዋል ሚንስትሩ ። ሶስት አለም አቀፍ  ተቋማት በአፍሪካ ደረጃ ከወጣለቸው አራት ሃገራት መካከል ኢትዮጵያን  በ ቢ ፕላስ ደረጃ አስቀምጠዋታል። አቶ ሶፊያን ደረጃው ኢትዮጵያ በዕድገት ግስጋሴዋ ያስመዘገበችው ውጤት ተጨባጭ መሆኑን ያሳየ ነው ብለዋል። በተጨማሪም ይህ ውጤት አገሪቱ ቀደም ሲል ትታወቅበት የነበረው የድህነት ገፅታ መቀየር መቻሉን ያመላከተ ነው ያሉት። አገሪቱ ይህን ደረጃ ያገኘችው ባለት የኢንቨስትመንት አማራጮች ፣ ምቹነት እንዲሁም ኢንቨስትመንትን የመሳብ አቅም እና በአጠቃላይ በመላ አገሪቱ ያለው የልማት እንቅስቃሴን ከግምት ውስጥ በማስገባት መሆኑ ነው የተመለከተው። ስድስት ወራተን በፈጀ ጥናት የተመለከተው የኢኮኖሚ እድገትና ኢንቨስትመንት መስህብ አለም አቀፍ ደረጃ ኢትዮጵያን ከምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ ፣ ከአፍሪካም አምስተኛዋ አገር አድርጓታል። በቀጣይም ተመሳሳይ ደረጃ ለማውጣት ዓመታዊ ምዘና እንደሚካሄድ ተመልክቷል። ለተጨማሪ

Breakthrough wins for Belete and Teshome at 5th edition of EVERY ONE Campaign Races in Hawassa

Image
Hawassa, Ethiopia  -  Tenaw Belete  won the biggest race of his career in the  2014 EVERY ONE Campaign Half-Marathon Race  in  Hawassa  on Sunday 11th May, while  Yewebdar Teshome  stepped up from her ninth place finish in 2013 to become this year’s women’s champion. Meanwhile in the mass 21km race there were wins for Yibeltal Biyalf (1:20:17) in the men’s race and Kirstin Mitchell (1:40:03) in the women’s race. Including the mass 7km race and the children’s races more than 3,500 participants took part in this year’s EVERY ONE races. Belete runs for the same  Omedla Police club  as  Haile Gebrselassie . To win this race in a new personal best time of 1:03:29 was a big step up in his career. As he explained after the race: “Last October I finished 3rd in the inaugural  Haile Gebrselassie Marathon  in Hawassa and won 15,000 birr. Before then I’d been struggling with not having enough money to cover my food and rent, but now this money will give more stability to my training. I’m no

ፍትህ የተነፈገው የግንቦቱ ዕልቂት፤ ሎቄ!

Image
Photos@Internet Editor: Worancha Information Network ''... The Sidama people, like other peoples under this regime, are denied their legitimate right on their own land. They were massacred in cold blood when they demonstrated against forceful eviction from their ancestral land. Instead of investigating this atrocity committed by the regime’s special notorious unit known as  Agaazi , as promised by the regime, the evidences were suppressed and the perpetrators were also promoted. One of the culprits of that atrocity is the president of the Southern Peoples’ Region at the time and the current Prime Minister of Ethiopia Hailemariam Desalegn....'' Gadaa.com By Desalegne Mesa , May 10, 2014, Hawassa, Sidama በሁሉም የኢትዮጵያ ብሔሮች ፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ዘንድ ከግንቦት ወር ጋር በተያያዘ አንድ አይነት አመለካከት ( አሉታዊ ) እንዳላቸው መገመት ይቻላል፡፡ ምክንያቱም ሁሉም ለማለት በሚያስደፍር መልኩ ግንቦትን ከወራት ሁሉ ክፉ፣ አደጋ በብዛት የሚከሰትበትና በባህሪዩም ደረቅ ወር ( ምንም እንኳን ዝናብና ልምላሜ ይዞ ቢመጣም ) አድርገው በአዕምሮአቸው ስለዋልና ነው፡፡ ለዚህም ይመስላል በአብዛኛው ኢትዮጵ

በሃዋሳ ከተማ ለኣምስተኛ ጊዜ የተካሄደው Everyone ታላቁ ሩጫ ውጤት ደርሶናል

Image
" የጨቅላ ህፃናትን ህይወት እንታደግ " በሚል መሪ ቃል የእናቶችን ሞት ለመታደግ ታስቦ የተዘጋጀው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ በሃዋሳ መ ካሄ ዱ ይታወሳል ። ውድድሩ በግማሽ ማራቶን፣ በሰባት ኪሎ ሜትርና በህፃናት ውድድር በአንድ ነጥብ ሁለት ኪሎ ሜትር ተካሂዷል። ትናንት በተካሄደው ሩጫ አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ፣ አርቲስት ሰለሞን ቦጋለ፣ አርቲስት ግሩም ኤርሚያስ እና ሌሎችም ታዋቂ ሰዎች  ተገኝተዋል። በወንዶች ግማሽ ማራቶን ጤናው በለጠ  አንደኛ ሲሆን ርቀቱን ለማጠናቀቅ 1 ሰዓት ከ 3 ደቂቃ ከ 23 ሰከንድ ወስዶበታል። ሀብታሙ ካሳሁን 1 ሰዓት ከ 3 ደቂቃ ከ 45 ሰከንድ በሆነ ሰዓት በሁለተኝነት አጠናቋል። ሀብታሙ ካሳሁን ውድድሩን ለማጠናቀቅ በግማሽ ማራቶን ሶስተኛ የሆነው የፍቃዱ ግርማ ሲሆን ከሀብታሙ በ 10 ሴኮንድ ዘግይቶ ገብቷል። በሴቶቹ የግማሽ ማራቶን የሩጫ ውድድር የውብዳር ተሾመ ውድድሯን በአንደኝነት ስታጠናቅቅ የወሰደባት ሰዓትም 1 ሰዓት ከ 15 ደቂቃ ከ 43 ሴኮንድ ነው። እምሻው ንጉሴ በሁለት ሴኮንድ በየውብዳር ተቀድማ ሁለተኛ ሆና ውድድሯን አጠናቃለች። በሴቶች ግማሽ ማራቶን ሶሰተኛ የሆነችው ኑሪት ሽመልስ ስትሆን የወሰደባት ሰዓትም 1 ሰዓት ከ 16 ደቂቃ ከ 15 ሴኮንድ ወስዶባታል። በሀዋሳ ከተማ ታላቁ ሩጫ ሲካሄድ ዘንድሮ ለአምስተኛ ጊዜ ነው። በዚህ ውድድር አሸናፊዋች በአጠቃላይ 64 ሺህ ሁለት መቶ ብር ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። በሴትም በወንድም አንደኛ ሆነው ውድድራቸውን ለጨረሱ 14 ሺህ ብር ሽልማት ሲያገኙ ሁለተኛ ሆነው የጨረሱ 7 ሺህ ብር ተሸልመዋል፡፡ ሶስተኛ የወጡት ደግሞ 4 ሺህ ብር ተሸልመዋል።

ያላረፈው አየር ማረፊያ እንዳያፋጀን!

Image
ከማህበራዊ መረብ የተገኘ በ ደሳለኝ መሳ በኢትዮጵያ ውስጥ ባሉ ክልሎች መካከል የመሰረተ ልማትና የልማት ልዩነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየሰፋ መምጣቱን የተለያዩ ፀሐፊዎችና ባለሙያዎችም ጭምር ይስማሙበታል፡፡ መንግሰት በየጊዜ ፍትሐዊ የሀብት ክፍፍል በክልሎች መካከል አረጋግጫለው ብሎ ቢከራከርም በተጨባጭ ከሚታየው ነገር አንፃር የኢህአዴግ ክርክር ውሃ የሚቋጥር አልሆነም፡፡ በዚህ መጣጥፍ ልያነሳ የፈለኩት መንግስት ለአየር ማረፊያ ግንባታን ለማስፋፋት ካለው ፍላጎትና ተግባር አንፃር የፍትሐዊነት ጉድለት እንዳለው ከማሳየትም አልፎ አሁን በሲዳማ እየተሞከረው ያለው ነገር ከጥቅሙ ጉዳቱ ሊያመዝን እንደምችል ለማመላከት ነው፡፡ ማንም ሰው ለመገንዘብ እንደምችለው ( አልገነዝብም ካሉት ውጭ ) ሐዋሳ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሳች ካለችው የጎብኚዎች ሳቢቷና ከአካባቢም ከሚገኘው የኢኮኖሚ ወሳኝነቷ አንጻር አየር ማረፍያ አስፈላጊ ብቻ ሳይሆን አንገብጋቢ ጉዳይ ነው፡፡ ነገር ግን ይህ ነገር እስከ አሁን ድረስ ተፈፃሚ አልሆነም፤ ሀዋሳና አካባቢውም እድለኛ መሆን አልቻለም፡፡ ሀዋሳና አካባቢዋ አንድ አየር ማረፍያ እንኳን ሳይኖራት የተለያዩ ከልሎች ከአንድ በላይ አየር ማረፊያ ተከፋፍለዋል፡፡ ለምሳሌ የትግራይን ክልልን ብናይ በቅርቡ ዓለም አቀፍ በረራ ማስተናገድ ከጀመረው የመቐለ “አሉላ አባነጋ” አየር ማረፍያ በተጨማሪ በሌሎች አራት ከተሞች የሀገር ውስጥ በረራ የሚያስተዳግዱ አየር ማረፊያዎች ተገንብቶላቸዋል፡፡ በአማራ ክልልም በቅርቡ ወደ ጎሮቤት ሀገር በረራ ማስተናገድ የጀመረውን የባህር ዳሩን ጨምሮ በጎንደርና በወሎ የሀገር ውስጥ በረራ የሚያስተናግዱ አየር ማረፊያዎች አላቸው፡፡ ከባህር ዳር እሰከ ጎንደር ያለው ርቀት 225 ኪ . ሜ ሲሆን በዚህ ርቀት ሁለት አየር ማረፊያ አላት የአ