Posts

በሃዋሳ ከተማ ለኣምስተኛ ጊዜ የተካሄደው Everyone ታላቁ ሩጫ ውጤት ደርሶናል

Image
" የጨቅላ ህፃናትን ህይወት እንታደግ " በሚል መሪ ቃል የእናቶችን ሞት ለመታደግ ታስቦ የተዘጋጀው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ በሃዋሳ መ ካሄ ዱ ይታወሳል ። ውድድሩ በግማሽ ማራቶን፣ በሰባት ኪሎ ሜትርና በህፃናት ውድድር በአንድ ነጥብ ሁለት ኪሎ ሜትር ተካሂዷል። ትናንት በተካሄደው ሩጫ አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ፣ አርቲስት ሰለሞን ቦጋለ፣ አርቲስት ግሩም ኤርሚያስ እና ሌሎችም ታዋቂ ሰዎች  ተገኝተዋል። በወንዶች ግማሽ ማራቶን ጤናው በለጠ  አንደኛ ሲሆን ርቀቱን ለማጠናቀቅ 1 ሰዓት ከ 3 ደቂቃ ከ 23 ሰከንድ ወስዶበታል። ሀብታሙ ካሳሁን 1 ሰዓት ከ 3 ደቂቃ ከ 45 ሰከንድ በሆነ ሰዓት በሁለተኝነት አጠናቋል። ሀብታሙ ካሳሁን ውድድሩን ለማጠናቀቅ በግማሽ ማራቶን ሶስተኛ የሆነው የፍቃዱ ግርማ ሲሆን ከሀብታሙ በ 10 ሴኮንድ ዘግይቶ ገብቷል። በሴቶቹ የግማሽ ማራቶን የሩጫ ውድድር የውብዳር ተሾመ ውድድሯን በአንደኝነት ስታጠናቅቅ የወሰደባት ሰዓትም 1 ሰዓት ከ 15 ደቂቃ ከ 43 ሴኮንድ ነው። እምሻው ንጉሴ በሁለት ሴኮንድ በየውብዳር ተቀድማ ሁለተኛ ሆና ውድድሯን አጠናቃለች። በሴቶች ግማሽ ማራቶን ሶሰተኛ የሆነችው ኑሪት ሽመልስ ስትሆን የወሰደባት ሰዓትም 1 ሰዓት ከ 16 ደቂቃ ከ 15 ሴኮንድ ወስዶባታል። በሀዋሳ ከተማ ታላቁ ሩጫ ሲካሄድ ዘንድሮ ለአምስተኛ ጊዜ ነው። በዚህ ውድድር አሸናፊዋች በአጠቃላይ 64 ሺህ ሁለት መቶ ብር ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። በሴትም በወንድም አንደኛ ሆነው ውድድራቸውን ለጨረሱ 14 ሺህ ብር ሽልማት ሲያገኙ ሁለተኛ ሆነው የጨረሱ 7 ሺህ ብር ተሸልመዋል፡፡ ሶስተኛ የወጡት ደግሞ 4 ሺህ ብር ተሸልመዋል።

ያላረፈው አየር ማረፊያ እንዳያፋጀን!

Image
ከማህበራዊ መረብ የተገኘ በ ደሳለኝ መሳ በኢትዮጵያ ውስጥ ባሉ ክልሎች መካከል የመሰረተ ልማትና የልማት ልዩነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየሰፋ መምጣቱን የተለያዩ ፀሐፊዎችና ባለሙያዎችም ጭምር ይስማሙበታል፡፡ መንግሰት በየጊዜ ፍትሐዊ የሀብት ክፍፍል በክልሎች መካከል አረጋግጫለው ብሎ ቢከራከርም በተጨባጭ ከሚታየው ነገር አንፃር የኢህአዴግ ክርክር ውሃ የሚቋጥር አልሆነም፡፡ በዚህ መጣጥፍ ልያነሳ የፈለኩት መንግስት ለአየር ማረፊያ ግንባታን ለማስፋፋት ካለው ፍላጎትና ተግባር አንፃር የፍትሐዊነት ጉድለት እንዳለው ከማሳየትም አልፎ አሁን በሲዳማ እየተሞከረው ያለው ነገር ከጥቅሙ ጉዳቱ ሊያመዝን እንደምችል ለማመላከት ነው፡፡ ማንም ሰው ለመገንዘብ እንደምችለው ( አልገነዝብም ካሉት ውጭ ) ሐዋሳ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሳች ካለችው የጎብኚዎች ሳቢቷና ከአካባቢም ከሚገኘው የኢኮኖሚ ወሳኝነቷ አንጻር አየር ማረፍያ አስፈላጊ ብቻ ሳይሆን አንገብጋቢ ጉዳይ ነው፡፡ ነገር ግን ይህ ነገር እስከ አሁን ድረስ ተፈፃሚ አልሆነም፤ ሀዋሳና አካባቢውም እድለኛ መሆን አልቻለም፡፡ ሀዋሳና አካባቢዋ አንድ አየር ማረፍያ እንኳን ሳይኖራት የተለያዩ ከልሎች ከአንድ በላይ አየር ማረፊያ ተከፋፍለዋል፡፡ ለምሳሌ የትግራይን ክልልን ብናይ በቅርቡ ዓለም አቀፍ በረራ ማስተናገድ ከጀመረው የመቐለ “አሉላ አባነጋ” አየር ማረፍያ በተጨማሪ በሌሎች አራት ከተሞች የሀገር ውስጥ በረራ የሚያስተዳግዱ አየር ማረፊያዎች ተገንብቶላቸዋል፡፡ በአማራ ክልልም በቅርቡ ወደ ጎሮቤት ሀገር በረራ ማስተናገድ የጀመረውን የባህር ዳሩን ጨምሮ በጎንደርና በወሎ የሀገር ውስጥ በረራ የሚያስተናግዱ አየር ማረፊያዎች አላቸው፡፡ ከባህር ዳር እሰከ ጎንደር ያለው ርቀት 225 ኪ . ሜ ሲሆን በዚህ ርቀት ሁለት አየር ማረፊያ አላት የአ

Of Elections and Diapers in Ethiopia in 2015 | Somalilandpress.com | Somali News Online from Somaliland – Somalia and Horn of Africa

Image
Of Elections and Diapers in Ethiopia in 2015 | Somalilandpress.com | Somali News Online from Somaliland – Somalia and Horn of Africa

የሲዳማ ፓርቲዎች ህብረት ለነጻነት እና ፍትህ (USPFJ)፤ የራሷ እያረረባት የሰው ታማስላለች!

Image
የሲዳማ ፓርቲዎች ህብረት ለነጻነት እና ፍትህ የሰሞኑ ጋዜጣዊ መግለጫ በኣንባቢያ ዘንድ ክርክር ጫረ የተባበሩት የሲዳማ ፓርቲዎች ለነጻነት እና ፍትህ በምጻረ _ ቃል (USPFJ) ሰሞኑን በኢትዮጵያ ውስጥ በኦሮሞ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ላይ በኣገሪቱ የጸጥታ ኃይሎች የተወሰደውን የኃይል እርምጃ በመቃወም ጋዜጣዊ መግለጫ ስጥቷል። በመግለጫውም ለበርካታዎች ሞት እና ኣካል ጉዳት ምክንያት የሆነውን የመንግስት እርምጃ ኮንኗል። ይህንን የድርጅቱን መግለጫ የወራንቻ ኢፎርሜሽን ኔትዎርክ ከጋዳ ድህረገጽ ላይ በማግኘት ለኣንባቢያኑ ያደረሰ ሲሆን፤ የህብረቱን ጋዜጣዊ መግለጫ ተከትሎ የተለያዩ ሰዎች ኣስተያየት በመስጠት ላይ ናቸው። በርካታ ኣንባቢያን ለወራንቻ ኢንፎርሜሽን ኔትዎርክ በጻፏቸው መልዕክቶች እንዳመለከቱት፤ የተባበሩት የሲዳማ ፓርቲዎች ህብረት ለነጻነት እና ፍትህ፤ በበርካታ ሲዳማውያንን እና የሰብኣዊ መብት ተከራካሪ ድርጅቶች የተወገዘውን፦ የኢትዮጵያ የጸጥታ ኃይሎች በቅርቡ በሃዋሳ ከተማ የኣላሙራ እና ታቦር ከፍተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሲዳማ ተወላጅ ተማሪዎች ላይ የወሰዱትን የኃይል ጥቃት ካለማውገዙ በላይ በጥቃቱ ልጆቻቸው ለተጎዱባቸው ቤተሰቦች ኣጋርነቱን ኣለመግለጹን እንዳዛዘናቸው ገልጸዋል። ከኣስተያየት ስጪዎቹ መሃከል፦ ስሙን T H በማለት የጠራው እና የዩቨርሲቲ መምህር መሆኑን የገለጸው ኣስተያየት ሲጪ እንዳለው፤ ህብረቱ ምንም እንኳን እታገልለታለው ከሚለው ህዝብ ጋር የግንባር ለግንባር ግንኙነት የሌለው ብሆንም ባለፉት ኣመታት በሲዳማ ውስጥ ያለውን የፖለቲካ እና ስብኣዊ መብት ጥስቶችን በማጋለጥ ከፍተኛ ሚና መጫወቱን ኣስተውሰዋል። ኣክለውም ህብረቱ በቅርቡ በኦሮሞ ተማሪዎች ላይ በመንግስት የተወሰደውን የኃይል እር

በአዲስ አበባ ዙሪያ ገበሬዎች የሚፈናቀሉት ያለ በቂ ዝግጅት ነው ተባለ፤ ተመሳሳይ እድል ለገጠማቸው የሃዋሳ ዙሪያ ገበሬዎችስ ምን ታስቦል?

Image
የመሬት ወረራ መስመር ሰሜን፦ዳቶ ኦዳሄ ሰሞኑን ኣዲስ ኣድማስ ጋዜጣ እንዳስነበበው በኣዲስ ኣበባ ዙሪያ ኣርሶ ኣደሮች ያለ በቂ ዝግጅት በተለያዩ  ምክንያቶች ከመሬት ይዞታቸው የሚፈናቀሉ ሲሆን፤ ተፈናቃዮቹም ለተለያዩ ችግሮች በመጋለጥ ላይ መሆናቸውን ኣትቷል። በተመሳሳይም ልክ እንደ ኣዲስ ኣበባ ዙሪያ ገበሬዎች የሃዋሳ ዙሪያ ኣርሶ ኣደሮችም ለላፉት 20 ኣመታት ተመሳሳይ ከመሬት ይዞታቸው በተለያዩ ምክንያቶች የመፈናቀል እድል ገጥሞቸዋል። የመሬት ወረራ መስመር ምስራቅ፦ ጫፌ ( ከሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ጀርባ ) እነዚሁ ተፈናቃዮች በከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ችግር ውስጥ ከመግባታቸው ባሻገር የኣገር ሽክም በመሆን ላይ ናቸው። መንግስት ይህን መሰል ያለ በቂ ዝግጅት የምደረግ የኣርሶ ኣደር የማፈናቀል ተግባራ ለመግታት ምን እያደረገ ነው? ለማንኛውም ስለ ሃዋሳ ዙሪያ ተፈናቃይ ኣርሶ ኣደሮች በሌላ ጊዜ እንመለስበታለን፤ ለኣሁኑ ግን ስለ ኣዲስ ኣበባ ዙሪያ ገበሬዎች ከታች ያንቡ፦ የመሬት ወረራ መስመር ደቡብ፦ ሎቄ ከግማሽ ሚሊዮን እስከ 2 ሚሊዮን ብር ካሣ የተከፈላቸው ገበሬዎች አሉ በተከፈላቸው ካሣ ንድግ ጀምረው የተሳካላቸው ጥቂቶች ናቸው          “ቦታው ለሪል እስቴትና ለልማት ይፈለጋል ተብለን የእርሻ መሬታችንና የመኖሪያ ቦታችን በመንግስት ከተወሰደብን አራት አመታት ሞላን” ይላሉ - በሰበታ አዋስ ወረዳ እያረሱ ይኖሩ እንደነበር የገለፁ አርሶአደሮች፡፡ ለእርሻ መሬት እንደየስፋቱ ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ ካሳ የተከፈላቸው ገበሬዎች መኖራቸው አይካድም፡፡ ለመኖሪያ ቤትም 24 ሺ ብር ድረስ ካሳ እንደተከፈላቸውና ቤት መስሪያ ቦታ እንደሚሰጥም ቃል ተገብቶላቸው እንደነበር የተፈናቀሉ ገበሬዎች ያስታውሳሉ፡፡ “ከዛሬ ነገ ቦታ ተሰጥቶን ባለችን ብ