Posts

ደቡብ ግሎባል ባንክ ወደ አትራፊነት መግባቱን ገለጸ

Image
- የኮር ባንኪንግ ቴክኖሎጂ ግዥ ፈጸመ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በኢትዮጵያ በባንክ ኢንዱስትሪ ውስጥ ለመሰማራት ይጠየቅ የነበረውን የተከፈለ 100 ሚሊዮን ብር ወደ 500 ሚሊዮን ብር ከማሳደጉ በፊት 15ኛው የግል ባንክ በመሆን የአገሪቱን የባንክ ኢንዱስትሪ የተቀላቀለው ደቡብ ግሎባል ባንክ 19 ወራት አስቆጥሯል፡፡ ከሌሎች የግል ባንኮች በተለየ በአንድ የአክሲዮን ሽያጭ ፕሮግራም በሚሊዮን የሚቆጠር አክሲዮን በመሸጥ በ138.9 ሚሊዮን ብር የተከፈለ ካፒታል በማሰባሰብ ወደ ሥራ የገባ ባንክ ነው፡፡ በ5481 ባለአክሲዮኖች የተመሠረተው ይህ ባንክ ወደ ሥራ ከገባ በኋላ በመጀመርያው የሥራ ዓመት (10 ወራት) አትራፊ መሆን ባይችልም በአሁኑ ወቅት ግን ወደአትራፊነት እየገባ መሆኑን ባንኩ አስታውቋል፡፡ የባንኩን የ19 ወራት የሥራ እንቅስቃሴ በተመለከተ በተሰጠ መግለጫ ላይ እንደተመለከተው፣ ባንኩ መጋቢት 2006 ዓ.ም. 14.5 ሚሊዮን ብር አትርፏል፡፡ የባንኩ ፕሬዚዳንት አቶ ወርቁ ለማ እንደገለጹት፣ በመጀመርያው ዓመት ላይ ተመዝግቦ የነበረው ኪሳራ አሁን መለወጡንና በየወሩ እያተረፈ መጓዝ ጀምሯል፡፡ በመጀመርያው የሥራ ዘመንም ትርፍ ይገኛል ተብሎ ባይጠበቅም ደቡብ ግሎባል ባንክ ግን በአጭር ጊዜ ወደ ትርፍ መግባት ከመቻሉም በላይ አሁን እያስመዘገበ ያለው ትርፍ በ2006 በጀት መዝጊያ ጥሩ ትርፍ የሚያገኝ መሆኑን ያሳያልም ብለዋል፡፡ በመጋቢት 2006 ዓ.ም. ያስመዘገበው የትርፍ መጠንም አምና ከነበረው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር 223 በመቶ ብልጫ ያለው ነው፡፡  ባንኩ ትርፍ ማስመዝገብ ከመጀመሩ ባሻገር በዋና ዋና የባንክ አገልግሎቱ እያደገ መምጣቱን የፕሬዚዳንቱ ገለጻ ያስረዳል፡፡ የባንኩ የሥራ እንቅስቃሴ በለውጥ ጎዳና ላይ ስለመሆኑም ዋና

ገዥው ፓርቲ በከተማ ኣስተዳደር ስም በሲዳማ የፈጸመውን ኣይነት የመሬት ወረራ በኣሮሚያ ልዩ ዞኖች መድገም ኣልቻለም

Image
ገዥው ፓርቲ በከተማ ኣስተዳደር ስም በሲዳማ ዞን ሃዋሳ ዙሪያ ወረዳ ውስጥ ይገኙ የነበሩትን የገጠር ቀበሌዎችን በሃዋሳ ከተማ ኣስተዳደር ስር በማጠቃለል በልማት ስም የኣርሶ ኣደሮች ይዞታ የሆነውን መሬት በመንጠቅ በልዝ ለባለጋብቶች ለማከፋፈል እና ኣርሶ ኣደሮችን መሬት ኣልባ ለማድረግ በኦሮሚያ ክልል ያደረገው ጥረት ኣለመሳካቱ ሰሞኑን ተሰምቷል። ዝርዝር ዜና የሪፖርተር ጋዜጣ ነው።   የኦሮሚያ ልዩ ዞኖችን በሚያጠቃልለው ማስተር ፕላን ላይ መግባባት አልተቻለም - በክልሉ የሚንቀሳቀሱ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች ማስተር ፕላኑን ተቃወሙ -ከአዲስ አበባ አዳማ በአዲሱ መንገድ ግራና ቀኝ መሬት መሸጥ ቁጥጥር ሊደረግበት ነው አዲስ አበባ ከተማና በዙሪያዋ የሚገኙትን አምስት ልዩ የአሮሚያ ዞን ከተሞች  ሰበታ፣ ቡራዩ፣ ሱሉልታ፣ ለገጣፎና ገላን አጠቃሎ በተሠራው ማስተር ፕላን ላይ መግባባት ባለመቻሉ ግምገማዊ ውይይት በማድረግ የመግባቢያ ፊርማ ለማድረግ የተጀመረው ስብሰባ ሳይጠናቀቅ መቋረጡን ምንጮች ለሪፖርተር ገለጹ፡፡ መጋቢት 19 ቀን 2006 ዓ.ም. የልዩ ዞኑና የአዲስ አበባ ከተማ ተወካዮች በማስተር ፕላኑ አስተዳደራዊ ጉዳዮች ላይ ለመወያየት የተሰበሰቡ ቢሆንም፣ በተሠራው ማስተር ፕላን ላይ አንድ ዓይነት አቋም ሊይዙ አለመቻላቸው ታውቋል፡፡ ከአንዳንድ ተሳታፊዎች መግባባቱን ወደኋላ ሊመልሱ የሚችሉ ጥያቄዎችና አስተያየቶች በመነሳታቸው፣ በዕለቱ ይካሄዳል ተብሎ በነበረው የጋራ ውይይት ላይ ልዩነት መፈጠሩን ምንጮች አስረድተዋል፡፡ በአዳማ በተደረገው ውይይት በልዩ ዞኖቹ በኩል የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አብዱልአዚዝ መሐመድና አዲስ አበባን በመወከል ከንቲባ ድሪባ ኩማ በጋራ ውይይቱን የመሩት ቢሆንም፣ በውይይቱ የተሳተፉ የተለያዩ ቢ

2ኛው ዙር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬና ነገ ይካሄዳል፤ ሃዋሳ ከነማ ከመብራት፧ ሲዳማ ቡና ከመከላከያ ይጫወታሉ

Image
2ኛው ዙር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬና ነገ ይካሄዳል፤ ሃዋሳ ከነማ ከመብራት፧ ሲዳማ ቡና ከመከላከያ ይጫወታሉ መልካም እድል ለሲዳማ ክላቦች አዲስ አበባ ፣ ሚያዚያ 4 ፣ 2006 ( ኤፍ.ቢ.ሲ. ) ሁለተኛው ዙር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬና ነገ ይካሄዳል። ዛሬ ወላይታ ዲቻ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 9 ሰዓት ላይ ሲገናኙ ፤ መብራት ሃይል ከሃዋሳ ከነማ በ11 ሰዓት ከ30 ላይ ይጫወታሉ። ነገ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከሙገር በአዲስ አበባ ስታዲየም 10 ሰዓት ላይ ይገናኛሉ። አርባ ምንጭ ከነማ ከኢትዮጵያ መድህን ፣ ሲዳማ ቡና ከመከላከያ ፣ ዳሽን ቢራ ከሃረር ቢራ በተመሳሳይ 9 ሰዓት ላይ ይጫወታሉ። በሌላ በኩል ሊጠናቀቅ  አምስት ሳምንታት በቀረው በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ስቶክ ሲቲ ከኒውካስትል ፣ ስንደርላንድ ከኤቨርተን ፣ ዌስት ብሮም ከቶተንሃም በተመሳሳይ 11 ሰዓት 07 ላይ ይገናኛሉ። ነገ የሊጉ መሪ ሊቨርፑል ሁለት ተስተካካይ ጨዋታ ካለውና በሊጉ የደረጃ ሰንጠረዥ በሶስተኛነት ከተቀመጠው ማንቸስተር ሲቲ ጋር 9 ሰዓት ከ37 ላይ የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው። ቸልሲ በበኩሉ ከሜዳው ውጭ ስዋንሲን 12 ሰዓት ከ07 ላይ ይገጥማል። በእንግሊዝ ኤፍ ኤ ካፕ የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ ዛሬ አርሰናል ከዊጋን አትሌቲክ ምሽት 1 ሰዓት ከ07 ላይ ጨዋታውን  ያደርጋል። በፕሪሚየር ሊጉና በኤፍ ኤ ካፕ ጨዋታዎች የተጨመረው 7 ደቂቃ ፥ ከሃያ አራት አመታት በፊት ሊቨርፑል ከኖቲንግሃም ፎረስት ሲጫወቱ የደረሰውን የሂልስ ቦሮውን አደጋ ለማስታወስ መሆኑ ተገልጿል። በ33ተኛው ሳምንት የስፔን ላሊጋ ዛሬ ግራናዳ ከባርሴሎና 3 ሰዓት ላይ ሲገናኙ ፤ ሪያል ማድሪድ ከአልሜሪያ ምሽት 5 ሰዓት ላይ ይጫወታሉ።

Ethiopia’s coffee industry booms

Image
Since late last year, a severe drought has stunted growth on coffee plantations in the heart of Brazil’s coffee-growing region and this is reportedly stimulating a resurgence in the Ethiopian coffee industry, whose value has risen to an astonishing 17.5% in one week. Reports indicate that demand for Ethiopian coffee has risen sharply with exporters inking deals worth millions of dollars/pounds. Just two months ago, a pound of exportable washed coffee was traded on the Ethiopian Commodity Exchange (ECX) for 1.15 dollars/pound(0.45kgs). Despite being renowned to be one of the world’s best sources of coffee, a  study  has revealed that only a meagre 1% of Ethiopia’s coffee is sold as specialty. After the drought in the coffee producing belt of Brazil, the price of coffee in the market has shown an increase of 32.5 pc in a matter of 20 days, according to ICE. This drought, which has been described as ‘historic’, has forced more than 140 cities in Brazil to ration water. Rep

መከላከያ ሚኒስቴር የሠራዊቱን ወቅታዊ የብሔር ተዋጽኦ ለፓርላማ ይፋ አደረገ፤ ሲዳማን እና ወላይታን በብዛት የያዘው ደቡብ ሁለተኛ ደረጃ ይዟል

Image
ሰሞኑን የመከላከያ ሚኒስቴር የሰራዊቱን ወቅታዊ የብሄር ተዋጽኦ ለፓርላማ ይፋ ያደረገ ሲሆን ለዘመናት በሰራዊቱ ውስጥ በቁጥርም በጥራትም የበላይነት እንደያዘ የሚነገርለት የትግራይ ክልል በኣማራ ክልል የተተካ መሆኑን ታውቋል። በደቡቦች በመመራት ላይ በሚገኘው መከላከያ ሚኒስቴር ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሰራዊቱ የደቡብ ክልል በቁጥር እያደገ የመጣ ሲሆን፤ በብዛት ሲዳማን እና ወላይታን እንደያዘ የተገመተው የደቡብ ክልል በኣሁኑ ጊዜ በብዛት ሁለተኛ ደረጃ ይዟል።  ለዝርዝር ዜናው ከስር ይመልከቱ፦ foto ከድረገጽ Ethiopian reporter በሕገ መንግሥቱ በተደነገገው መሠረት የአገር መከላከያ ሠራዊት የብሔር ተዋጽኦን ለማመጣጠን እየሠራ መሆኑንና በአሁኑ ወቅትም የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ውክልና በሁለተኛ ደረጃ ላይ መድረሱን፣ የመከላከያ ሚኒስትሩ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ይፋ አደረጉ፡፡  ሚኒስትሩ አቶ ሲራጅ ፈጌሳ ባለፈው ሳምንት የመከላከያ ሚኒስቴርን የግማሽ ዓመት የሥራ አፈጻጸም ለፓርላማው ባቀረቡበት ወቅት ነው የሠራዊቱ የብሔር ተዋጽኦ እየተመጣጠነ መምጣቱን የገለጹት፡፡   በሚኒስትሩ ሪፖርት መሠረት ከአጠቃላይ የመከላከያ ሠራዊቱ አባላት የአማራ ብሔር ተዋጽኦ 30.3 በመቶ በመሆን ከ2004 ዓ.ም. ጀምሮ በአንደኛነት ሲመራ የቆየ ሲሆን፣ በ2006 ዓ.ም. 29.46 በመቶ በመሆን በቀዳሚነት እየመራ ይገኛል፡፡ የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ተዋጽኦ ደግሞ በ2006 ዓ.ም. 25.05 በመቶ በመሆን በሁለተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ በሪፖርቱ ተመልክቷል፡፡ የኦሮሞ ብሔር በ2004 ዓ.ም. በ25.2 በመቶ የሁለተኛነት ድርሻ ይዞ የነበረ መሆኑን፣ በ2006 ዓ.ም. ግን ወደ 24.45 በመቶ በመውረድ የሦስተኛ ደረጃን እ