Posts

መከላከያ ሚኒስቴር የሠራዊቱን ወቅታዊ የብሔር ተዋጽኦ ለፓርላማ ይፋ አደረገ፤ ሲዳማን እና ወላይታን በብዛት የያዘው ደቡብ ሁለተኛ ደረጃ ይዟል

Image
ሰሞኑን የመከላከያ ሚኒስቴር የሰራዊቱን ወቅታዊ የብሄር ተዋጽኦ ለፓርላማ ይፋ ያደረገ ሲሆን ለዘመናት በሰራዊቱ ውስጥ በቁጥርም በጥራትም የበላይነት እንደያዘ የሚነገርለት የትግራይ ክልል በኣማራ ክልል የተተካ መሆኑን ታውቋል። በደቡቦች በመመራት ላይ በሚገኘው መከላከያ ሚኒስቴር ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሰራዊቱ የደቡብ ክልል በቁጥር እያደገ የመጣ ሲሆን፤ በብዛት ሲዳማን እና ወላይታን እንደያዘ የተገመተው የደቡብ ክልል በኣሁኑ ጊዜ በብዛት ሁለተኛ ደረጃ ይዟል።  ለዝርዝር ዜናው ከስር ይመልከቱ፦ foto ከድረገጽ Ethiopian reporter በሕገ መንግሥቱ በተደነገገው መሠረት የአገር መከላከያ ሠራዊት የብሔር ተዋጽኦን ለማመጣጠን እየሠራ መሆኑንና በአሁኑ ወቅትም የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ውክልና በሁለተኛ ደረጃ ላይ መድረሱን፣ የመከላከያ ሚኒስትሩ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ይፋ አደረጉ፡፡  ሚኒስትሩ አቶ ሲራጅ ፈጌሳ ባለፈው ሳምንት የመከላከያ ሚኒስቴርን የግማሽ ዓመት የሥራ አፈጻጸም ለፓርላማው ባቀረቡበት ወቅት ነው የሠራዊቱ የብሔር ተዋጽኦ እየተመጣጠነ መምጣቱን የገለጹት፡፡   በሚኒስትሩ ሪፖርት መሠረት ከአጠቃላይ የመከላከያ ሠራዊቱ አባላት የአማራ ብሔር ተዋጽኦ 30.3 በመቶ በመሆን ከ2004 ዓ.ም. ጀምሮ በአንደኛነት ሲመራ የቆየ ሲሆን፣ በ2006 ዓ.ም. 29.46 በመቶ በመሆን በቀዳሚነት እየመራ ይገኛል፡፡ የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ተዋጽኦ ደግሞ በ2006 ዓ.ም. 25.05 በመቶ በመሆን በሁለተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ በሪፖርቱ ተመልክቷል፡፡ የኦሮሞ ብሔር በ2004 ዓ.ም. በ25.2 በመቶ የሁለተኛነት ድርሻ ይዞ የነበረ መሆኑን፣ በ2006 ዓ.ም. ግን ወደ 24.45 በመቶ በመውረድ የሦስተኛ ደረጃን እ

የመብት ጥያቄ ያነሱት የሲዳማ ተማሪዎች በኣሸባሪነት ልከሰሱ መሆኑ ተሰማ፤ገዥው ፓርቲ ከተማሪዎቹ ንቅናቄ ጀርባ የሲኣን እጅ ኣለበት በማለት ላይ ነው

Image
ባለፈው ሳምንት በሃዋሳ ከተማ በኣላሙራ እና በታቦር ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የምማሩ የሲዳማ ተማሪዎች በየትምህርት ቤቶቹ ለሲዳምኛ ቋንቋ ትኩረት ተነፍጎታል በማለት ሲዳምኛ ቋንቋ በትምህርት ቤቶቹ የሰራ ቋንቋ መሆን ኣለበት በምል እና ሌሎች የመብት ጥያቄዎችን ኣክለው ድምጻቸውን ባሰሙ ተማሪዎች እና በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች በማካከል በተፈጠረው ግጭት የታሰሩት ተማሪዎች በኣሽባርነት ለመክሰስ መንግስት እየተዘጋጀ ነው። ሪፖርተራችን ጥቻ ወራና ከሃዋሳ እንደዘጋበው ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ እና በተለያዩ ክፍለ ከተማዎች ተበታትነው ታስረው ከሚገኙት ተማሪዎች መካከል 25 ቱን በኣሸባሪነት ለመክሰስ ኣቃቤ ህግ መረጃ በማሰባሰብ ላይ መሆኑ ታውቋል። በጉዳዩ ጋር በተያያዘ የከተማው ኣስተዳደር የተማሪዎቹን ቤተሰቦች ባለፈው ቅዳሜ ለማናገር የሞከረ ሲሆን፤ በሰብሰባው ላይ የተገኙት የተማሪዎቹ ቤተሰቦች መንግስት በህጻናቱ ላይ የኃይል እርምጃ ከወሰደ በኃላ ልጆቻችሁን ምከሩ የምል መልዕክት ማስተላለፉ የሲዳማን ባህል ያልተከተለ መሆኑን በመግለጽ ቁጣቸውን ኣሰምቷል። እንደተማሪዎቹ ቤተሰቦች ከሆነ፤ በሲዳማ ባህል መሰረት ልጆች ካጠፉ ለወላጆቻቸው ተነግሮ ወላጆቻቸው እንድመክሯቸው ይደረጋል እንጅ የኃይል እርምጃ በመውሰድ በልጆቹ ላይ ጉዳት ካደረሱ በኃላ ምክሩ ማለት ኣግባብነት የለው ብለዋል። በተያያዘ ዜና ከተማሪዎቹ ንቅናቄ ጀርባ የሲኣን / መድረክ እጅ ኣለበት በማለት የገዥው ፓርቲ የተማሪዎቹን ንቅናቄ ፖለቲካዊ ገጽታ በመስጠት ላይ ነው። እንደሪፖተራችን ጥቻ ወራና ገለጻ ከሆነ፤ ገዥው ፓርቲ የተማሪዎቹን የመብት ጥያቄ በኣግባቡ ከመመለሰ ይልቅ ንቅናቄውን ፖለቲካዊ ገጽታ በማላበስ ሲኣንን የመሳሰሉ ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች

የሀዋሳ መስፋፋትና የሲዳማ ህዝብ ፈተና

Image
ከማህበራዊ መረብ ላይ የተገኘ ጽሁፍ ተጻፈ በደሳለኝ መሳ  ምንጭ፦  Desalegne Mesa ከቅርብ ዓመታት (1950ዎቹ) ወዲህ ከተመሰረተቱት ከተሞች አንፃር ሐዋሳ ጥሩ የሚባል እድገት ጎዳና ላይ እንዳለች የሚታወቅ እውነታ ነው፡፡ በተለይም ተፈጥሮ በለገሰቻት ውበት ምክንያት ሁሉም ሰው ለማለት በሚያስችል መልኩ ልቡ ወደ ሀዋሳ ሽፍተዋል፡፡ ነጋዴዎች ፣ ጎብኝዎች የመንግሥትና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ምርጫና መሰብሰቢያ አየሆነች መታለች አዳሬ-ሐዋሳ፡፡ ይህንን የህዝብ ፍልሰትንና ፍላጎት ለማስተናገድና ለማርካት ይመስላል የተለያዩ ሰማይ ጠቀስ ህንፃዎች(የማን ናቸው?) መበራከት ጀምረዋል፡፡ የተጠቀሱት ሁሉ የከተማዋን ተጨማሪ ውበት ስለምሰጡ ጥሩ ናቸው፡፡ ከዚህም ያለፈ የተለያዩ ፀሐፊዎች ስለ ሀዋሳ ውበት፣ ሳቢነት፣ ሳብነቱን ተከተሎ እየተከሰቱ ያሉትን ወጣ ያሉ ተግባራትንና የሀዋሳ ሂሊውና የሆነው የሀዋሳ ሀይቅ ብክለትና ስለተደቀነበት ፈተና ጽፈዋል፤ ለሚመለከታቸው ይጠቅማል ያሉትን አስተያየቶችንም ለመሰንዘር ጥረት አድርገዋል፤ የሚሰማ ከተገኘ፡፡ ነገር ግን የዚህ ፅሑፍ አዘጋጅ ትኩረት ለመስጠት የሚፈልገው የከተማውን ያልተጠና መስፋፋትን ተከትሎ እተጎዳ ስላለው ህብረተሰብና ስለተደቀነበት አደጋ ይሆናል፡፡  ከላይ የተጠቀሱት የከተማይቱ መሳጭ ጎኖች ቢኖሩትም በዛው ልክ ደግሞ የህዝብ መከራ የሚያበዙ፣ ከአካባቢ ወጣ ያሉና የምዕራባውያን ባህል መበራከትና ነባሩን የአካባቢውን ባህልና ትውፍት በመዋጥ ረገድ ከፍተኛ አሉታዊ ተፅዕኖ ያሳድራሉ፡፡ ይህ ወጣ ያለ ነገር እንዳይከሰት ለህዝብና ባህሉ የሚቆረቆር ስርዓት መገንባትና ስርዓቱን የሚመሩ ሰዎችም የአካባቢውን ባህልና ትውፍት በሰለጠነ መልኩ ለጎብኝዎችና ለአዲስ ከታሚ ህዝብ በማቅረብ የባእድ

በኣላሙራ እና ታቦር ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የተነሱ ጥያቄዎችን እንደምደግፉ ኣንዳንድ የሃዋሳ ከተማ ነዋሪዎች ኣስታወቁ፤ የሲዳማ የፖለቲካ ፓርቲዎች የኃይል እርምጃውን ኣለማውገዛቸው እንዳዛዘናቸው ገለጹ

Image
ሪፖርተራችን ሚሊዮን ማቲያስ በጉዳዩ ላይ ያናገራቸው በቱላ ክፍለ ከተማ በንግድ ስራ ላይ የሚተዳደሩ ካላ ማርቆስ ሪብሳ በሰጡት ኣስተያየት መንግስት በተለያዩ ጊዜት የተለያዩ የመብት ጥያቄ ያነሱ ተማሪዎች ላይ የኃይል እርምጃ መውሰዱን ኣስታውሰው፤ በተማሪዎቹ ለተነሱት ጥያቄዎች በኣግባቡ ምላሽ ከመሰጠት ይልቅ የኃይል እርምጃ መውሰድ መልካም ኣስተዳደር እና ዴሞክራሲን ኣሰፍናፈው ከምል መንግስት የምጠበቅ ኣይደልም ብለዋል። ኣክለውም መንግስት የመብት ጥያቄ በምያነሱት ላይ የኃይል እርምጃ በመውሰድ የማይቀለበሰውን የመብት ጥያቄ ለመቀልበስ ከመሞከር ሌላ ሰላማዊ ኣማራጭ መንገዶችን መምረጥ ኣለበት ብለዋል። በሃዋሳ ከተማ ኣረብ ሰፈር ነዋሪ የሆኑት እና ስማቸውን እንድጠቀስ ያልፈለጉት ሌላው ኣስተያየት ስጪ በበኩላቸው ሰሞኑን የኣላሙራ እና ታቦር ትምህር ቤቶች የሲዳማ ተማሪዎች ያነሳቸውን ጥያቄዎችን እንደምደግፉ ገልጸው፤ በከተማው በምገኙ ትምህርት ቤቶች ለሲዳምኛ ቋንቋ ትኩረት እንድሰጠው መጠየቅ ስህተት ኣለመሆኑን ኣስረድተዋል። እኝሁ ኣስተያየት ሰጪ ኣንዳብራሩት፤ የኣገሪቱ ህገ መንግስት ብሄር፤ ብሄረሰቦች እና ህዝቦች በራሳቸው ቋንቋ መማር መብት ከደነገገበት ወቅት ጅምሮ በመላው ኣገሪቷ ትምህርት በኣከባቢው ቋንቋ በመሰጠት ላይ ሳለ እዚህ ሃዋሳ ከተማ ተግባራዊ ኣለመደረጉ ኣግባቢነት የለውም። በሃዋሳ ከተማ ሰፈረ ሰላም ያገኛናቸው ሌላዋ ኣስተያየት ሰጪ በበኩላቸው የተማሪዎቹ ጥያቀ የእርሳቸውም ጥያቄ መሆኑን ጠቁመው፤ ሃዋሳ ከተማ በምገኙ በመንግስት ትምህርት ቤቶች ብቻ ሳይሆን በግል ትምህርት ቤቶችም ጭምር በሲዳምኛ ቋንቋ ትምህርት ላይ ትኩረት እንድሰጥ እንደምፈልጉ ተናግረዋል። በተያያዘ ዜና የሲዳማ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሰሞኑን የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች

Ethiopia: Two Side to Ethiopia - the Plea for Press Freedom

Image
OPINION There are two Ethiopias. Or better said there two narratives about Ethiopia. On one side, there is the Ethiopia as celebrated by the international aid community and the European Union : a country which is growing fast and seriously fighting poverty, a country which wisely uses the considerable international assistance that it receives to channel it towards sustainable development. On the other side there is the Ethiopia as criticized by press freedom and human rights groups. A country ruled by an authoritarian regime, the second largest jailer of journalists in Africa, a country which misuses laws on anti-terrorism and civil society regulation to chill speech and prevent journalists from doing their legitimate watchdog work. Press freedom groups do not deny the economic and social realities of Ethiopia, but they also warn about the negative effects and features of the current model that Ethiopia's sycophants do not want to address. "In Ethiopia," wr