Posts

በሐዋሳ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከመልካም ተሞክሮ ባሻገር ጥቃቅን ችግሮችም አይናቁ

Image
ወደ ሐዋሳ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ግቢ ስዘልቅ ሞቃታማ አየሯን የምትረጨውን ፀሐይ ተቋቁመው በየትምህርት መስካቸው ተግባራዊ ልምምድ የሚያደርጉ ተማሪዎች እዚህም እዚያም ሲታትሩ ታይተውኛል። በስተቀኝ በመንገድ ሥራ የሚሠለጥኑ ተማሪዎች አፈሩን እየደለደሉና እየጠቀጠቁ ጥራት ያለው መንገድ እንዴት መሥራት እንደሚቻል ተግባራዊ ልምምድ ሲያደርጉ፤ በስተግራ ደግሞ በኮብል ስቶን ሥራ እና በቅየሳ የሚሠለጥኑ ተማሪዎች በየሙያቸው የሚያስፈልጓቸውን ቁሶች ታጥቀው ሙሉ ትኩረታቸውን በልምምዱ ላይ አድርገው ይታያሉ። ከተማሪዎቹ መካከል ወደ አንዱ ጠጋ ብዬ  « ሥልጠና እንዴት ነው ?»  የሚለውን የጋዜጠኛ ጥያቄዬን አስቀደምኩ። ተማሪው አራርሶ ወልዴ ይባላል። የመጣው ከሀዲያ ዞን ሾኔ ከሚባል አካባቢ ነው። የሦስተኛ ዓመት የመንገድ ሲቪል ዎርከ ሠልጣኝ ሲሆን፤ በኮሌጁ በነበረው ቆይታ በክፍተትና በመልካም ተሞክሮነት የሚጠቀሱ ጉዳዮችን እንዲህ በማለት ይገልጽልኝ ጀመር  «  ባለፉት ዓመታት የመምህራን እጥረት ነበር። በሳምንት አምስት ቀን መማር ቢኖርብንም አንዳንድ ቀን መምህራን እየጠፉ ትምህርት የማናገኝበት ቀን ነበር። ይሁን እንጂ ያሉት መምህራን ጊዜያቸውን በመሰዋት ትምህርት እየሰጡን ክፍተቱን ለመሙላት ይጥሩ ነበር። አንዳንድ ለተማሪ ፍቅር የማይሰጡ መምህራንም ነበሩ። ተማሪ ሊያጠፋ ይችላል መምህር መቻል፣ መምከርና ትምህርቱን በአግባቡ መስጠት መቻል አለበት።  » ሠልጣኝ አራርሶ በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ የሚሰጡ ሥልጠናዎች ሰባ ከመቶ ተግባር ተኮር እንዲሆኑ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት የሚሰጠው ሥልጠና በኮሌጃቸው በአግባቡ እየተተገበረ መሆኑን ይናገራል። ሰላሳ በመቶ የሚሆነውን ሥልጠና በክፍል ከተማሩ በኋላ ቀሪውን በተግባር ይሰለጥናሉ። በእነርሱ የሥልጠና ዘርፍ የተሟሉ የተግባር ት

ሲኣን ከኣባላቱ እና ከደጋፊዎቹ ጋር ልመክር ነው

Image
በመጪው መጋቢት 20 ላይ በምካሄደው ህዝባዊ ጉባኤ፤ የሲዳማ ኣርነት ንቅናቄ ብሔራዊ የፖለቲካ ፓርቲ ከሆነው ከመድረክ ጋር ግንባር መፍጠር ያስፈለገበትን ምክንያት ለማብራራት እና ግንባሩን ወደፊት ለማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ከሰፊው የሲዳማ ህዝብ ጋር ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል። ሪፖርተራችን ጥቻ ወራና እንደዘጋበው ለኣንድ ቀን በሚውለው በዚህ ህዝባዊ ጉባኤ ላይ የሲዳማ ኣባቶች በባህሉ መሰረት መርቀው የሚከፍቱ ሲሆን፤ በሲዳማኣፎ ፤ በኣማርኛ እና በኦሮሚፋ ቋንቋዎች እንደየኣስፈላጊነቱ ለመጠቀም ፕሮግራም መያዙ ታውቋል። በተጨማሪም ጉባኤ በተለያዩ የመዝናኛ ዝግጅቶች ይታጀባል። ከዚህም ባሻገር በሃዋሳ በሌሎች የሲዳማ ከተሞች በሚገኙ ዋና ዋና መገናኛ ቦታዎች ላይ ስለ ጉባኤው ዓላማ እና ዝግጅት የሚያትቱ ፖስተሮችን እና ማስታወቂያዎች እንደምሰቀሉ ተገልጿል። በጉባኤው ላይ በድርጅቱ ኣከፋፈል መሰረት በሰባቱ የሲዳማ ክልል ዞኖች ውስጥ ከምገኙ 21 ወረዳዎች እና 502 ቀበሌያት የተጋበዙ የድርጅቱ ኣባላት እና ደጋፊዎች ብሎም ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች እንደምገኙ ይጠበቃል። በተጨማሪም ከሲዳማ ህዝብ ጋር በባህልና በሃይማኖት ከተሳሰሩት እና ተመሳሳይ የፖለቲካ ኣካሄድ ካለቸው ብሄሮች መካከል የኦሮሞ ብሄረሰብ ተወካዮች ተሳታፊ እንደምሆኑ ታውቋል። ባለፈው ሳምንት በመድረክ ኣዘጋጅነት በሻሾሚኔ ከተማ በተካሄደው ህዝባዊ ጉባኤ ላይ የሲዳማ ኣርነት ንቅናቄ ( ሲኣን ) በ 15 ኣባላቱ የተወከለ ሲሆን፤ ኣባለቱ በሲዳማ ባህላዊ ኣልባሳት ተሽቀርቅረው ወደ ጉባኤው ኣዳራሽ በገቡበት ወቅት የጉባኤው ተሳታፊዎች ከመቀመጫቸው በመነሳት በጭብጨባ ታላቅ ኣቀባበል ማድረጋቸው ይታወሳል። በወቅቱ የሲዳማ እና የኦሮሞ ሽማግሌዎች የተለያዩ ሰጦታዎች

የሲዳማ ኣርነት ንቅናቄ (ሲኣን) በሃዋሳ ከተማ ታላቅ ህዝባዊ ጉባኤ መጥራቱ ተሰማ

Image
ንቅናቄው በቅርቡ ከተቀላቀለው ብሔራዊ ድርጅት ከመድረክ ጋር በጋራ በመሆን በመጪው መጋቢት 20 ታላቅ ህዝባዊ ሰብሰባ በሃዋሳ ከተማ በሲዳማ ባህል ኣደራሽ ኣዘጋጅቷል። በተመሳሳይ ዜና ባለፈው ቅዳሜ በመድረክ ኣዘጋጅነት በተካሄደው ህዝባዊ ሰብሰባ ላይ የሲዳማ ኣርነት ንቅናቄ በ 15 ተወካዮች የተሳተፈ ሲሆን፤ ተወካዮቹ በሲዳማ የባህል ኣልባሳት ኣምረው ዘንጠው ወደ ጉባኤው ኣዳራሽ በገቡበት ወቅት ቤቱ በታላቅ ጭብጭባ ደማቅ ኣቀባበል እንዳደረገላቸው ሪፖርተራችን ጥቻ ወራና ከሃዋሳ ዘግቧል።

Africa Looks To Colombia For Tips On Sustainable Coffee

Image
Producers from Rwanda, Burundi and Ethiopia have visited the Colombian estates of producers to discover the social, environmental and aesthetic benefits of growing shade coffee. BOGOTA  — Which is better,  Colombian  or  African coffee ? Whatever your preference, both regions are major world producers and have begun to work together to produce coffee that offers much more than enticing flavors and aroma. This idea exchange began when producers in  Rwanda  and  Burundi  explored how they could focus on quality but also on environmental care and long-term sustainability. They wanted to generate additional revenues via tourism and improve the welfare of coffee workers at the same time.  “The two countries begin to identify these elements as important practices for sustainable landscape management, with numerous environmental and social benefits,” says Paola Agostini, the World Bank’s Africa Regional Coordinator. So it made sense that they wanted to visit South America, where

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ከኃላፊነታቸው ለቀቁ፤ በሲዳማ ቡና ገበያ ላይ ተጽኖ ይኖረው ይሁን?

Image
ዘመናዊ የግብይት ሥርዓት ለመዘርጋት ምሳሌ ይሆናል የተባለውን የኢትዮጵያ ምርት ገበያ በዋና ሥራ አስፈጻሚነት ሲመሩ የቆዩትን ዶ/ር እሌኒ ገብረ መድኅንን ተክተው ሲሠሩ የቆዩት አቶ አንተነህ አሰፋ ከኃላፊነታቸው ለቀቁ፡፡ ምንጮች እንደጠቆሙት አቶ አንተነህ ከኃላፊነት የለቀቁት አሜሪካ ሆነው ባመለከቱት የሥራ መልቀቂያ ደብዳቤ ሲሆን፣ የምርት ገበያው ቦርድ ጥያቄያቸውን ተቀብሎ አፅድቆታል፡፡  በቀድሞው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ አዲሱ ለገሰ ሊቀመንበርነት የሚመራው የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ቦርድ የሥራ መልቀቂያውን ተቀብሎ ውሳኔ የሰጠው፣ ሐሙስ መጋቢት 4 ቀን 2006 ዓ.ም. መሆኑን የተገኘው መረጃ ያስረዳል፡፡   አቶ አንተነህ ሥራቸውን ለመልቀቅ ውሳኔ ላይ ያደረሳቸው የጤና ችግር መሆኑን ምንጮች ጠቁመዋል፡፡ በልብ ሕመም ምክንያት በአገር ውስጥ በሕክምና ላይ እንደነበሩና አነስተኛ ቀዶ ጥገና ተደርጐላቸው እንደነበር ታውቋል፡፡ በዚህ ምክንያት ለከፍተኛ ሕክምና አሜሪካ የሄዱት አቶ አንተነህ፣ ሕክምናውን እዚያው በቅርብ እንዲከታተሉ በመወሰኑ ሥራቸውን ለመልቀቅ እንደተገደዱ እየተነገረ ነው፡፡ ወደ አሜሪካም ሲጓዙ ቤተሰቦቻቸውን ይዘው እንደሆነም ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ለሪፖርተር አስረድተዋል፡፡  በሥራ ገበታቸው ላይ ሳይገኙ ከሁለት ወራት በላይ የቆዩት አቶ አንተነህ፣ ይመለሳሉ ተብሎ በሚጠበቅበት ጊዜ የሥራ መልቀቂያ መላካቸው ያልተጠበቀ ነው ተብሏል፡፡  አቶ አንተነህ ዋና ሥራ አስፈጻሚ በመሆን ሙሉ የምርት ገበያውን ኃላፊነት ተረክበው መምራት ከመጀመራቸው ቀደም ብሎ፣ ከነሐሴ 24 ቀን 2004 ዓ.ም. እስከ መስከረም 20 ቀን 2005 ዓ.ም. ድረስ ዕጩ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ተብለው ከዶ/ር እሌኒ ጋር በጋራ ሲሠሩ እንደነበር ይታወሳል፡፡ መስከረም