Posts

በኣለማችን ላይ “ሲዳማ” የምትለውን ቃል በኢንተርኔት ላይ ሰርች የሚያደርጉ ሰዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱን የጎግል መረጃ ኣመለከተ።

Image
ጎግል በኣለም ደረጃ “ሲዳማ” በምል ቃል ስለ ሲዳማ ጎግል የምያደርጉ ሰዎች ቁጥር ካለፉት ኣስር ኣመታት ጀምሮ እያደገ መምጣቱን የገለጸ ሲሆን፤ በተለይ እንደ ፈረንጆቹ ዘመን ኣቆጣጠር በ 2013 ከፍተኛ ቁጥር ያለው የኢንተርኔት ተጠቃሚ ሲዳማን መፈለጉ ታውቋል። እንደጎግል መረጃ በተለይ እኣኣ ከ 2007 በፊት ሲዳማ ብዙም ጎግል የተደረገ ቃል ባይሆንም፤ በ 2008 ኣጋማሽ ላይ በርካታ ሰዎች “ሲዳማ”ን ጎግል ማድረጋቸው ተመልክቷል። ቀጥሎም በ 2009 መጀመረያ ላይ የሲዳማ ጎልጋዮች ቁጥር የወረደ ሲሆን በተመሳሳይ ኣመት መጨረሻ ላይ እንደገና ኣድጓል። ከ 2010 ጀምሮ የጎልጋዮች ቁጥር ኣንዴ ስያድግ ሌላ ግዜ ሲወርድ ቆይቶ በበላፈው ኣመት መጀመሪያ ላይ በታሪኩ ታይቶ በማይታወቅ መልኩ መጨመሩ ታውቋል። ነገር ግን ከ 2013 ኣጋማሽ ጀምሮ ይቁጥር በመውረድ ላይ ይገኛል። ጎግል እንዳመለከተው “ሲዳማ” የምትለውን ቃል የምጎለጉሉ ሰዎች ትራፊክ በኣብዛኛው የምፈጠረው ከሰሜን ኣሜሪካ ሲሆን፤ ኢትዮጵያ እና ሰሜን ኣውሮፓ ኣገራት እንድሁ የትራፊክ ምንጮች ናቸው። የሲዳማ ጎልጋዮች ቁጥር መጨመር እና መውረድ ከሲዳማ ዞን የፖለቲካ ሁኔታ ጋር የተያያዘ መሆኑን የወራንቻ ኢንፎርሜሽን ኔትዎርክ ትንተና ያመለከተ ሲሆን፤ ለዚህም ማሳያ በሲዳማ ዞን ውስጥ የፖለቲካ ትኩሳት የነበረባቸው ኣመታት ማለትም በ 2006 እና 2013 የተፈጠረውን ትራፊክ ማየት ይቻላል።

የሲዳማ ዘመን መለወጫ /ፍቼ/ በአል አከባበር

Image
ከይረጋዓለም ከተማ አስተዳደር ጋር በመተባበር  ፍቼ በዓል በሲዳማ ፎቶ ከሲዳማ ባ/ቱ/መ/ኮ/መምሪያ “ፍቼ” በሲዳማ ባህል ከትውልድ ትውልድ ሲተላለፍ የቆየ የዘመን መለወጫ በአል ነው፡፡ በአሉ ከሁለት ሳምንት ላላነሰ ጊዜ በድምቀት የሚከበር ሲሆን አከባበሩም ቅደም ተከተላዊ ሂደትና በደረጃ እየሰፋ የሚሄድ የጋራ የአከባበር አድምታ ያለው ነው፡፡ ስለሆነም ፍቼ በቤተሰብ ወይም በጎረቤት ደረጃ ተሰባስቦ በማክበር የሚያበቃ ሳይሆን ከዚህም በሰፋ መልኩ በባህላዊ አደባባይ /ጉዱማሌ/ በጋራ በድምቀት የማክበር ሂደትን ያካትታል፡፡ ለአከባበሩ እያንዳንዱ ቤተሰብ በቅድሚያ እንደ አቅሙ ቅድመ ዝግጅት ያደርጋል፡፡ ከዚሁ አንጻር የቤቱ እመቤት ለበአሉ ቅቤ ታጠራቅማለች ወተት በታጠነ ማለፊያ “ቁሹና” /የወተት እቃ/ ታከማቻለች የእንሰት ውጤት የሆነውን ቆጮ ለበአሉ በሚሆን መጠንና ጥራት ከወዲሁ ታሰናዳለች፡፡ አባወራው በፍቼ ማግስት /በጫምበላላ/ እለት ለከብቱ የሚያበላውን ቦሌ ያዘጋጃል፡፡ ልጃገረዶች ለበአሉ መዋቢያ ለእግሮቻቸውና ለእጆቻቸው ጣቶች ቀለበት፣ ለፀጉራቸው መስሪያ “ሄቆ” /የተለያዩ ቀለማት ያሉት የቱባ ክር/፣ ጨሌ፣ ለአንገታቸው ቡሪቻና ዶቃ የጌጥ አይነት ለጸጉራቸው ማሸሚያ ግንባራቸው ላይ የሚያስሩትን በእራፊ ጨርቅ ላይ ደርድረው የሚሰፉትን ኢልካ /አዝራር/ ወዘተ የመሳሰለውን ያስገዛሉ እግራቸውና እጃቸው ላይ የሚቀቡትን እንሶስላ ያዘጋጃሉ፡፡   ፍቼ/ Fichchaa / የሲዳማ ሸንጎ ፎቶ ከሲዳማ ባ/ቱ/መ/ኮ/መምሪያ የፍቼ ዕለተ በዕለተ ቃዋዶ በአሉ መከበር የሚጀምረው ከአመሻሽ ጀምሮ ነው፡፡ ለዚህም በቅቤ የራሰ “ቡሪሳሜ” ከቆጮ የተሰራ ባህላዊ ምግብ “በሻፌታ” /ከሸክላ በተሰራ ባህላዊ ገበታ/ ቀርቦ በወተት በጋራ የመመገብ ሥርዓት የሚካ

ጥቂት ስለ ሲዳማ ቡና የእግር ኳስ ቡድን

Image
PROFILE ሲዳማ ቡና  ሙሉ ስም ፡  ሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ  ምስረታ ፡  1999 ስታዲየም ፡   ይርጋለም ስታዲየም  ሀዋሳ ስታዲየም የክለቡ የወቅቱ አሰልጣኝ ፡  ታረቀኝ አሰፋ   ዳኜ ክለቡ ያገኛቸው ክብሮች ፡  የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሊግ ሻምፒዮን 2001 ሲዳማ ቡና በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ እየተሳተፈ ያለ ክለብ ነው፡፡ ክለቡ ከተመሰረተ ጥቂት አመታት ብቻ ቢቆጠሩም በብሔራዊ ሊግ ሻምፒዮን ሆኗል፡፡ በፕሚየርሊጉም ጥሩ ተፎካካሪ እየሆነ ይገኛል፡፡ ምስረታ  ሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ የተመሰረተው በ 1999 ዓ/ም ነበር በደቡብ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ላይ ሲዳማ ዞንን በመወከል ሥስት ክለቦች ይሳተፋሉ ከእነዚህ ውስጥ አንዱ ዳራ ከነማ ነበር፡፡ ዳራ በውድድሩ ለፍፃሜ በመድረስ ውጤታማ ይሆናል፡፡ ይህም ክልሉን በመወከል ሀዋሳ ላይ ወደተካሄደው የኢትዮጵያ የክልል ክለቦች ሻምፒዮና ከተሳተፉ አራት ቡድኖች አንዱ ለመሆን አበቃው፡፡ በዚህ ውድድር ቀዳሚዎቹን አራት ደረጃዎች የሚይዙ ቡድኖች ወደ ብሔራዊ ሊግ ሲያልፉ ዳራም ሦስተኛ ደረጃን አግኝቶ ስለነበር ብሔራዊ ሊጉን ተቀላቀለ፡፡ እናም ዳራ ከተማን ብቻ ይወክል የነበረው ክለብ መላውን የሲዳማ ዞንን እንዲወከል በማሰብ ሲዳማ የሚለውን ስያሜ አገኘ፡፡ ሲዳማ ቡና በብሔራዊ ሊግ ሲዳማ ቡና ሁለት አመት በብሔራዊ ሊግ አሳልፏል፡፡ በመጀመሪያው አመት ቆይታው በ 2000 አራተኛ ደረጃን ይዞ ነው ያጠናቀቀው፡፡ በሁለተኛው አመት 2001 ውድድሩ በሁለት ምድብ ተከፍሎ ሲካሔድ በምድብ ሁለት የነበረው ሲዳማ በመጨረሻው ጨዋታ ከአየር ሀይል ጋር ያለ ግብ በመለያየት ከምድቡ ከሜታ አቦ ቢራ ቀጥሎ ሁለተኛ ደረጃን አግኝቷል፡፡ በዚህ ጨዋታ ቢሸነፍ ኖሮ ይህን ደረጃ አ

በሀዋሳ በተለያዩ ዘርፎች ዉጤታማ የሆኑ ሴቶች ተሸለሙ

Image
ሀዋሳ መጋቢት 5/2006 በሃዋሳ ከተማ የላቀ እንቅስቃሴ ላበረከቱ ሴቶችና በትምህርታቸው ጥሩ ውጤት ላስመዘገቡ ሴት ተማሪዎች የማበረታቻ ሽልማት ተሰጠ፡፡ በኢትዮጵያ ለ38ኛ ጊዜ የተከበረውን  የሴቶች ቀን ምክንያት በማድረግ በተደረገው ሽልማት በሁሉም የትምህርት ደረጃ በትምህርታቸው የላቀ ውጤት ላመጡ 31 ሴት ተማሪዎች ለትምህርታቸው አጋዥ የሆኑ መጽሓፍት ተበርክቶላቸዋል። በሃዋሳ ከተማ በሚገኙ ትምህርት ቤቶች በመጀመሪያው መንፈቀ ዓመት ለሴት ተማሪዎች ልዩ የትምህርት ድጋፍ  ያደረጉ  ሞዴል ሴት መምህራን በከተማው ሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች  ጉዳይ ጽሕፈት ቤት የተዘጋጀላቸውን የምስክር ወረቀትና የገንዘብ ሽልማት ተቀብለዋል። በከተማው በተለያዩ የልማት ቡድን በመደራጀት ውጤታማ የሆኑ 16 የልማት ቡድኖችም የተዘጋጀላቸውን ሽልማት ተረክበዋል፡፡ በቅርቡ በተጀመረው የከተማ ጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም በስምንቱም ክፍለ ከተሞች አበረታች ውጤት ያስመዘገቡ ስምንት ጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎችም ተሸላሚዎች ሆነዋል፡፡ ከተሸላሚ ተማሪዎች መካከል ተማሪ ዝናሽ ዘንባባና ተማሪ አብጊያ ብርሃኑ በሰጡት አስተያየት ሴቶች ባለፉት ስርዓት ከነበረው ጭቆናና አድሎአዊ አሰራር ተላቀው በልማትና በመልካም አስተዳደር እኩል ተጠቃሚነታቸው መረጋገጡ እጅግ ያኮራናል ብለዋል፡፡ የሃዋሳ ከተማ አስተዳደር የሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች ጉዳይ  ጉዳይ መምሪያ  ኃላፊ ወይዘሮ ገነት ገረመው  እንደተናገሩት በከተማው የሴቶችን ኢኮኖሚያዊ  አቅም ለማሻሻል የብድር አገልግሎት ለመስጠት ከፍተኛ ጥረት በመደረግ ላይ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በርካታ ሴቶች በማህበር ተደራጅተውና ሃብት አፍርተው ወደ ባለሃብትነት መሸጋገራቸውንና ለብዙዎች የስራ እድል መፍጠራቸውንም ተናግረዋል፡፡ ምንጭ፦ኢዜኣ

በሃዋሳ ከተማ ኣስተዳደር ስር በተካተቱ የገጠር ቀበሌያት ውስጥ በሚገኙ ትምህርት ቤቶች በሲዳማኣፎ ትምህርት እየተሰጠነውን?

Image
በሃዋሳ ከተማ ኣስተዳደር ስር በተጠቃለሉት የቀድሞ የሃዋሳ ዙሪያ ወረዳ የገጠር ትምህርት ቤቶች ውስጥ በሲዳማኣፎ በምሰጠው የትምህርት ዙሪያ ሪፖርተራችን ጥቻ ወራና የምቀጥለውን ዘገባ ልኮልናል፦ Umihunni, Hawaasi katami gashshooti giddora qolli gaxarete qawallara/ kiiro 12 qawale/ noo rosi minnara Sidaamu Afoo seekine rosiinsanni hee'noonni. Urrinse nafa di egeninoonni. Hatti gaxarete qawalla heedhanno kifle katami Tula kifle ketema yinanni. Wolootu kifle ketemarrano, Sidaamu ooso batidhdhe noowa Sidaamu oosora calla/partially/ 1 - 4 geeshsha Sidaamu afiinni baalanka roso rosiinsanni. 5-8 kifle geeshsha noo rosi minnara kayinni Sidaamu Afoo mitte subjecte assine uyiinanni baalunkura. 2005 M.D kayise 10 kifleranna 12 kiflera uyinanni fonqolira mitte subject ikke shiqeenna rosaano fonqolante sainno. Xaa isinni roore universitete deerinni rosiisa hananfoonni daafira konni ka'a kaajanno yine hendanni.