Posts

የፕሬዚዳንቱን ይቅርታ የማድረግ ሥልጣን የሚቀንስ አዋጅ ቀረበ

ሪፖርተር ጋዜጣ 12 March 2014 -   መጋቢት 3, 2006 ዓ.ም. - የፓርላማ አባላት ከሕገ መንግሥቱ ጋር እንዲጣጣም ጠይቀዋል የአገሪቱ ፕሬዚዳንትን ለሕግ ታራሚዎች ይቅርታ የማድረግ ሥልጣን የሚቀንስ አዲስ ‹‹የይቅርታ አሰጣጥና አፈጻጸም ሥነ ሥርዓት›› ረቂቅ አዋጅ ለፓርላማው ቀረበ፡፡ አንዳንድ የፓርላማው አባላት ረቂቅ አዋጁ ከሕገ መንግሥቱ ጋር ይቃረናል በማለት እንዲስተካከል ጠይቀዋል፡፡ የፕሬዚዳንቱን ሥልጣንና ተግባር የሚዘረዝረው የሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 71 (7) ‹‹ፕሬዚዳንቱ በሕግ መሠረት ይቅርታ ያደርጋል›› በማለት ይደነግጋል፡፡ በ1996 ዓ.ም. የወጣው በአሁኑ ወቅት በሥራ ላይ የሚገኘው የይቅርታ ሥነ ሥርዓት አዋጅም በሕገ መንግሥቱ ለፕሬዚዳንቱ የተሰጠውን ይቅርታ የማድረግ ሥልጣን ያጠናክረዋል፡፡ በዚህ አዋጅ መሠረት ፕሬዚዳንቱ የይቅርታ ቦርድ የውሳኔ ሐሳብን መሠረት በማድረግ፣ እንዲሁም በውሳኔ ሐሳቡ ላይ የቀረቡ መረጃዎችን ፕሬዚዳንቱ በራሱ መመዘን ለሕግ ታራሚዎች ይቅርታ እንዲያደርግ ወይም እንዲከለክል ሥልጣን ይሰጠዋል፡፡ የፕሬዚዳንቱን ይቅርታ ያገኘ ታራሚ በሕጉ መሠረት የተጣለበትን ጥሶ የተገኘ ከሆነ በይቅርታ ቦርዱ የውሳኔ ሐሳብ አቅራቢነት ፕሬዚዳንቱ የሰጠውን ይቅርታ የማንሳት መብት በዚሁ በሥራ ላይ ባለው አዋጅ ለፕሬዚዳንቱ ተሰጥቷል፡፡  ባለፈው ማክሰኞ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀረበው ረቂቅ አዋጅ ግን፣ ‹‹ፕሬዚዳንቱ የይቅርታ ቦርድን የውሳኔ ሐሳብ መሠረት በማድረግ ይቅርታ ይሰጣል፤›› ሲል በረቂቁ ክፍል ሁለት አንቀጽ 4 (1) ላይ አስቀምጧል፡፡ በማከልም ቦርዱ ለፕሬዚዳንቱ የሚልከው የውሳኔ ሐሳብ ይቅርታ የተወሰነላቸውን ታራሚዎች በመተለከተ ብቻ ነው፡፡  በቦርዱ ውሳኔ አቅራቢነት

ሳቅ እንደ አማራጭ ሕክምና?

ኮከቤ የማነ የፊኛ ካንሰር እንዳለበት ያወቀው ከአሥር ዓመታት በፊት ነበር፡፡ ህመሙን ካወቀ በኋላ ከሌሎች የካንሰር ሕመምተኞች ሰምቶ ሕመሜን ቢያስታግስልኝ በማለት ወደ ሳቅ ትምህርት ቤት ይቀላቀላል፡፡ በወቅቱ ሞትን እስከመመኘት ድረስ በበሽታ ይሰቃይ እንደነበር ይናገራል፡፡ ኮከቤ የኬሞቴራፒ ሕክምና ይፈጥርበት የነበረውን ሕመም ለመቋቋምና ስቃዩን ለማስታገስ ከረዱት ዋነኛው ሳቅ እንደሆነ ይገልጻል፡፡   የካንሰር ሕክምናን አብረውት ይከታተሉ ከነበሩት መካከል ብዙዎች ሕይወታቸው ሲያልፍ ተመልክቷል፡፡ በአካል የሚያውቃቸው ሲያልፉ ከማየቱም በላይ ሕይወቱ አደጋ ላይ በወደቀበት ወቅት ራሱን መሳቅ አስተምሯል፡፡ ኮከቤ ወደኋላ በትዝታ እየቆዘመ ‹‹ዕድለኛ ነኝ›› ይላል፡፡  ዛሬ የ45 ዓመት ጐልማሳ ነው፤ ባለትዳርና የልጆች አባትም ነው፡፡ በቤተ መንግሥት ውስጥ የሜዳ ቴኒስ አጫዋች የሆነው ኮከቤ ‹‹የእኔ ደስተኛ መሆን ለቤተሰቦቼም ተርፏል፤ ማታ ቤት እስክገባ ይቸኩላሉ፡፡ ምንም ችግር ቢኖር በሳቅ እናሳልፈዋለን፤›› ይላል፡፡ ደስተኛ መሆኑን የሚገልጸው ኮከቤ ልጆቹ እሱን በማየት ሲስቁ ማየት ያስደስተዋል፡፡  በዓለም የድንቅ ነገሮች መዝገብ ላይ ለሦስት ሰዓት ከስድስት ደቂቃ ያለማቋረጥ በመሳቅ ሪከርድ የጨበጠና ‹‹የዓለም የሳቅ ንጉሥ›› የሚል መጠሪያ ያገኘው በላቸው ግርማ፣ ኮከቤን ለመሰሉና ሌሎች የሳቅ ትምህርት ቤት ካቋቋመ ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡ በእነዚህ ዓመታት ወደ ትምህርት በመሔድ ስለ ሳቅ፣ አሳሳቅንና በሌሎች ተያያዥ ትምህርቶች ለአንድ ወር ሠልጥነው የወጡ ተማሪዎች አሉ፡፡ በአፍሪካ ባሉ አገሮች ጅማሮዎች ቢኖሩም በኢትዮጵያ የሚገኘው ትምህርት ቤት የቆየና ግንባር ቀደም እንደሆነ የተለያዩ ዘገባዎች ያመለክታሉ፡፡  በላቸው ስለሳቅ ትምህርት ቤት ሲና

Ethiopia: Ribbon Cutting Brings Addis Abeba-Nairobi Highway a Step Closer

The 100km long Yabelo-Mega road - part of the 1,000km Mombasa-Nairobi-Addis Abeba Road Corridor - will be opened for traffic on Sunday, March 9, 2014 in the presence of Worqineh Gebeyehu, minister of Transport. The inauguration, which will take place in Yabelo town - 564km from Addis Abeba in Borena Zone of the Oromia Region - will also be attended by officials from the Ethiopian Roads Authority (ERA). The African Development Bank (AfDB) has extended a 770 billion Br loan to Ethiopia for the construction of the Yabelo-Mega section of the project. The Mombasa-Nairobi-Addis Abeba Road Corridor is an important part of the Trans-African Highway, from Cairo to Cape Town. In Kenya and Ethiopia, the road is a link from Addis Ababa to Nairobi. The Kenyan section of the road between Isiolo and Moyale is about 525km and was constructed as a gravel road in 1974. On the Ethiopian Side of the border, the road is entirely bitumen-paved from Moyale to Addis Abeba. However, the section of th

Is Egypt Securing Diplomatic Success over Ethiopia?

Image
The Blue Nile accounts for 85 percent of the Nile's water flow. It joins the White Nile, whose headwaters lie in the East African highlands of Burundi. Ethiopians consider the Grand Ethiopian Renaissance Dam (GERD) and the other dams the government of Ethiopia plans to build a symbol of national pride as they will produce electricity that will transform the economic prospects not only for their country but for much of seriously under-developed East Africa. In talks last January between Egypt, Ethiopia and Sudan, negotiations hit a dead-end, with MENA reporting that Ethiopia refused to discuss the terms of "confidence-building measures," which Egyptian officials say must be changed in order to avoid reduction of Egypt's Nile river water share. Egypt, with its 84 million people totally dependent on the Nile for water, cites British colonial agreements in 1929 and 1959 that guarantee it the lion's share of the water and a veto over upstream dam construct

የሃዋሳ ከተማ ኣስተዳደር በትምህርት ጥራት ላይ እየሰራሁ ነኝ ኣለ

Image
Ethio-American School Hawassa-Yirgalem በሃዋሳ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ በተደረገው ጥረት ለውጥ እየመጣ ነው ሀዋሳ መጋቢት 1/2006 በሃዋሳ ከተማ አስተዳደር የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅና መጠነ ማቋረጥ ለመቀነስ  በተደረገው ጥረት  አበረታች ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የከተማው አስተዳደር ትምህርት መምሪያ ገለጸ፡፡ በመምሪያው የትምህርት ጥራት ማረጋገጫ ዋና የስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ገዛኸኝ ደገፉ እንደገለጹት የትምህርት ጥራት ፓኬጁን ተግባራዊ ለማድረግ ከወላጆች ቦርድ፣ ከመምህራንና ተማሪዎች ጋር ተቀናጅተው እየሰሩ ናቸው፡፡ በዚህም በርካታ ትምህርት ቤቶች የትምህርት ጥራት ማሻሻያ ፕሮግራሞች በመጀመራቸው የተማሪዎች ውጤት በየአመቱ ከፍተኛ ለውጥ እያመጣ ነው፡፡ ባለፈው አመት የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ከወሰዱ 8ሺህ 643 ተማሪዎች መካከል 72 በመቶ ወደ ቀጠዩ ደረጃ መሸጋገራቸውንና ይህም ከቀዳሚው አመት ጋር ሲነፃፀር 8 በመቶ ብልጫ አለው፡፡ በተመሳሳይ የ10ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከተቀበሉ 5ሺህ 986 ተማሪዎች ከ83 በመቶ በላይ የማለፊያ ነጥብ ማምጣታቸውን ጠቁመው  በየአመቱም እድገት ማሳየቱን አስተባባሪው ተናግረዋል፡፡ ትምህርታቸውን ጀምረው የሚያቋርጡ ተማሪዎች ቁጥር ከአምስት በመቶ በታች ዝቅ ማድረግ ተችሏል፡፡ በተለይ የወላጆች ቦርድ፣ መምህራንና የትምህርት ቤት ኮሚቴዎች በየወቅቱ በትምህርት ጥራት ፓኬጅ ዙሪያና በሚከሰቱ ችግሮች  እንዲሁም መፍትሄዎቻቸው ላይ በመወያየት ተቀናጅተው እየሰሩ መሆናቸውን ተመልክቷል፡፡ እንዲሁም ወላጆች ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት እንዲልኩ ባለድርሻ አካላት ባደረጉት የጋራ ጥረትም ከ115 ሺህ በላይ የሚሆኑ ተማሪዎች ትምህርት ቤት እንዲገቡ ማድረግ ተችሏል፡፡