Posts

የቡና ኤክስፖርት ለሙስናና ብልሹ አሰራር ተጋልጧል

Image
የካቲት ፯ (ሰባት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ቡናን ኤክስፖርት ከማድረግ ጋር በተያያዘ በክትትልና ቁጥጥር፣ በመረጃ አያያዝ፣ ያለብሔራዊ ባንክ ፈቃድ ቡናን ወደውጭ ኤክስፖርት ከማድረግ እና በሁሉም አካባቢ የቡና ድርጅቶችን መጋዘኖች ክምችት ቆጠራ በወቅቱ ባለማድረግ ላይ ክፍተቶች እንደሚስተዋሉ የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ያጠናው አንድ ጥናት አመለከተ፡፡ ጥናቱ  ኤክስፖርት በማያደርጉ ድርጅቶች ላይ እርምጃ ያለመውሰድ፣ በንግድ ፈቃድ ላይ የተጠናከረ ቁጥጥር ያለማድረግ እና በሕገወጥ የቡና ምርት ዝውውርና ግብይት ላይ የሚመለከታቸው አካላት ተቀናጅተው ያለመስራት በዘርፉ የሚታዩ ችግሮች መሆናቸውን ማመላከቱን ኮምሽኑ በድረገጹ ላይ ባሰፈረው ዜና ገልጿል፡፡ ኢትዮጵያ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ከምታገኝባቸው የግብርና ምርቶች መካከል በቀዳሚነት የሚጠቀሰው የቡና ኤክስፖርት ሒደት ለሙስናና ብልሹ አሠራር ያለውን ተጋላጭነት አስመልክቶ በኮሚሽኑ የተካሔደው ጥናት ይፋ የሆነው ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት በተገኙበት ሰሞኑን በግዮን ሆቴል ጥናቱን ለማዳበር በተከናወነ የምክክር ስብሰባ ላይ ነው፡፡ የውይይት መድረኩ የተዘጋጀበት ዓላማ በዘርፉ ስለሚስተዋሉ የአሠራር ጉድለቶች ለሚመለከታቸው ክፍሎች ግልጽ ግንዛቤ ለማስያዝና ችግሮቹን በመቅረፍ ረገድ የተሻለ አሠራር በማመላከት የመፍትሔው አካል ሆነው የድርሻቸውን እንዲወጡ ለማስቻል እንዲሁም በክፍተቶቹ ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ በመያዝ ለመፍትሔው በጋራ ለመንቀሳቀስ ነው ተብሎአል፡፡ አገሪቱ ከቡና ኤክስፖርት የምታገኘው ገቢ በተለይ ባለፉት ሶስት ዓመታት ማሽቆልቆሉ የሚታወቅ ሲሆን ችግሩ ከዚህ ዓይነቱ ሙስናና ብልሹ አሰራር ጋር በቀጥታ ይያያዝ ፣አይያዝ የተገለጸ ነገር የለም፡፡ http://ethsat.co

Over 30 cooperatives are engaged in bamboo farming in Sidama

Image
African Bamboo Plc. Awarded US$ 1.75 million in USAID Grant USAID awarded a total grant of US$ 1.75 million to African Bamboo Plc, Fortune reported. One million dollars of the grant is for developing and testing a heating process to make industrial and commercial quality bamboo using biofuels from organic waste. The second grant, amounting to US$ 750,000 is said to help the Company prepare feasibility studies and market analyses to attract investment capital and to meet requirements for exports to the United States and the European Union, according to Fortune. African bamboo is among 475 organisations that applied for the USAID grant, which supports innovative projects integrating clean energy technology into the agriculture sectors of developing countries to improve production. African Bamboo is currently installing machinery at its bamboo production facility. The company is planning to produce bamboo panels for outdoor decking, construction and pre-fabricated bamboo house

የሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ የሲዳማን ቋንቋ'' ሲዳሙ ኣፎ'' ለማሳደገ የሚያደርገው ጥረት የሚበረታታ ነው

Image
የሲዳማ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም የሆነው የሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ በሲዳማ ባህል እና ቋንቋ ላይ የተለያዩ ጥናቶችን ከሚያደርጉ የኣገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎች መካከል ግንባር ቀደም ሲሆን፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሲዳማ ቋንቋ የትምህርት ክፍል ከፍቶ በማስተማር ላይ ነው። ሪፖርተራችን ጥቻ ወራና የዩኒቨርሲቲውን የሲዳማ ቋንቋ ዲፓርትመንት የስራ እንቅስቃሴ ቃኝቶ የላከልን ኣጭር ዘጋባ እንደሚያመለክተው፤ ዩኒቨርሲቲው የሲዳማን ቋንቋ ለማሳደግ የሚያደርገው ጥረት የምደነቅ ነው ነው። ሙሉ ዘጋባውን እንደምከተለው ኣቅርበነዋል፦ Hawaasi universite mitte yanna Debuubi university yinanni su'ma afidhdhe shiima diro keeshshitu gedensaanni Sidaamu daga kaajado xa'monni xa noo su'mira/ Hawassa university/ soorinoonni. Hakko barrinni kayise Hawaasi universite giddo sidaamu danchate yinanni millimillo assanni leellanno. Sidaanchu beetti/tto unversitete Gashshatenni kayise/Top position/ e''la mine feyaate geeshsha noo position duuchchu manni afirino. Lowo geeshsha danchaho yaa nafa hoongiro albinni woyyate yinanni deerinni Hawaasi unversite giddo sidaamu fooli roore gawwu yaanno. Rosu islanchimma lainohunni, Rosu islanchimma ba'a xaphoomu Tophiyu rosu poolise la

ሰበር ዜና : የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላንን የጠለፈው ረዳት አብራሪ በቁጥጥር ሥር ዋለ

Image
ሰኞ ማለዳ (የካቲት 10) ከአዲስ አበባ ወደ ሮም ሲያመራ የነበረውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ጠልፎ ጄኔቭ እንዲያርፍ ያስገደደው የአውሮፕላኑ ረዳት አብራሪ በጄኔቭ ፖሊስ በቁጥጥር ሥር ዋለ፡፡ የበረራ ቁጥር ET 702 አውሮፕላን የጠለፈው ረዳት አብራሪ በስም ባይጠቀስም ተገዶ ባረፈው አውሮፕላን ውስጥ የሚገኙት ተሳፋሪዎችም ሆኑ የአውሮፕላኑ ሠራተኞች በመልካም ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በድረ ገጹ አስታውቋል፡፡ ሮይተርስ ቀደም ብሎ ያነጋገራቸው የኢትዮጵያ መንግሥት ቃል አቀባይ ሬድዋን ሁሴን አውሮፕላኑ በሱዳን መዲና ካርቱም በኩል ማለፉንና ምናልባትም ጠላፊው ወይም ጠላፊዎቹ ከዚያው ሳይሳፈሩ እንዳልቀረ ተናግረው ነበር፡፡ መጨረሻ ላይ በተገኘው መረጃ ጠላፊው ረዳት አብራሪው መሆኑ ተረጋግጧል፡፡

የመንግሥት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ቁንጥጫ በርትቷል

Image
ፎቶ ሪፖርተር ጋዜጣ የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱን ግቦች መሠረት በማድረግ የተጀመሩ በርካታ የመሠረተ ልማት ግንባታዎች በመካሄድ ላይ ናቸው፡፡ እነዚህ ፈርጀ ብዙ ግንባታዎች በሚካሄዱበት አገር ውስጥ ለዓመታት አስቸጋሪ የነበሩ ኋላ ቀር የአገልግሎት ዘርፎች የሚፈጥሩትን ችግር እያየን ነው፡፡ ከኋላ ቀር አሠራርና አኗኗር ለመውጣት የሚደረገውን ጥረት መሰናክል ሲሆኑበትም ይታያል፡፡ እነዚህን መሰናክሎች እንዲህ ማየት የግድ ይላል፡፡  1.የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት መቆራረጥ  ምንም እንኳን በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ ማጠቃለያ ላይ የአገሪቱ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት አቅም አሥር ሺሕ ሜጋ ዋት ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል ቢባልም፣ በአገሪቱ ውስጥ ካሉ የተለያዩ የኃይል ማመንጫዎች የሚገኘውን ከሁለት ሺሕ ሜጋ ዋት በላይ ኃይል በቅጡ ማሰራጨት አልተቻለም፡፡ ለትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ መሳካት ጉልህ ሚና ይኖራቸዋል ተብለው የሚታሰቡ ትላልቅና መካከለኛ ኢንዱስትሪዎች በኃይል መቆራረጥና እጥረት ምክንያት ማምረት እየተቸገሩ ናቸው፡፡  ከፍተኛ ኢቨስትመንት የፈሰሰባቸው የተለያዩ የንግድ፣ የማምረቻና የአገልግሎት ተቋማት በኃይል መቋረጥ ምክንያት ለኪሳራ እየተዳረጉ ናቸው፡፡ የባንክ ብድር መመለስ እስኪያቅታቸው ድረስ ምርት እየተስተጓጐለባቸው ነው፡፡ የተመረተውን ምርት መሸጥ አልተቻለም፡፡ ሆቴሎች ለጄኔሬተርና መሰል የኃይል አማራጮች ለከፍተኛ ወጪ እየተዳረጉ ናቸው፡፡ በኢንቨስትመንት አካባቢ ከፍተኛ ጉዳት እያጋጠመ ነው፡፡ የኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጥ በቢሮዎች፣ በመኖሪያ ቤቶችና በመሳሰሉት ከግለሰብ እስከ አገር አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ዋጋ እያስከፈለ ነው፡፡ ሕፃናትን መመገብና መንከባከብ የማይቻልበት ደረጃ እየተደረሰ ነው፡፡ በቤተሰብ ደረጃ እንኳ ቢታይ