Posts

Patient satisfaction with outpatient health services in Hawassa University Teaching Hospital, Southern Ethiopia

Image
ለተጨማሪ ንባብ ፦ Full Length Research Paper

Fish Market at Awassa Lake

Image
ተጨማሪ  ፎቶዎችን በዚህ ሊንክ ይመልከቱ፦  Fish Market at Awassa Lake

AWASSA KENEMA VS. KEDUS GIORGIS

Image

የይርጋለም ከተማ የንጽህ ውሃ ግንባታ ፕሮጀክት መቼ ይሁን የምጠናቀቀው?

Image
ኣንድ ሚሊዮን ለምጠጉ የ ይርጋለም ከተማ እና ለኣከባቢዋ የገጠር ቀበሌያት ነዋሪዎች ኣገልግሎት ይሰጣል ተብሎ፤ ከ 50 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በመገንባት ላይ የሚገኘው የውሃ ፕሮጀክት በተለያዩ ምክንያቶች ከሚጠበቀው በላይ ተጓቷል። ይህ የውሃ ፕሮጀክት 60  ሊትር በሰከንድ ወይም  5  ሺ  142  ሜትር ኪዩብ በቀን የመስጠት አቅም ያለው እና እስከ  2012 ዓ . ም ድረስ ለ 898  ሺ ያህል የከተማዋ ሕዝብ አገልግሎት ለመሥጠት ያስችላል መባሉ ይታወሳል ። እንደ ኣዲስዘመን ጋዜጣ ዘገባ ከሆነ፤ የውሃ ፕሮጀክት በአንድ ዓመት ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ ቢጠበቅም ከቧንቧ መገጣጠሚያ አካል  ( ፊቲንግ )  አቅርቦት ችግር ጋር ተያይዞ መጓተቱን የሥራ ኃላፊዎች ይናገራሉ፡፡ አምስት ጥልቅ የውሃ ጉድጓዶች ካሉት ፕሮጀክት መካከል ሁለቱ በጄነሬተር ሥራ ቢያስጀምሩም ሌሎቹ ግን ውሃ መስጠት አልቻሉም። ለዚህ ምክንያቱ ደግሞ ውሃ መግፋት የሚያስችል በቂ የኃይል አቅርቦት ባለመኖሩ ምክንያት ነው።   « ትራንስፎርመር ለማስተከል ክፍያ የፈፀምነው በ 2003  ዓ . ም ቢሆንም እስካሁን ከአንዱ በቀር ምላሽ አልተሰጠንም »  የሚሉት የፕሮጀክቱ ኃላፊዎች፤ በዚህ ምክንያት ህብረተሰቡ በቂ ውሃ ማግኘት አለመቻሉን ይገልጻሉ፡፡ ከዚህ በተጨማሪም አንድ ትራንስፎርመር ቢተከልም በሶስት ቀን ውስጥ እንደፈነዳና አገልግሎት እንዳቆመ ይናገራሉ፡፡ የፈነዳውን ለማስለወጥ ያደረጉት ጥረት ምላሽ አለማግኘቱን ጨምረው ገልጸዋል፡፡ እንደጋዜጣው ዘገባ፤ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደቡብ ክልል ቅርንጫፍ የገበያና ሽያጭ ኃላፊ አቶ ታደሰ መርጋ፤ ከፍላጎት መጨመር ጋር ተያይዞ ወረፋ መኖሩን ገልፀው፤  « ፈነዳ »  ስለተባለው ትራንስፎርመር ግን የሚያውቁ

በሃርቤ ጎና ወረዳ በአንድ ሚሊዮን ሄክታር መሬት ላይ ቀርከሃ ልለማ ነው

Image
ፋብሪካው በሲዳማ ዞን በአንድ ሚሊዮን ሄክታር መሬት ላይ  ቀርከሃ ለማልማት ዝግጅት እያደረገ ነው በኢትዮጵያዊ ባለሀብትና በአሜሪካ የልማት ድርጅት ትብብር የተቋቋመው  « አፍሪካን ባንቡ »  የተሰኘው የቀርከሃ ፋብሪካ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የቀርከሃ ጣውላ በማምረት ወደ ጀርመንና የተለያዩ የዓለም ሀገራት ለመላክ ማቀዱን አስታወቀ፡፡ የአፍሪካ ባምቡ ፋብሪካ ስራ አስኪያጅ አቶ ካሊድ ዱሪ የፋብሪካውን በይፋ ስራ መጀመር አሰመልክቶ ከትናንት በስቲያ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንዳመለከቱት፤ በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል ሲዳማ ዞን አርቤጎና ወረዳ ውስጥ በ 250  ሚሊዮን ብር የተገነባው ይኸው የቀርከሃ ፋብሪካ በሙሉ አቅሙ ማምረት ሲጀምር በየአመቱ  140  ሚሊዮን ብር የሚጠጋ ገቢ ለማስገባት አቅዷል፡፡ በአሁኑ ወቅት ከምርቱ  52  በመቶውን ወደ ጀርመን ለመላክ ስምምነት ፈጽሟል፡፡ « በሀገሪቱ የደን ሽፋን ካለፉት  40  አመታት ወዲህ እየተመናመነ በመምጣቱ የእንጨት ጥሬ እቃ እጥረት በከፍተኛ ደረጃ አጋጥሟል »  ያሉት ስራ አስኪያጁ፣ በየአራት ዓመቱ ራሱን በሚተካው ቀርከሃ ይህን የጥሬ ዕቃ አቅርቦቱን በመሸፈን ከቀርከሃ ጣውላ እንደሚመረት ነው ያስታወቁት። ከሀገሪቱ የደን ሽፋን ከ 50 በመቶ በላይ የሚሆነው ቀርከሃ መሆኑንም አስታውቀዋል። እንደ ስራ አስኪያጁ ገለጻ፤ የፋብሪካው ዋነኛ ጥሬ ዕቃ የሆነውን ቀርከሃ በሲዳማ ዞን አርቤ ጎና ወረዳ በአንድ ሚሊዮን ሄክታር መሬት ላይ ለማልማት ዝግጅት እየተደረገ ነው። በአሁኑ ወቅትም 50  ሺ ችግኞችን በማፍላት ለአርሶ አደሮች እየተከፋፈለ ይገኛል። በየአመቱም አርሶ አደሮቹ የሚያመረቱትን ቀርከሃ ከ 30  ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ እየገዛ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያደርጋል፡፡አርሶ አደሮ