Posts

የሲዳማ ኣርነት ንቅናቄ በወቅታዊ የፖለቲካ ኣካሄዱ ላይ የሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ

Image
መግቢያ የሲዳማ ህዝብ የትግል ታሪክ እንደሚያሳየው የሲዳማ ህዝብ እንደማንኛውም ጭቁን ህዝቦች ለነፃነትና ዴሞክራሲ መስፈን ያላሰለሰ ጥረት አድርጓል፡፡ አሁን ለሚታየውም አንፃራዊ መረጋጋት አያለ የህዝብ ልጆች ደማቸውን በማፍሰስና አጥንታቸውን በመከስከስ አኩሪ የታሪክ አሻራ አስቀምጠው አልፈዋል፡፡ ምንም እንኳን የተከፈለው መስዋዕትነት ከፍተኛ ቢሆንም የሲዳማ ህዝብ እስከ አሁን ድረስ የተሰዋለትን ነፃነት ፣ ሰላምና ዴሞክራሲ ብሎም አስተዳደራዊ ነፃነት እንደተነጠቀ ዘመናትን አስቆጠረዋል፡፡ በዚህ ምክንያት ከትውልድ ወደ ትውልድ የተላላፈው የነፃነት ትግልም እስከ አሁን ድረስ የቀድሞውን ቁልፍ የህዝብ ጥያቄዎችን በማንገብ የሚነሳውን የአሁኑን ትውልድ ደም እያፈሰሰ፣ የሕይወት ዋጋም እያስከፈለ ከጊዜ ወደ ጊዜ ተጠናክሮ ቀጥለዋል፡፡ ስለዚህ የሚያባሪር ካልቆሜ የሚሸሽ ስለማይቆምም (shorrannohu uurrikkinni xooqannohu diuurranno) እንደምባለው የህዝብን ታሪካዊ አደራ ከዳር ለማድረስና ሰላማዊ ትግል ለማቀጣጠል በየደረጃው የሚገኙ የሲአን አመራርና መላው የሲዳማ ህዝብ ብሎም የትግሉ ደጋፊ የሆኑ የሌላ ብሔር አባላት ከምን ጊዜውም በላይ መጠናከር ወሳኝ ጉዳይ ከመሆኑም ባሻገር የሲአን ከፍተኛ አመራርም የድርጅቱን አላማ አንግቦ ይበልጥ ወደ ህዝብ መድረስ አስፈላጊ ብቻ ሳይሆን አንገብጋቢ ወቅት ላይ እንገኛለን፡፡ ክፍል አንድ የትግል ማጠናከሪያ አንኳር ዘዴዎች፡ 1. የውስጥ አደረጃጀት ማጠናከር፣ ከሌሎች ትክክለኛና ተቀራራቢ የትግል ዓላማ ካላቸው ተቃዋም ፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በመተዳደሪያችን ደንብና ፖለቲካ ፕሮግራማችን መሠረት በጋራ መስራት ይገኝበታል፡፡ የውስጥ አደረጃጀትን ማጠናከር አብዘኛው የዓለም ታሪክ እንደሚያ

በሃዋሳ ከተማ የኣንዳንድ መንደሮች ነዋሪዎች በራስ ተነሳሳሽነት መልካምኣስተዳደርን ለማምጣት የሚያደርጉት እንቅስቃሴ የክልሉን መንግስት ትኩረት መሳቡ ተነገረ

Image
በሃዋሳ ከተማ የኣንዳንድ መንደሮች ነዋሪዎች በራስ ተነሳሳሽነት መልካምኣስተዳደርን ለማምጣት የሚያደርጉት እንቅስቃሴ የክልሉን መንግስት ትኩረት መሳቡ ተነገረ ሪፖርተራችን ቱንስሳ ጂሎ ከሃዋሳ እንደዘገበው፤  በሀዋሳ ከተማ በባህል አዳራሽ ክፍለ ከተማ የሚገኙ የታረቀኝ፣ የዳንዲ ቦሩ፣ የአረጋውያንና የግራር መንደር ነዋሪዎች በአንድ ለአምስት በመደራጀት ጨለማን ተገን በማድረግ የሚፈጸሙ የዝርፊያና ሌሎች ህገወጥ ድርጊቶችን ለማስቆም በትምህርት ፣በጤናና በግብር ዙሪያ ሌሎች ቀበሌዎች ኣርኣያ የሆኑ ተግባራትን በማከናውን ላይ ናቸው። እነዚህ መሃል ከተማ መንደሮች ከዚህ በፊት በጸጥታ እና በሌሎች ችግሮች የሚታወቁ እና የመደሮቹም ነዋሪዎች በዘርፎብዙ ችግሮች ይሰቃዩ የነበሩ ናቸው። ሰሞኑን በክልሉ ምክትል ርዕስ መስተዳደር  በኣቶ መለሰ ኣለሙ  የተመራ ኣንድ የመንግስት ኣካል የመደራቱን የስራ እንቅስቃሴ የጎበኘ ሲሆን፤ በስራ ኣፈጻጸማቸው መደሰቱን እና በሃዋሳ  ከተማ የሚታዩ የመልካም አስተዳድር ችግሮችን ለመፍታት ነዋሪው የተለያዩ አደረጃጀቶች በመጠቀም እያከናወነ ያለውን ተግባር ተጠናክሮ መቀጠል ኣለበት ብለዋል።   የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ አቶ ዮናስ ዮሴፍ በበኩላቸው እንዳሉት የአራቱ መንደር ነዋሪዎች በራሳቸው ተነሳሽነት በመንደሮቹ ያለውን የመንገድ ችግር ለማቃለል ከመቶ ሺህ በላይ ብር በማዋጣትና ከከተማው አስተዳደር ጋር በመተባበር ጠጠር በማልበስና ሌሎች የልማት ስራዎችን በማከናወን  ከጠባቂነት ለመላቀቀ ያላቸውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል።  መንግስት በከተሞች መልካም አስተዳደርን ለማስፈን እያከናወነ ያለውን ተግባር ለማገዝ የመንደሮቹ ነዋሪዎች እየሰሩት ያለው ስራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትነ አምልክተዉ ይህን ስራቸውን

የሃዋሳን ከተማ ነዳጅ ማደያዎችን ጨምሮ የነዳጅ ምርቶችን በአግባቡ በማያከፋፍሉ ኩባንያዎች ላይ መንግስት እርምጃ ሊወስድ ነው

Image
አዲስ አበባ ፣ ጥር 27 ፣ 2006  (ኤፍ.ቢ.ሲ ) ሰሞኑን የቤንዚንና የናፍታ እጥረት በመዲናችን አዲስ አበባና በበርካታ የክልል ከተሞች ተከስቷል ። በአንዳንድ አካባቢዎች እና ከተሞች ችግሩ አሁን ድረስ ያልተፈታ ሲሆን  ፥ በትራንስፖርት እንቅስቃሴው ላይም ከፍተኛ ጫናን እያሳረፈ ይገኛል ። የቤንዚንና የናፍታ እጥረቱ በዋናነት በአዲስ አበባና በደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል በሚገኙት ከተሞች  በሃዋሳ ፣ ሆሳዕና ፣ ወላይታ ሶዶ እና ሚዛን አማን ነው የተከሰተው ። በሃዋሳ ከተማ ወደ 45 ሺህ ሊትር የሚጠጋ የነዳጅ ስርጭት እየተካሄደ እንደሚገኝና ይህም ቢሆን በቂ እንዳልሆነ የንግድ ሚንስትር ድኤታ አቶ ዓሊ ሲራጅ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ተናግረዋል። በተቀሩት ከተሞች ማለትም  ሆሳዕና ፣ ወላይታ ሶዶ እና ሚዛን አማን ግን እጥረት መስተዋሉን ነው የጠቀሱት። በተመሳሳይ በተለያዩ የመዲናችን አካባቢዎች በዚህ ሳምንት የነዳጅ እጥረት የተስተዋለባቸውን ምክንያቶች አቶ ዓሊ ሲራጅ የገለፁ ሲሆን ፥ በዋናነትም ሃላፊነቱ የተሰጣቸው የነዳጅ አከፋፋይ ኩባንያዎች ሀላፊነታቸውን በአግባቡ ባለመወጣታቸውና ነዳጁን ማከፋፈል በማቆማቸው የተፈጠረ ነው ብለዋል። ዋናውና እጥረቱን ያባባሰው  ኩባንያዎቹ በወሩ መጨረሻ የነዳጅ ዋጋ ይጨምራል በሚል የተሳሳተ እሳቤ ቀደም ብለው በርካሽ የገዙትን ነዳጅ በውድ ዋጋ ለመሸጥ ካላቸው ፍላጎት የተነሳ እንደሆነ የገለፁት ሚንስትር ድኤታው ፥ ይሁንና ምንም አይነት የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ እንደሌለ ህብረተሰቡም ሆነ የነዳጅ አከፋፋዮች መረዳት እንዳለባቸው ነው የገለፁት። በተጨማሪም ኦይል ሊቢያ ይጠቀምባቸው የነበሩ 48 ያህል ተሽከርካሪዎች ወደ ሌሎች ኩባንያዎች በመሄዳቸው ፤ የነዳጅ አቅርቦት እጥረቱ ከተሽከርካሪ እ

በሲዳማ ዞን ሃርቤጎና ወረዳ በ250 ሚሊየን ብር ቀርከሃን ወደ ጣውላ የሚቀይር ፋብሪካ ሊገነባ ነው

Image
ኢህኣዴግ ወደ ስልጣና መምጣቱን ተከትሎ በመላው ኣገሪቷ የኢንዱስትሪ ልማት በከፍተኛ መልኩ ትኩረት ተሰጥቶት በመካሄድ ላይ ቢሆንም የሲዳማ ዞን የዚህ እድል ተጠቃሚ ሳይሆን ቆይቷል፤ መንግስት በተለይ በሲዳማ ዞን እና በሃዋሳ ከተማ በመከተል ላይ ባለው የኣገልግሎት ኢንዱስትሪ የማስፋፋት ፖሊስ የተነሳ  ወደ ዞኑ ብሎም ወደ ከተማዋ የሚፈሰው የኢንቨስትመንት ፍስት በኣገልግሎት ስጪ ድርጅቶች ግንባታ ላይ ያተኮረ በመሆኑ፤ ዞኑ በሆቴሎች እና ሎጆች እንዲሞላ ከማድረግ ያለፈ ፋይዳ ኣልነበረውም፤ የሲዳማ ዞን በሃዋሳ ከተማ እና በዙሪያዋ በባለሃብቶች ከተገነቡ ጥቂት የመጠጥ እና ምግብ ፋብሪካዎች በስተቀር ለላፉት 20 ኣመታት  በኢንዱስትሪ ልማት ዘርፍ የተረሳ ዞን ነው። በሲዳማ ዞን ውስጥ ኣልፎ  ኣልፎ  በየወረዳዎች ከምታዩት የቡና መፈልፈያ እና ማቀነባበሪያዎች በስተቀር ለዞኑ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያለውን ልማት ማስመዝገብ የሚያስችል ኣንድም ፋብሪካ የለም። ሃዋሳ እና በዙሪያዋ ያሉት ጥቂት ፋብሪካዎች ለሲዳማ ኢኮኖሚ ያበረከቱት ኣስተዋጽኦ ይሄ ነው የሚባል ኣይደለም፤ በእነዚህ ፋብሪካዎች ተቀጥረው ራሳቸውን እና ቤተሰቦቻቸውን የምደጉሙ ሲዳማውያን በጣት የምቆጠሩ ናቸው። በተቃራኒው መንግስት ለኢንዱስትሪ ልማት በማለት ቤት ንብረታቸውን ኣስነስቶ  መሬቶቻቸውን የነጠቃቸው ሲዳማውያን ቁጥር በርካታ ነው።  ከዚህም ባሻገር መንግስት በተለይ በሲዳማ ዞን እና በሃዋሳ ከተማ በመከተል ላይ ባለው የኣገልግሎት ኢንዱስትሪ የማስፋፋት ፖሊስ የተነሳ  ወደ ዞኑ ብሎም ወደ ከተማዋ የሚፈሰው የኢንቨስትመንት ፍስት በኣገልግሎት ስጪ ድርጅቶች ግንባታ ላይ ያተኮረ በመሆኑ፤ ዞኑ በሆቴሎች እና ሎጆች እንዲሞላ ከማድረግ ያለፈ ፋይዳ የለው። የሲዳማ ዞን መንግስት

የቡና ዘርፍን በባለቤትነት የሚያስተዳድር ድርጅት ሊቋቋም ነው

Image
ባለቤት የሌለውን የኢትዮጵያ የቡና ዘርፍ ባለቤት እንዲኖረው ለማድረግ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት የሚገኙበት ልዑካን ቡድን የሌሎች አገሮች ልምድ በመቅሰም ሥራ ላይ ተጠምዷል፡፡ ጥናቱ ሲጠናቀቅ ቡናን በበላይነት የሚመራ መንግሥታዊ ተቋም ይቋቋማል ተብሏል፡፡  ከጥቂት ሳምንታት በፊት በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ቦርድ ሰብሳቢ በሆኑት አቶ አዲሱ ለገሰ የሚመራ ልዑካን ቡድን ብራዚልና ኮሎምቢያ በመጓዝ፣ አገሮቹ የቡናን ዘርፍ እንዴት እንደሚመሩ ልምድ ቀስሞ ተመልሷል፡፡  ባለፈው ሳምንት ደግሞ የንግድ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ያዕቆብ ያላ፣ በጠቅላይ  ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የፋይናንስ፣ የንግድ፣ የፖሊሲና የዕቅድ አፈጻጸም ቁጥጥር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ አያና ዘውዴን ጨምሮ የግብርና ሚኒስቴር ባለሥልጣናት ያሉበት የልዑካን ቡድን ጓቴማላና ኮስታሪካ በዘርፉ ያላቸውን ልምድ ለመቅሰም ተጉዟል፡፡ በሌላ በኩል የኢትዮጵያ የቡና ዘርፍ ምን ዓይነት አደረጃጀትና አሠራር ይኑረው የሚለውን ጉዳይ የአውሮፓ ኅብረትና ዩኤስአይዲ በየራሳቸው መንገድ ጥናት እያስጠኑ መሆናቸው ታውቋል፡፡ እነዚህ ጥናቶች ሲጠናቀቁ ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ቀርቦ ውሳኔ እንደሚያገኝ መረጃዎች አመልክተዋል፡፡ ባለፉት ዘመናት የቡና ዘርፍ በተለያዩ አደረጃጀቶች ተመርቷል፡፡ ቀደም ሲል ቡና ቦርድ፣ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን፣ ቀጥሎም የቡናና ሻይ ሚኒስቴር ተቋቁሞ የቡናን ዘርፍ ሲመሩት ቆይተዋል፡፡ ነገር ግን ኢሕአዴግ አገሪቱን ከተቆጣጠረ በኋላ ወጥ በሆነ መንገድ ዘርፉን የሚመራ ተቋም ባለመኖሩ ዘርፉ የሚጠበቀውን ያህል ርቀት መጓዝ ሳይችል እንደቀረ ባለሙያዎች ያብራራሉ፡፡ መንግሥት ዘግይቶ የቡናን ዘርፍ የሚመራ አንድ ጠንካራ ተቋም ያስፈልጋል የሚል ውሳኔ ላይ በመድረሱ፣ ለጉዳዩ ቅ