በሲዳማ ዞን ሃርቤጎና ወረዳ በ250 ሚሊየን ብር ቀርከሃን ወደ ጣውላ የሚቀይር ፋብሪካ ሊገነባ ነው
ኢህኣዴግ ወደ ስልጣና መምጣቱን ተከትሎ በመላው ኣገሪቷ የኢንዱስትሪ ልማት በከፍተኛ መልኩ ትኩረት ተሰጥቶት በመካሄድ ላይ ቢሆንም የሲዳማ ዞን የዚህ እድል ተጠቃሚ ሳይሆን ቆይቷል፤ መንግስት በተለይ በሲዳማ ዞን እና በሃዋሳ ከተማ በመከተል ላይ ባለው የኣገልግሎት ኢንዱስትሪ የማስፋፋት ፖሊስ የተነሳ ወደ ዞኑ ብሎም ወደ ከተማዋ የሚፈሰው የኢንቨስትመንት ፍስት በኣገልግሎት ስጪ ድርጅቶች ግንባታ ላይ ያተኮረ በመሆኑ፤ ዞኑ በሆቴሎች እና ሎጆች እንዲሞላ ከማድረግ ያለፈ ፋይዳ ኣልነበረውም፤ የሲዳማ ዞን በሃዋሳ ከተማ እና በዙሪያዋ በባለሃብቶች ከተገነቡ ጥቂት የመጠጥ እና ምግብ ፋብሪካዎች በስተቀር ለላፉት 20 ኣመታት በኢንዱስትሪ ልማት ዘርፍ የተረሳ ዞን ነው። በሲዳማ ዞን ውስጥ ኣልፎ ኣልፎ በየወረዳዎች ከምታዩት የቡና መፈልፈያ እና ማቀነባበሪያዎች በስተቀር ለዞኑ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያለውን ልማት ማስመዝገብ የሚያስችል ኣንድም ፋብሪካ የለም። ሃዋሳ እና በዙሪያዋ ያሉት ጥቂት ፋብሪካዎች ለሲዳማ ኢኮኖሚ ያበረከቱት ኣስተዋጽኦ ይሄ ነው የሚባል ኣይደለም፤ በእነዚህ ፋብሪካዎች ተቀጥረው ራሳቸውን እና ቤተሰቦቻቸውን የምደጉሙ ሲዳማውያን በጣት የምቆጠሩ ናቸው። በተቃራኒው መንግስት ለኢንዱስትሪ ልማት በማለት ቤት ንብረታቸውን ኣስነስቶ መሬቶቻቸውን የነጠቃቸው ሲዳማውያን ቁጥር በርካታ ነው። ከዚህም ባሻገር መንግስት በተለይ በሲዳማ ዞን እና በሃዋሳ ከተማ በመከተል ላይ ባለው የኣገልግሎት ኢንዱስትሪ የማስፋፋት ፖሊስ የተነሳ ወደ ዞኑ ብሎም ወደ ከተማዋ የሚፈሰው የኢንቨስትመንት ፍስት በኣገልግሎት ስጪ ድርጅቶች ግንባታ ላይ ያተኮረ በመሆኑ፤ ዞኑ በሆቴሎች እና ሎጆች እንዲሞላ ከማድረግ ያለፈ ፋይዳ የለው። የሲዳማ ዞን መንግስት