Posts

በኣነስተኛ እና ጥቃቂን ማህበራት የተደራጁ የሲዳማ ወጣቶች የመንግስት ትኩረት እንደምያሹ መግለጻቸውን ተከትሎ የዞኑ መንግስት ለማህበራቱ የገበያ ትስስር መፈጠሩን ኣስታወቀ

Image
ከሶስት ሳምንታት በፊት የወራንቻ ኢንፎርሜሽን ኔትዎርክ ዘጋብ ሪፖርተር ጥቻ ወራና '' በተለያዩ የሲዳማ ከተሞች በኣነስተኛ እና ጥቃቂን ማህበራት ተደራጅተው ያሉ የሲዳማ ወጣቶች የመንግስት ትኩረት ያሻቸዋል ተባለ '' በምል ሃዋሳን  ጨምሮ  በሲዳማ ዞን ባሉ በኣነስተኛ እና ጥቃቂን ማህበራት የተደራጁ ወጣቶችን የስራ እንቅስቃሴ የምቃኝ ዘገባ ማቅረቡን ተከትሎ የዞን መንግስት ለወጣቶቹ የገበያ ትስስር ስራ መስራቱን በመናገር ላይ ነው። ሪፖርተራችን ያናገራቸው በጥቃቅን እና ኣነስተኛ የልማት ስራዎች የተደራጁ ወጣቶች ዘላቂነት ያለው የሙያ ስልጠና የማግኘት እና ለምርቶቻቸው ደግሞ ገበያ የማፈላለግ ችግሮች እንዳሉባቸው የጠቆሙ ሲሆን፤ የዞኑ ንግድና ኢንዱስትሪ መምሪያ በበኩሉ ከ85 ሚሊዮን ብር በላይ የገበያ ትስስር መፈጠሩን ዛሬ ለኢትዮጵያ ዜና ኣገልግሎት በሰጠው መረጃ ኣመልክቷል። ሁለቱንም ዘጋባዎች ኣያይዘን ኣቅርበናል ከታች ያንቡ፦      አዋሳ ጥር 14/2006 በሲዳማ ዞን  ባለፉት ስድስት ወራት ተደራጅተው በጥቃቅንና አነስተኛ የልማት ስራዎች ለተሰማሩ አንቀሳቃሾች ከ85 ሚልዮን ብር በላይ የገበያ ትስስር መፈጠሩን የዞኑ ንግድና ኢንዱስትሪ መምሪያ ገለጸ፡፡  በመምሪያው የኢንተርፕራይዞች ልማት የስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ደበበ ተገኝ ትናንት ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት የገበያ ትስስሩ የተፈጠረው ከ11ሺህ በላይ ለሚሆኑ አንቀሳቃሾች ነው፡፡  በዞኑ ሁለት የከተማ አስተዳደሮችና 19 ወረዳዎች ለሚገኙት ለእነዚሁ አንቀሳቃሾች ምርትና አገልግሎታቸውን ለገበያ የሚያቀርቡበት ሁኔታ በማመቻቸት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ተደርጓል፡፡  በዞኑ ባለፉት 6 ወራት ከ11ሺህ በላይ  ሰዎች ተደራጅተው በጥቃቅንና አነስተኛ ንግድና የስራ ዘ

Deadly bacterial wilt disease free ''wesse'' for Sidama

Image
[ADDIS ABABA] A research project for developing varieties of enset, a traditional Ethiopian crop which resembles the banana plant, resistant to the deadly bacterial wilt disease has been launched.    The project launched last month (16 December) in Addis Ababa, Ethiopia, is expected to address the perennial problem of the bacterial wilt disease that has remained a nightmare for scientists and   farmers   in the country.   The disease is caused by the bacterium   Xanthomonas campestris   pv. musacearum,   and results in total crop wilt. “Bacterial wilt is the major threat to enset, which supports the livelihoods of nearly 20 million smallholder farmers.” Adugna Wakjira, Ethiopian Institute of Agricultural Research (EIAR)   Adugna Wakjira, the deputy director of the Ethiopian Institute of Agricultural Research (EIAR), tells SciDev.Net : “Bacterial wilt is the major threat to enset, which supports the livelihoods of nearly 20 million smallholder farmers,” adding that lack of   res

Natural Attraction in Sidama

Image
Tourism Natural Attraction in Sidama The magnificent natural scenery & hot spring water in the Sidama zone include:   Wondo Genet, Burqito Gidabo, etc.     Like wise the zone is blessed with spectacular water falls; Logita Fall Sidama 120km from Hawassa with torrential sound and Bonora Fall Sidama 135km from Hawassa cataract & blue winged birds There are two areas proposed as protected wildlife reserve that are now being delimited. Garamba   Mountain   is the highest point in the zone. It is located at a distance of 363 km from   Addis Ababa , 84 km distance from Hawassa, and also only 14 km away from Yaye (District main town). The height of the mountain is between 2800m and 3360m. The mountain is surrounded by bamboo forest; and it is convenient for tourists who have mountain trekking hobby. The mountain is home for various wildlife and bird species. There is an attractive topography round the foot of the mountain. One can watch   Bale   Mountai

በሀዋሳ ከተማ አንድ ነዳጅ የጫነ ቦቴ በእሳት በመያያዙ በንብረት ላይ ጉዳት ደረሰ

Image
አዋሳ ጥር 12/2006 በሀዋሳ ከተማ ከትናንት በስቲያ ምሽት አንድ የነዳጅ መጫኛ ቦቴ ባልታወቀ ምክንያት በእሳት በመያያዙ ተሽከርካሪውና ነዳጁ መውደማቸዉን  የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ ። የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር ዳንኤል ገዛኽኝ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት በእለቱ ከምሽቱ  አንድ ሰዓት ገደማ ላይ አደጋዉ የደረሰዉ ቦቴዉ የጫነዉን ነዳጅ በኦይል ሊቢያ ነዳጅ ማደያ ዉስጥ በማራገፍ ላይ እንዳለ በተነሳዉ ድንገተኛ እሳት ነዉ  ። የነዳጅ መጫኛ ቦቴዉ  በእሳት በመያያዙ ሾፌሩ በፍጥነት መኪናውን ከነዳጅ ማደያው በማውጣትና ወደ ዋናው መንገድ ላይ ወስዶ በማቆም እሳቱ ወደ  እንዳይዛመት በማድረግ ሊደርስ ይችል የነበረዉን አደጋ መከላከል መቻሉን አስታዉቀዋል ። አሽከርካሪውን በፍጥነት ከማደያዉ አካባቢው በማራቁም  በአቅራቢያ  በሚገኙ ሁለት ሌሎች የነዳጅ ማደያ ጣቢያዎች ላይ ሊደርስ የሚችለዉን  አደጋ መከላከል መቻሉን  ተናግረዋል ። እሳቱን ለማጥፋት የከተማው ነዋሪዎችና የፖሊስ አባላት ከፍተኛ ርብርብ ማድረጋቸዉንና በንብረት ውጪ በሰው ህይወት  ላይ የደረሰ ጉዳት አለመኖሩን ዋና ኢንስፔክተሩ ጠቁመው የአደጋው መንስኤና የደረሰው ውድመት እየተጣራ ነዉ ብለዋል ። የነዳጅ ቦቴው በውስጡ ባሉት አራት ክፍሎች  በአጠቃላይ እስከ 600 ሺህ ሊትር ነዳጅ የመያዝ አቅም እንዳለው ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸዉ ባለሙያዎች ጠቁመዋል ።

በሲዳማ ዞን ከ13ሺህ በላይ ላሞችና ጊደሮችን የማዳቀል ስራ ተከናውኗል

Image
አዋሳ ጥር 12/2006 በሲዳማ ዞን ባለፉት 6 ወራት ከ13ሺህ በላይ ላሞችና ጊደሮችን የውጭ ዝርያ ካላቸው ኮርማዎችና በሰው ሰራሽ ዘዴ የማዳቀል ስራ መከናወኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ ገለጸ ፡፡ የማዳቀሉ ስራ የተከናወነው በሸበዲኖ፣በአለታ ጩኮ፣ በአለታ ወንዶና በዳሌ ወረዳዎች ሲሆን በቀጣይም በቀሪ የዞኑ ሁሉም ወረዳዎች በተመሳሳይ ለማካሄድ ዝግጅት መጠናቀቁም ተመልክቷል፡፡ በመምሪያ   የግብርና ልማት እቅድ፣ ዝግጅት፣ ክትትልና ግብረ መልስ የስራ ሂደት ኦፊሰር አቶ ደርቤ በትራ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት እንስሳቱን ማዳቀል ያስፈለገው  የወተትና የስጋ  ምርትና ምርታማነታቸውን በማሻሻል የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማጎልበት ነው፡፡ በዚህም አንዲት የአካባቢው ዝርያ ያላት ላም በቀን የምትሰጠውን ከሁለት እስከ ሶስት ሊትር ያልበለጠ የወተት ምርት ከሶስት እጥፍ በላይ ማሳደግ ያስችላል፡፡ በየወረዳዎቹ የሚገኙ አርሶ አደሮችን በአንድ ለአምስትና በልማት ቡድኖች በማቀናጀት በየደረጃው በሚገኙ የዘርፉ ባለሙያዎች አማካኝነት የአቅም ግንባታ ስልጠና መሰጠቱን የገለጹት ኦፊሰሩ የእንስሳት ዝርያ የማሻሻሉ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡ ቀደም ብሎ በኮርማና በሰው ሰራሽ ዘዴ የተዳቀሉ ከ6ሺህ በላይ ጥጆች መወለዳቸውንም ተናግረዋል፡፡ በዚህም  ባለፉት ስድስት ወራት የወተት ምርትና ምርታማነትን በማሻሻል 66ሺህ 890 ቶን ወተት በማምረትና ለገበያ በማቅረብ አርሶ አደሩን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ገልፀዋል፡፡ በዞኑ ሰፊ የእንስሳት ሃብት ቢኖርም በተለይ የወተትና ወተት ተዋፅኦ ምርት ዝቅተኛ በመሆኑ ይህንን ለማሻሻል በሁሉም የዞኑ ወረዳዎች የዝርያ ማሻሻሉ ስራ ለማስፋፋት መዘጋጀታቸውን የስራ ሂደቱ ኦፊሰር አመልክተዋል፡፡