Posts

ግብፅ ዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት ለኢትዮጵያ ብድርና ዕርዳታ እንዳይሰጡ እየተንቀሳቀሰች ነው ተባለ

‹‹ለሱዳን የተሰጠ መሬት የለም››  መንግሥት ዓለም አቀፍ አበዳሪና ለጋሽ ድርጅቶች ለኢትዮጵያ የሚሰጡትን ብድርና ዕርዳታ እንዲያቆሙ ግብፅ እየተንቀሳቀሰች መሆኗን መንግሥት መረጃ እንዳለው አስታወቀ፡፡  በታላቁ የህዳሴ ግድብ ላይ የተጀመረው የሦስትዮሽ ድርድር ሦስተኛ ስብሰባ በቅርቡ ያለውጤት ከተበተነ በኋላ፣ በግብፅ በኩል አፍራሽ የሆኑ እንቅስቃሴዎች መጀመራቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል፡፡  ባለፈው ዓርብ ረፋድ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ በጽሕፈት ቤታቸው መግለጫ የሰጡት አምባሳደር ዲና፣ በግብፅ በኩል የቀረበውና በኢትዮጵያና በሱዳን ውድቅ የሆነው ሐሳብ፣ እስካሁን ግድቡን አስመልክቶ የተጀመሩ ውይይቶችን ወደኋላ የሚመልስ መሆኑን ተናግረዋል፡፡  የውጭ ባለሙያዎች ያሉበትና ከሦስቱም አገሮች የተውጣጡ የውኃ ባለሙያዎች የተሳተፉበት የኤክስፐርቶች ፓነል ለአንድ ዓመት በግድቡ ዙሪያ ጥናት አካሂዶ ባወጡት ሪፖርት፣ ከተወሰኑ ቴክኒካዊ ማስተካከያዎች ውጪ ግድቡ ዓለም አቀፍ ደረጃ ያሟላ መሆኑን ይፋ ማድረጋቸው ይታወሳል፡፡  የፓነሉ ምክረ ሐሳብ ተግባራዊ የሚያደርግ ከሦስቱ አገሮች የተውጣጡ የውኃ ባለሙያዎች ያሉበት ኮሚቴ የተቋቋመ መሆኑን፣ ግብፆች አዲስ የዓለም አቀፍ ባለሙያዎች ቡድን ተቋቁሞ የኮሚቴውን ሥራ በበላይነት እንዲከታተል የሚል ሐሳብ ነው ያቀረቡት፡፡  እንደ አምባሳደር ዲና ገለጻ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ተቃውሞ በዓለም አቀፍ ባለሙያዎች ፓነል መቋቋም ላይ ሳይሆን፣ ሚናውን በተመለከተ ነው፡፡ በዚህ ልዩነት የተነሳ ያለውጤት ስብሰባው ከተበተነ በኋላ፣ ግብፆች በሚዲያዎቻቸው ‹‹ኢትዮጵያ ለመተባበር እምቢተኛ ሆነች›› እያሉ እያቀረቡ መሆኑንና ከዓለም ባንክ፣ ከአይኤምኤፍና በሌሎች ዓለም አቀፍ

Ethiopia: Hawassa Earned 48 mln. Birr Revenue from Tourism

Hawassa City earned over 48 million birr revenue from tourists who visited attraction in the city in the past six months, The Ethiopian Herald reported. The amount earned in the reported period increased by nine million birr compared to the same period in the pervious year, according to the city's Culture, Tourism and Communication Affairs Department. The department attributed the growth to promotion activities carried out in collaboration with stakeholders, infrastructure developments and making destinations attractive for tourists. Over 93,940 local and foreign tourists visited historic and natural sites during the reported period. Source: The Ethiopian Herald

የደቡብ ክልል ፍትህ ቢሮ 60 አቃቢያነ ህግን በስነምግባር ግድፈት ከስራ አሰናበተ

አዲስ አበባ፣ ጥር 9፣ 2006(ኤፍ.ቢ.ሲ.) የደቡብ ክልል ፍትህ ቢሮ 60 አቃቢያነ ህግን በስነምግባር ግድፈት ከስራ አሰናበተ። ቢሮው ሌሎች 211 የሚሆኑትን ከቀላል እስከ ከባድ የሚደርስ እርምጃ ወስዶባቸዋል። በተመሳሳይ የክልሉ ማረሚያ ኮሚሽንም 42 የሰራዊቱ አባላት ላይ ከባድ እርምጃ የወሰደ ሲሆን፥ ከዚህ ውስጥ 10 የሚሆኑት ሙሉ በሙሉ ከስራቸው የተሰናበቱ ናቸው የክልሉ ፍትህ ቢሮ ሃላፊ አቶ እድማሱ አንጎ እና የማረሚያ ኮሚሽን ኮሚሽነሩ አዳነ ዲንጋሞ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደተናገሩት፥ ግለሰቦቹ እርምጃው የተወሰደባቸው ጉቦ በመቀበል፣  ፍትህ በማዛባት፣ በወገናዊነት መስራት እና እስረኞች እንዲያመልጡ ማድረግ የመሳሰሉትን ወንጀሎች ፈፅመው በመገኘታቸው ነው። ከቀበሌ እስከ ክልል ድረስ ነዋሪዎችን ባሳተፈ ሁኔታ የተካሄደው እርምጃ ቀጣይነት የሚኖረው መሆኑንም የስራ ሃላፊዎቹ ተናግረዋል። እርምጃ  ከተወሰደባቸው  ግለሰቦች መካከልም አብዛኛዎቹ  ክስ  ይመሰረትባቸዋል ተብሏል። http://www.fanabc.com/index.php?option=com_content&view=article&id=7153:----60------&catid=102:slide

የካንሰር ህክምና ማዕከል በሃዋሳ ሊከፈት ነው

አዲስ አበባ ፣ ጥር 9 ፣ 2006(ኤፍቢሲ)በተለያዩ የሃገሪቱ አካባቢዎች ስድስት የካንሰር ህክምና ማዕከላት ሊከፈቱ ነው። የጤና ጥበቃ ሚንስትሩ ዶክተር ከሰተብርሃን አድማሱ ማዕከላቱ አስፈላጊው ግብዓት ተሟልቶላቸው  በመጪው መስከርም ወር ስራ እንደሚጀምሩ ተናግረዋል። በአሁኑ ውቅትም ከ12 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ ወጪ በማድረግ ለማዕከላቱ የህክምና ቁሳቁስ ግዥ ለመፈፀም ሂደቱ መጠናቀቁን ገልፀዋል። የካንሰር ህክምና መስጫ ማዕከላቱ በጎንደር፣ መቀሌ፣ ጅማ፣ ሀዋሳ እና በሀሮማያ የሚከፈቱ ሲሆን፥ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ደግሞ  ማዕከሉን የማስፋፋት ስራ እየተካሄደ ይገኛል ። የካንሰር ህክምና መስጫ ማዕከላቱ  መስፋፋት በመስኩ የሚሰተዋለውን የህክምና አገልግሎት እጥረት በመቀረፍ እና የካንሰር ህሙማን እንግልትን በመቀነስ ተገቢውን አገልግሎት እንዲያገኙ ያሰችላል ብለዋል።

አሁንም የፕሬስ ነፃነት ይከበር እንላለን!

ሕገ መንግሥቱ ለፕሬስ ነፃነት ዋስትና ሲሰጥ በአንቀጽ 29 በሚገባ በማብራራት በማናቸውም መንገድ ሕጋዊ ከለላ እንደሚደረግለት ደንግጓል፡፡ የሕገ መንግሥቱ  አንቀጽ 29 በሰባት ንዑስ አንቀሶች ታጅቦ የአመለካከትና ሐሳብን በነፃ የመያዝና የመግለጽ መብት አረጋግጧል፡፡ ይህ የሕገ መንግሥቱ ወርቃማ አንቀጽ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የሰብዓዊ መብት ድንጋጌ አንቀጽ 19 ቀጥተኛ ግልባጭ ነው፡፡ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 29 መሠረት ማንም ሰው ያለማንም ጣልቃ ገብነት ሐሳብ የመግለጽ፣ በፕሬስና በሌሎች መገናኛ ብዙኃን፣ እንዲሁም በማንኛውም የማሠራጫ ዘዴ ማንኛውንም መረጃ የመሰብሰብ፣ የመቀበልና የማሠራጨት መብቶችን ያጠቃልላል፡፡ ቅድመ ምርመራ (ሳንሱር) ተከልክሏል፡፡ የተለያዩ አስተሳሰቦችን ማራመድ ይቻላል፡፡ ለዚህም ሕጋዊ ጥበቃ ይሰጣል፡፡ ማንኛውም ዜጋ በእነዚህ መብቶች አጠቃቀም ረገድ የሚጣሉ ሕጋዊ ገደቦችን ጥሶ ከተገኘ በሕግ ተጠያቂ ሊሆን ይችላል ይላል፡፡  ኢትዮጵያ ውስጥ የግል ጋዜጦችና መጽሔቶች ሥራ ላይ ከዋሉ 22 ዓመታት እየተቆጠሩ ነው፡፡ በእነዚህ ዓመታት በበርካታ ውጣ ውረዶች ውስጥ በማለፍ የግሉ ፕሬስ ውጤቶች ጠቃሚ አስተዋጽኦ ማበርከታቸው አይካድም፡፡ አሁንም በጎርባጣው ጎዳና ላይ እየተጓዙ ናቸው፡፡ በመቶዎች የሚቆጠሩ የፕሬስ ውጤቶች ይቀርቡባቸው የነበሩ ዓመታት አልፈው አሁን ውስን ጋዜጦችና መጽሔቶች ቀርተዋል፡፡ በእነዚህ ዓመታት የግሉ ፕሬስ ፈተናዎች በሁለት ምክንያቶች ሥር ሊጠቃለሉ ይችላሉ፡፡ አንደኛው ውጫዊ ሲሆን፣ ሁለተኛው ውስጣዊ ችግር ነው፡፡  የውጭውን ተፅዕኖ ስንፈትሽ ችግሩ ከመንግሥት ይጀምራል፡፡ መንግሥት የፕሬስ ነፃነትን በተመለከተ ሕጎችን፣ ደንቦችንና መመርያዎችን ከማውጣት ባለፈ ለፕሬሱ ዕድገት የሚያደርገው አስተዋጽ