የሲዳማኔት ኮሌጅ አምስተኛውን የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውድድር በሐዋሳ ኣዘጋጅቷል
በልዩ ልዩ ምክንያቶች በውድድሩ የማይሳተፉ ተቋማት ከማህበሩ ጋር በመነጋገር ተሳታፊ መሆን እንደሚገባቸው በመግለጫው ወቅት አጽንኦት ተሰጥቶታል፤ በየዓመቱ በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች መካከል የሚካሄደው የስፖርት ፌስቲቫል ከየካቲት 16 እስከ 30 በደቡብ ክልል ዋና ከተማ ሀዋሳ እንደሚካሄደ ተገለጸ። የውድድሩ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ትናንት በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ለማወቅ እንደተቻለው ፌስቲቫሉን የሲዳማኔት ኮሌጅ ያዘጋጃል። የግል ከፍተኛ ተቋማት ስፖርት ማህበር ፕሬዚዳንት ዶክተር አብነት ግርማይ እንደተናገሩት፣ የዘንድሮው ውድድር በአስር የስፖርት ዓይነቶች በሁለቱም ጾታዎች ይካሄዳል። በውድድሩ 25 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እንደሚሳተፉና ከ 2 ሺ 500 እስከ 3 ሺ የሚደርሱ ስፖርተኞች እንደሚካፈሉ ተናግረዋል። በውድድሩ የሚካፈሉ ተቋማት በብዛት የሚገኙት ከአዲስ አበባ፣ ከኦሮሚያና ከደቡብ ክልሎች ብቻ ስለመሆናቸው፣ ከመንግሥት ከፍተኛ ተቋማት ጋር ውድድሩን ለማካሄድ ስላለመቻሉና ሌሎች ጥያቄዎች ከጋዜጠኞች የቀረበላቸው ዶክተር አብነት፣ « ውድድሩን በሁሉም የሀገራችን ክልሎች ለማካሄድ ፍላጎትና እቅድ ቢኖረንም የተቋማቱ ፍላጎት ማጣት ነው በሦስቱ ክልሎች ብቻ እንዲወሰን የተደረገው። ያም ሆኖ ከትግራይ ክልል ሁለት ኮሌጆችና ዩኒቨርሲቲ ኮሌጆች ይሳተፋሉ። ከመንግሥት ከፍተኛ ተቋማት ጋር በጋራ ውድድሩን ለማካሄድ እስካሁን ብዙ ሙከራ አድርገናል። አሁን ጥሩ ተስፋ ሰጪ ምልክቶች አሉ ውጤቱን ወደ ፊት የምናየው ይሆናል » ብለዋል። ውድድሩን በየዓመቱ ከማካሄድ በዘለለ በሁሉም ክልሎች የሚገኙ ተቋማት እንዲካፈሉና ውድድሩንም ለማዘጋጀት እንዲችሉ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴው ጥረት እያደረገ መሆኑን ዶክተር አብነት ጨምረው