Posts

የገና በዓልና ተያያዥ ኩነቶች

Image
በአገራችን ከሚከበሩ ሕዝባዊና ሃይማኖታዊ በዓላት መካከል ገና አንዱ ነው፡፡ ይህ በዓል በክርስትና አማኞች ዘንድ የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት መታሰቢያ ነው፡፡ ከፈረንጆቹ ገና በአንድ ሳምንት ዘግይቶ የሚከበረው ይህ ሃይማኖታዊ በዓል፣ በሁሉም የክርስቲያን ቤተ እምነቶች በኩል በተለያዩ ሃይማኖታዊ ሥርዓቶች ይከበራል፡፡ የቱሪስት መስህብ በሆነው በደብረ ሮሃ ላስታ ላሊበላ ያለው አከባበር ደግሞ ከሁሉም የተለየና የሚማርክ ነው፡፡ በበዓሉ ዋዜማ ካህናቱ በሚያቀርቡት ኅብረ ዜማ ይደምቃል፡፡ ከላሊበላ አቢያተ ክርስቲያናት አንዱ በሆነው በቤተ ማርያምና በዙሪያው ባለው የማሜ ጋራ ዝማሬው በጥንግ ድርብና በጧፍ ታጅቦ ይከበራል፡፡ የሃይማኖት አባቶች እንደሚገልጹት፣ በጋራው ላይ የሚያሸበሽቡት ካህናት የመላዕክት፣ ከጋራው ሥር የሚያሸበሽቡት ካህናት ደግሞ የሰው ልጆች ምሳሌዎች ናቸው፡፡  ኢየሱስ ክርስቶስ በተወለደ ጊዜ ካህናትና ሰዎች በአንድነት ኢየሱስ ክርስቶስን ያመሰገኑበት ምሳሌ መሆኑ፣ በስፋት ይነገራል፡፡ የገና ባህላዊ በዓልነቱ በአብዛኛው በገጠራማው የአገራችን ክፍል የሚስተዋል ቢሆንም የተወሰኑ የባህሉ ቅሪቶች በአንዳንድ ከተሞችም አይጠፉም፡፡ በዓሉን በባህላዊ ጭፈራ፣ በገና ጨዋታ፣ ባህላዊ ልብስ ለብሶ ማክበር የተለመደ ነው፡፡  ‹‹በገና ጨዋታ አይቆጡም ጌታ›› የሚለው ብሂል እንደሚያስረዳው፣ ሁሉም ወጣት ከቤቱ ወጥቶ በሜዳ ላይ ጨዋታ፣ በደስታና በሃሴት ያከብረዋል፡፡ እንደሌሎች በዓላት ሁሉ በገና በዓል ድፎ መጋገር፣ ሰንጋ መጣል፣ ጠጅና ጠላ መጎንጨት የተለመደ ነው፡፡ እንደ ፈረንጆቹ የበዛ ባይሆንም፣ በዚህ ጊዜ ስጦታ መስጠት የበዓሉ ዓቢይ መገለጫ ነው፡፡ ሕግ የኅብረተሰብን ባህላዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ሃይማኖታዊ ትስብር የሚገዛ እንደመሆኑ መጠን እነ

ሲዳማውያን በቅርበት ልከታተሉት የምገባ የመሬት ምዝገባ አዋጅ ጸደቀ፤ ኣዋጁ ኣንድ ወጥየኢኮኖሚ ማኀበረሰብ ለመፍጠር ያለመ ነው ተብሏል

የፍትሕ ሚኒስትሩ የተቃወሙት የመሬት ምዝገባ አዋጅ ይሁንታ ተቀባይነት አገኘ፤ ኣዋጁ ከክልሎች ሥልጣን ጋር የሚጋጭ ይዘት ኣለው   የፌዴሬሽን ምክር ቤት የከተማ መሬት ምዝገባ አዋጅን ለማፅደቅ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀረበለትን የይሁንታ ጥያቄ በፍትሕ ሚኒስትሩና በሌሎች ሁለት አባላት ተቃውሞ አፀደቀ፡፡ የምክር ቤቱ አባል የሆኑት የኦሮሚያ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አብዱላዚዝ አህመድ፦የቀረበው ረቂቅ አዋጅ መሬትን ብቻ መመዝገብ የሚመለከት ሳይሆን፣ ከመሬት ጋር ተያያዥ የሆኑ የማይንቀሳቀሱ ንብረቶችን አብሮ መመዝገብ የሚያካትት በመሆኑና ይህ ደግሞ የፌዴራል መንግሥት ሥልጣን ባለመሆኑ ይሁንታው መጠየቁን ጠቁመዋል፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከከተማ ልማት፣ ቤቶችና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር የቀረበለት የከተማ መሬት ምዝገባ ረቂቅ አዋጅ የተለያዩ አንቀጾች ከክልሎች ሥልጣን ጋር የሚጋጭ ይዘት ያለው በመሆኑና አንድ ወጥ የኢኮኖሚ ማኅበረሰብ ለመፍጠር ሲባል ነው የፌዴሬሽን ምክር ቤትን ይሁንታ የጠየቀው፡፡  ረቂቅ አዋጁ በአገሪቱ ውስጥ በሚገኙ ሁሉም ከተሞች መሬትንና በመሬት ላይ ያሉ ቋሚ ይዞታዎችን የመመዝገብ፣ የባለቤትነት መብትና የመጠቀም መብት ዕውቅናና ዋስትናን የሚሰጥ ነው፡፡ ነገር ግን ሕገ መንግሥቱ መሬትና የተፈጥሮ ሀብቶችን አጠቃቀምና አጠባበቅ የተመለከቱ ሕጐች የማውጣት ሥልጣን ለሕዝብ ተወካዮች ቢሰጥም፣ ክልሎች ደግሞ በፌዴራል መንግሥት የሚወጣውን ሕግ መሠረት በማድረግ የማስተዳደር ሕገ መንግሥታዊ ሥልጣን አላቸው፡፡ የቀረበው የመሬት ምዝገባ ረቂቅ አዋጅ በተወሰነ ሁኔታ የክልሎችን ሥልጣን የሚጋፋ ቢሆንም፣ አንድ ወጥ የኢኮኖሚ ማኅበረሰብን ለመፍጠር እጅግ ጠቃሚ በመሆኑ ይህንን አዋጅ በማፅደቅ ተግባራዊ ለማድረግ ክልሎች የሚወከሉበት

Very Nice Ethiopian music 2013 Teferi Lembo Sidama

Image
Very Nice Ethiopian music 2013 Teferi Lembo Sidama  

ጥቂቶች ሊመነደጉ፤ ብዙዎች አሽቆልቁለዋል

ከአዲሱ ጠ/ሚኒስትር አዲስ ራዕይ እንፈልጋለን “የራበው ሥራ ፈልጐ ማግኘት የማይችልና ልጆቹን ለማስተማር አቅም ያጣ ሰው ከባርነት ነፃ ነው ማለት አይቻልም፡፡” የሚለው የአሜሪካዊው ፕሬዚዳንት ሊንደን ቢ. ጆንሰን ንግግር እውነትነት አሁን አሁን በጆሮዬ መደወሉ ራሴን እያስገረመኝ መጥቷል፡፡ የዛሬ አምስትና ስድስት ዓመት ገደማ ደራሲና ጋዜጠኛ አለማየሁ ገላጋይ፤ ስለኑሮ ውድነት ሲጽፍ ብዙዎቻችን እያነበብን ፈገግ ከማለት በቀር ብዙ ልባችን አልተነካም ነበር፡፡ ምናልባትም በጣም አልፎ አልፎ ከምናነባቸው መጣጥፎች ይልቅ መንግስት ስለ ልማት የሚነፋው ጥሩንባ አደናቁሮን ይሆናል፡፡ አሁን አሁን የመንግሥት መዝገበ ቃላት “ልማት” የሚለው ትርጓሜ ግራ እያጋባን መጥቶ ጭራሽ ወደ ብስጭት የተመነዘረብን ብዙ ነን ብዬ አስባለሁ፡፡ መንግስት ልማት የሚለው ከእኛ አፍ “ቫት” እያለ የሚነጥቃትን ገንዘብ ሰብስቦ ለሌቦች ካጠገበ በኋላ፣ በፍርፋሪዋ የሚሠራትን መንገድና ጤና ጣቢያ ወይም ትምህርት ቤት ነው፡፡ ሌላው ቀርቶ “ኮንደሚኒየም” እየተባሉ የተሠሩት ቤቶች አካባቢ ያለውን ግድየለሽነት ተመልከቱ፡፡ የውሃ መፍሰሻ ቦዮቹ ገና ተሠርተው ሳያልቁ ይፈርሣሉ። ሕንፃው ውስጥ ያሉትን የግብር ይውጣ ሥራዎች ተውአቸው፡፡ ለመሆኑ ልማትና ዕድገት ምንድነው? ወረቀት ላይ የሃሰት ሪፖርቶችን ከምሮ መቀለድ ነው። ቀልድና ውሸትስ እስከ የት ያዘልቀናል? ከወር ወደ ወር ሰዎች በልተው የማደር አቅማቸውን እያጡ፣ ልጆቻቸውን ማስተማር ተራራ መቧጠጥ እየሆነባቸው ሲመጣ --- እንዴት ስለ ዕድገት ይወራል? ጋዜጠኛ መሳይ ካድሬዎች ስለልማትና እድገት ብዙ ቢለፈልፉም ከሕዝቡ የበለጠ ጓዳውን የሚያውቅ ማንም ሊኖር አይችልም፡፡ አለ ቢባልም ከተራ ቀልድነት አያልፍም፡፡ እርግጥ ነው፤ ባለፉት ሃያ ዓመታት ጥቂት

ህገመንግስትን የሚቃረን አንቀጽ ከፀረሙስና አዋጅ እንዲሰረዝ ተወሰነ

የፌዴሬሽን ምክር ቤት በፓርላማ የወጣውን ህግ ሲያሻሽል አሁን የመጀመሪይው ነው፡፡ የቀድሞ መከላከያ ሚኒስትር አቶ ስዬ አብርሃ ተመሳሳይ ጥያቄ አቅርበው ውድቅ ተደርጐባቸው ነበር፡፡  “በሚኒስትር ማዕረግ የገቢዎችና ጉምሩክ ባስልጣን ዋና ዳሬክተር አቶ መላኩ ፈንታ ላይ የቀረበው የሙስና ክስ መታየት ያለበት በከፍተኛ ፍ/ቤት ነው ወይስ በጠቅላይ ፍ/ቤትን” በሚል ለተነሳው ጉዳይ ምላሽ ለመስጠት ለሰዓታት የተከራከሩ የፌደሬሽን ምክር ቤት አባላት፤ የሚኒስትሮች ክስ በጠቅላይ ፍ/ቤት እንዲታይ የሚደነግገው አንቀጽ ከፀረ ሙስና አዋጁ እንዲሰረዝ በ76 የድጋፍና በ8 የተቃውሞ ድምጽ ወሰኑ፡፡  የሙስና ክሶችን በቀዳሚነት የመዳኘት ስልጣን የከፍተኛ ፍ/ቤት እንደሆነ የሚገልፀው የፀረሙስና አዋጅ፣ ሚኒስትሮች ሊከሰሱ ግን በቀጥታ ወደ ጠቅላይ ፍ/ቤት እንደሚቀርብ ይገልፃል፡፡ በ1993 ዓ.ም ኢህአዴግ ውስጥ በተከሰተው ፀብ ከፓርቲው አመራርነት የተባረሩት የቀድሞ መከላከያ ሚኒስትር ስዬ አብርሃ፣ በወቅቱ በሙስና መከሰሳቸው የሚታወቅ ሊሆን፣  ጉዳያቸው በቀጥታ በጠቅላይ ፍ/ቤት እንዲታይ መደረጉን ተቃውመው እንደነበር ይታወሳል፡፡ እንደሌሎች ተከሳሾች የአቶ ስዬ ክስ በከፍተኛ ፍ/ቤት እንዲታይ መከራከሪያ ያቀረቡት ጠበቃ፤ አለበለዚያ ግን ይግባኝ የመጠየቅ የተከሳሽ ህገመንግስታዊ መብትን የሚጥስ ይሆናል ብለዋል፡፡  በፀረ ሙስና አዋጅ የተካተተው አንቀጽ ህገመንግስቱን ስለሚቃረን ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ቀርቦ ውሳኔ እንዲሰጥበት የአቶ ስዬ ጠበቃ ቢከራከሩም፤ ፍ/ቤቱ ጥያቄውን ውድቅ ማድረጉ ይታወሳል፡፡  ጥያቄው እንደገና ፍ/ቤት ውስጥ የተነሳው ከአስር አመታት በኋላ የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ከፍተኛ ሃላፊዎች ላይ ከተመሰረተው ክስ ጋር ተያይዞ ነው፡፡ በአንድ በኩል ዋና ዳሬክተሩ አቶ መላ