Posts

‹‹የፖለቲካ ባህሉ መሠረት እንዲይዝ ብዙ ትግል ይጠይቃል››

Image
አምባሳደር ታዬ አፅቀ ሥላሴ፣ የሕገ መንግሥት አርቃቂ ኮሚሽን አባል የነበሩ አምባሳደር ታዬ አፅቀ ሥላሴ ከሃያ ዘጠኙ የሕገ መንግሥት አርቃቂ ... ኮሚሽን አባላት መካከል አንዱ ናቸው፡፡ ከቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ (የአሁኑ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ) በፖለቲካ ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት በዲግሪ የተመረቁት አምባሳደር ታዬ በሳይንስና ቴክኖሎጂ ኮሚሽን ነበር ሥራ የጀመሩት፡፡ ይሁንና ለበርካታ ዓመታት ያገለገሉት በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ነው፡፡ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ውስጥ ከ20 ዓመታት በላይ በቆየው አገልግሎታቸው በዲፕሎማትነት፣ በቆንስላ ጄነራልነት፣ በአምባሳደርነትና በተለያዩ የሥራ ዘርፎች ውስጥ አገልግለዋል፡፡ በተለያዩ አገሮች ውስጥ በሚገኙ የኢትዮጵያ ኤምባሲዎች ውስጥ የሠሩ ሲሆን ከእነዚህም መካከል ስዊዲንና አሜሪካ ይገኙበታል፡፡ በአሁኑ ጊዜ ደግሞ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአሜሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር በመሆን በማገልገል ላይ ይገኛሉ፡፡  ሰለሞን ጎሹ  የዛሬ 19 ዓመት ኅዳር 29 ቀን 1987 ዓ.ም. ፀድቆ በሥራ ላይ የዋለውን የኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት የማርቀቅ ሒደትና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ አምባሳደር ታዬን አነጋግሯቸዋል፡፡  ሪፖርተር፡- እርስዎ አባል የነበሩበት የሕገ መንግሥት አርቃቂ ኮሚሽን አሁን በሥራ ላይ ያለውን ሕገ መንግሥት በማርቀቁ ሒደት ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል፡፡ የሽግግሩ ዘመን ቻርተር የሽግግር መንግሥቱ ሕገ መንግሥት በማርቀቅ እንደሚያበቃ ይገልጻል፡፡ አጠቃላይ ሒደቱ ምን ይመስል ነበር? አወቃቀሩስ ምን ይመስል ነበር? በማርቀቅ ሒደቱ ተጨማሪ ሚና ከነበራቸው ሌሎች ተቋማት ጋርስ የነበራችሁ ግንኙነት እንዴት ነበር? አምባሳደር ታዬ ፡- የሽግግር መንግሥቱ ዋነኛ ተግባር ሕገ መንግሥት አዘጋጅቶ ሥልጣኑን በሕዝብ ለተመረጠ አካል
Image
አዲስ አበባ ፣ ህዳር 28፣ 2006 ( ኤፍ.ቢ.ሲ ) ትምህርት ሚኒስቴር ለመጀመሪያ ጊዜ በሁሉም ክልልች የሚገኙ 499  የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን የኢንተርኔት ተጠቃሚ ሊያደርግ ነው። በሚኒስቴሩ የትምህርት አይሲቲ ማእከል ሃላፊው ዶክተር ገበየሁ ወርቅነህ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንዳሉት ፥ ሚኒስቴሩ 422 አዳዲስ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርትቤቶችን ደግሞ የፕላዝማ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከኢትዮቴሌኮም ጋር በጋራ እየሰራ ነው ብለዋል። የኢንተርኔት አገልግሎቱ  ፕላዝማው  የመቋረጥ እድል ቢያጋጥመው እንኳን  ተማሪዎቹ ከትምህርት ሚኒስቴር ዋናው ማእከል የሚተላለፈውን ትምህርት በአማራጭነት እንዲከታተሉበት ታሳቢ ያደረገ ነው። ኢትዮ ቴሌ ኮም በክልሎች የሚሸፈን ቢሆንም ለፕላዝማዎቹ 78 ሚሊየን እንዲሁም ለኢንተርኔት አገልግሎቱ ደግሞ 2 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር  ውለታ ገብቷል። በኢትዮቴሌኮም የኮርፖሬት ኮሚኒኬሽን ስራ አስኪያጅ አቶ አብዱራሂም አህመድ የፕላዝማውም ይሁን የኢንተርኔት አገልግሎቱ  ከግማሽ በላይ መከናወኑን ነው የተናገሩት።

ከሞጆ ሀዋሳ ለሚገነባው መንገድ የአፍሪካ ልማት ባንክ የ2.4 ቢልዮን ብር ሰጠ

Image
ከሞጆ ሀዋሳ ለሚገነባው አውራ መንገድ ከአፍሪካ ልማት ባንክ 2.4 ቢልዮን ብር በላይ ብድርና እርዳታ መገኘቱን የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ገለፀ፡፡ ከሞጆ ሀዋሳ ለሚገነባው አውራ መንገድ  የ2.4 ቢልዮን ብር  በላይ  ብድርና ስጦታ ስምምነ ቱ የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚንስትር አቶ ሶፊያን አህመድ ና  የአፍሪካ ልማት ባንክ ተጠሪ ሚስ ጆሰፊን ንጉር ጋር ዛሬ ህዳር 27/2006   ተፈራርመዋል፡፡ የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚንስትር አቶ ሶፊያን አህመድ እንዳሉት ከአፍሪካ ልማት ባንክ ጋር የተፈረመው ስምምነት ኢትዮጵያ ለጀመረችው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ጉዞ አካል ለሆነው የመንገድ ልማት የሚውል ነው፡፡ አቶ ሶፍያን እንዳሉት በኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ባለቤትነት የሚገነባው የሀዋሳ ሞጆ መንገድ ወጭው ከአፍሪካ ልማት ባንክና ከኮሪያው ኤግዚም ባንክ በተገኘ የገንዘብ ድጋፍና በመንግስት የሚሸፈን ይሆናል፡፡ የመንገድ ፕሮጀክት ስራው ሲጠናቀቅ ወደ ደቡባዊ የሀገሪ ቱ ክፍል የሚደረገው የንግድና ኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ የሚደግፍ ይሆናል ም  ብለዋል፡፡ የአፍሪካ ልማት ባንክም ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን አጋርነት አጠናክሮ እንደሚቀጥል እምነታቸው መሆኑንም ሚንስትሩ ገልፀዋል፡፡ የአፍሪካ ልማት ባንክ ተጠሪ ሚስ ጆሰፊን ንጉር በበኩላቸው  ከአፍሪካ ልማት ባንክ ተጠቃሚ የአፍሪካ ሀገራት ኢትዮጵያ ግንባር ቀደ ም  መሆኗን አስታውሰው በቀጣይም ባንኩ የኢትዮጵያን የልማት ጉዞ እንደሚደግፍ አረጋግጠዋል፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ዛይድ ወ/ገብርኤል ስምምነቱ  በሁለት ክፍሎች ለሚገነባው 201 ኪሎ ሜትሮችን ለሚሸፍነውና በአንድ ጊዜ 6 መኪኖችን ማሳለፍ የሚችለው ዘመናዊ የሞጆ ሞያሌ አውራ መንገድ አ

US urged to tighten message on human rights abuses

Image
Human rights activists Wednesday urged the US government to be more consistent in its approach toward repressive regimes, warning that muddled responses sent the wrong message to democracy campaigners. America's over-arching focus on security concerns and the fight against terrorism is obscuring the need to hold governments accountable for rights abuses, activists said at the start of a two-day seminar organized by the Washington-based group Human Rights First. One delegate, Nadine Wahab, said US policy after the coup in Egypt, including a partial freeze in military aid which has halted delivery of large weapons systems but does not bar other arms, was part of the problem. "When funding... continues to go to the weapons that attack and create human rights violations, like tear gas and bullets, but you hold the F-16s, the message that's going to these governments and going to human rights defenders is that human rights is not important," said Wahab, an expert

የመስቀል በዓል በአለም ቅርስነት ተመዘገበ፤ የሲዳማ ፍቼ በኣልስ?

አዲስ አበባ ህዳር26/2006 ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በማይዳሰስና በማይጨበጥ ቅርስነት የመስቀል በዓልን በዓለም ቅርስነት አስመዘገበች፡፡ የቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮናስ ደስታ ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ በአዘርባጃን ዋና ከተማ ባኩ በተደረገው ስምንተኛው የተባበሩት መንግስታት የሳይንስ የትምህርትና ባህል ማዕከል/ዩኔስኮ/ ኢንታጀብል ባህላዊ ቅርሶች ጉባኤ የመስቀል በዓል በአለም ቅርስነት ተመዝግቧል። ይህም ኢትዮጵያ ለመጀመሪያው ጊዜ በአለም አቀፍ ደረጃ በማይዳሰሱ ባህላዊ ቅርሶች ያስመዘገበችው ሲሆን አገሪቱ በአጠቃላይ በዩኔስኮ በተባባሩት መንግስታት የሳይንሰና የባህል ማዕከል ያስመዘገበቻቸው ቅርሶች ብዛት አስር አድርሶታል። በጉባኤውም በአለም አቀፍ ለመመዝገብ ከቀረቡ 31 የማይዳሰሱና የማይጨበጡ ቅርሶች መካከል የመስቀል በዓል አንዱ ሆኖ መመረጡ ዋና ዳይሬክተሩ ተናግረዋል። የመስቀል በዓል ሃይማኖታዊ መሆኑ ቢታወቅም በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች በየራሳቸው ባህል፣ ትውፊትና እምነት አካሄድ የሚከበር ሲሆን በሰሜን የአገሪቱ ክፍሎች መንፈሳዊ ይዘቱ እንደሚያመዝን ተናግረዋል። በበዓሉ ተለያይተው የሚኖሩ የቤተሰብ አባላት የሚገናኙበትና ማህበራዊ ችግሮቻቸውን የሚፈቱበት፣ ወጣቶች ለጋብቻ የሚዘጋጁበትና የተጣሉ ሰዎች የሚታረቁበት በመሆኑ ከሀይማኖታዊ ትርጉሙ በሻገር የመተሳሰብ የወዳጅነት መንፈስ የሚጎለብትበት መሆኑን ተናግረዋል። ቅርሱ በአለም አቀፍ ቅርስነት መመዝገቡ ዓለማቀፍ እውቅናን ከማበርከቱ ባሻገር፣ የቱርስት መስህብነቱ ይጨምራል፣ ቅርሱ ከቀድሞ በተለየ አለማቀፍ ጥበቃ ይደረግለታል፣ ቅርሱ ባሕላዊ ይዘቱን ጠብቆና የማንነት መገለጫ ሆኖ ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲተላለፍ ያደርጋል ብለዋል። በተጨማሪም በአለም አቀፍ ደረጃ ቅርሱ እውቅና በ