የመስቀል በዓል በአለም ቅርስነት ተመዘገበ፤ የሲዳማ ፍቼ በኣልስ?
አዲስ አበባ ህዳር26/2006 ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በማይዳሰስና በማይጨበጥ ቅርስነት የመስቀል በዓልን በዓለም ቅርስነት አስመዘገበች፡፡ የቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮናስ ደስታ ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ በአዘርባጃን ዋና ከተማ ባኩ በተደረገው ስምንተኛው የተባበሩት መንግስታት የሳይንስ የትምህርትና ባህል ማዕከል/ዩኔስኮ/ ኢንታጀብል ባህላዊ ቅርሶች ጉባኤ የመስቀል በዓል በአለም ቅርስነት ተመዝግቧል። ይህም ኢትዮጵያ ለመጀመሪያው ጊዜ በአለም አቀፍ ደረጃ በማይዳሰሱ ባህላዊ ቅርሶች ያስመዘገበችው ሲሆን አገሪቱ በአጠቃላይ በዩኔስኮ በተባባሩት መንግስታት የሳይንሰና የባህል ማዕከል ያስመዘገበቻቸው ቅርሶች ብዛት አስር አድርሶታል። በጉባኤውም በአለም አቀፍ ለመመዝገብ ከቀረቡ 31 የማይዳሰሱና የማይጨበጡ ቅርሶች መካከል የመስቀል በዓል አንዱ ሆኖ መመረጡ ዋና ዳይሬክተሩ ተናግረዋል። የመስቀል በዓል ሃይማኖታዊ መሆኑ ቢታወቅም በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች በየራሳቸው ባህል፣ ትውፊትና እምነት አካሄድ የሚከበር ሲሆን በሰሜን የአገሪቱ ክፍሎች መንፈሳዊ ይዘቱ እንደሚያመዝን ተናግረዋል። በበዓሉ ተለያይተው የሚኖሩ የቤተሰብ አባላት የሚገናኙበትና ማህበራዊ ችግሮቻቸውን የሚፈቱበት፣ ወጣቶች ለጋብቻ የሚዘጋጁበትና የተጣሉ ሰዎች የሚታረቁበት በመሆኑ ከሀይማኖታዊ ትርጉሙ በሻገር የመተሳሰብ የወዳጅነት መንፈስ የሚጎለብትበት መሆኑን ተናግረዋል። ቅርሱ በአለም አቀፍ ቅርስነት መመዝገቡ ዓለማቀፍ እውቅናን ከማበርከቱ ባሻገር፣ የቱርስት መስህብነቱ ይጨምራል፣ ቅርሱ ከቀድሞ በተለየ አለማቀፍ ጥበቃ ይደረግለታል፣ ቅርሱ ባሕላዊ ይዘቱን ጠብቆና የማንነት መገለጫ ሆኖ ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲተላለፍ ያደርጋል ብለዋል። በተጨማሪም በአለም አቀፍ ደረጃ ቅርሱ እውቅና በ