Posts

ሃዋሳ፦የመናፈሻ ፓርክ ብርቅ የሆነባት ከተማ

Image
ሃዋሳ ከተማ የሲዳማ መናገሻ በኣለማችን ላይ በርካታ ዘመናዊ ከተሞች በተለይ በኣሁኑ ጊዜ ከኣለም የኣየር ሙቀት ጋር ተያይዞ ብሎም ለከተሞቹ ውበት እና ለከተሞቹ ነዋሪዎች ምቾት ሲባል በርካታ የመናፈሻ ፓርኮችን እየገነቡ እና ለኣገልግሎት እያበቁ ይገኛሉ። መናፈሻ ፓርኮች በከተሞች መኖራቸው የከተሞቹ ነዋሪዎች በእረፊት ጊዚያቸው ንጽህ ኣየር እየተነፈሱ ኣልያም በለምለም ዞፎች መካከል እየተንሸራሸሩ ጊዚያቸውን እንድያሳልፉ ያስችላቸዋል። ለኣብነት ያህል ኣብዛኛውቹ የደቡብ ኣሜሪካ ኣገራት ከተሞች ማለትም ከትናንሾቹ እንስቶ እስከ ሜክስኮ ሲቲ እና የብራዚሏን ሳኦፖሎን የመሳሰሉ ትላልቅ ከተሞች እያንዳንዱ የከተሞቹ መንደረ በፕላዛ ወይም በግሪንኤሪያ የተሞሉ ናቸው። እነዚህ ፓርኮች በከተሞቹ ነዋሪዎች ተሞልተው ይውላሉ። ፓርኮቹ የተለያዩ የስፖርት ማዘወተሪያ ማዕከላትን የያዙ በመሆናቸው በርካታ ወጣቶች ጊዚያቸውን ኣልባለ ቦታ ከማሳለፍ በተለያዩ ስፖርታዊ ክንውኖች ላይ እንዲያሳልፉ ኣስችሏቸዋል። በደቡብ ኣሜሪካ የከተሞች ውበት የምለካውም በያዙት ፓርኮች እና በፓርኮቹ ውበት ነው። በርግጥ የከተሞቹ ውበት እና ንጽህና የነዋሪዎቹን ስልጣነ ያሳያል። የሰሜን ኣሜሪካ ወይም የኣውሮፓ ከተሞችንም ሲንመለከት በውብ ፓርኮች የተሞሉ ናቸው። የየከተሞቹ ኣስተዳደር ለፖርኮች ግንባታ ከፍተኛ ትኩረት ስጥተው ይሰራል። ነዋሪዎችን ከየከተሞቹ ኣስተዳደር በላይ ለፓርኮቹ ውብ እና ንጽህ መሆን የበኩላቸውን ይወጣሉ። ከኣውሮፓ እና ከደቡብ ኣሜሪካ ከተሞች ፊታችንን ወደእኛዋ ከተማ ስንመልስ ሌላ ታሪክ ነው የምናየው። የሲዳማዋ ዋና ከተማ ሃዋሳ ከሊባኖስ ተነስቶ እስከ ሞዛሚብክ ለምዘንቀው ታላቁ ስምጥ ሸለቆ እምብርት ላይ የምትገኝ ከመሆኗ የተነሳ ሞቃት ኣየር ኣመቱን ሙሉ

የሲዳማ ቡና ኣምራቾች የተሳተፉበት በቡና ጥራት ላይ የምመክር ጉባኤ ሰሞኑን በሃዋሳ ከተማ ተካሄደ

Image
ሲዳም ቡና በወኢኔ በጉባኤው ላይ የንግድ ሚኒስትሩ አቶ ከበደ ጫኔ እና የደቡብ ክልል ኣዲሱ ፕሬዚዳንት ካላ ደሴ ዳልኬን ጨምሮ ጉዳዩ የምመለከታቸው ከፍተኛ ባለስልጣናት ተገኝተዋል። ከሃዋሳ ያገኘነው መረጃ እንደምያሳየው ፤ኣገሪቱ ዘንድሮ ከ 277 ሺህ ቶን በላይ ቡና ለውጪ ገበያ በማቅረብ ከአንድ ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ለማግኘት አቅዳ ለች ለዚህም ደቡብ ክልል ጨምሮ በየክክሉ የሚመረተው ቡና ጥራትና ደረጃውን ጠብቆ በብዛት መቅረብ ኣለበት ተብሏል ። እንደ ኢዜኣ ዘጋባ ፤ የንግድ ሚኒስትሩ አቶ ከበደ ጫኔ ከሲዳማ እና ከሌሎች በደቡብ ክልል ቡና አምራች ዞኖችና ልዩ ወረዳ አመራሮች ጋር ትናንት በሀዋሳ ባደረጉት ውይይት ላይ እንዳሉት ሚኒስቴር መሰሪያ ቤቱ ዘንድሮ ለውጪ ገበያ ከሚያቀርባቸው የኤክስፖርት ሰብሎች ከ 5 ነጥብ 6 ቢሊዮን ዶላር በላይ ለማግኘት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው ብለዋል ። ኣክለውም ከግብርና ምርት፣ ከማኑፋክቸሪንግና ከማዕድን ዘርፎች ለመሰብሰብ ካቀደው የውጪ ምንዛሪ ውስጥ 90 በመቶ ከግብርና ምርቶች የሚገኝ መሆኑን ጠቁመው ከዚህ ውስጥ ቡና ከፍተኛውን ድርሻ እንደምይዝ ኣብራሪተዋል ። በ 2004 ዓ . ም 169 ሺህ ቶን የታጠበና ደረቅ ቡና ለውጪ ገበያ በመላክ 832 ሚሊዮን ዶላር በ 2005 ዓ . ም ከቀዳሚው ዓመት በ 30 ቶን ብልጫ ያለው ቡና የቀረበ ቢሆንም በቡና ዋጋ መቀነስ ምክንያት 740 ሚሊዮን ዶላር እንደተገኘ ገልፀዋል፡፡ ዘንድሮ ቡናን በብዛት በመላክ ገቢውን ለማሳደግ ትኩረት መሰጠቱን አስታውቀዋል። በደቡብ ክልል ከፍተኛ በቡና የተሸፈነ ማሳ ያለ ቢሆንም በአቅርቦት ማነስና በጥራት መጓደል ምክንያት የሚጠበቀውን ያህል ገቢ ማግኘት ሳይቻል እንደቆየና ይህን የአቅርቦት ውስንነትና ጥራት መጓደል በማስቀ

በቅርቡ ከሲዳማ ዞን ዋና ኣስተዳዳሪነት ወደ ክልል ትምህርት ቢሮ ሃላፊነት የተዛወሩት ካላ ሚሊዮን ማቴዎስ በ19ኛው የአጠቃላይ ትምህርት ጉባኤ ላይ ሪፖርት በማቅረብ ስራ ጀምረዋል

Image
በደቡብ ክልል ባለፉት ሁለት ዓመታት ለትምህርት ቤቶች የተመደበው የድጎማ በጀት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርጓል   ሃዋሳ ጥቅምት 25/2006 ለትምህርት ቤቶች የተመደበው የድጎማ በጀት ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ የደቡብ ክልል ትምህርት ቢሮ አስታወቀ፡፡ በክልሉ ባለፉት ሁለት ዓመታት በመንግስትና በባለድርሻ አካላት ድጋፍ ለትምህርት ቤቶች ድጎማ የሚውል ከ564 ሚሊዮን ብር በላይ መመደቡ ተመልክቷል፡፡ የቢሮው ኃላፊ አቶ ሚሊዮን ማቴዎስ ሰሞኑን በ19ኛው የአጠቃላይ ትምህርት ጉባኤ ባቀረቡት ሪፖርት እንደገለጹት የትምህርት ስራ በተደራጀ የህዝብ ንቅናቄ በተለይም በትምህርት ተቋማት በተደራጁ የልማት ሰራዊት፣ በፖለቲካ አመራር፣ በትምህርት ባለሙያዎች እንዲሁም በመላው ህብረተሰብ ሁለንተናዊ ንቅናቄና በፍጹም ባለቤትነት ለመምራት የበጀት ድጋፉ ያበረከተው አስተዋጽኦ ቁልፍ ነበር፡፡ ባለፉት ሁለት ዓመታት ለድጎማ የዋለው በጀት መጠን 564 ሚሊዮን 861 ሺህ 714 ብር መሆኑንና ከፍተኛ መሻሻል ማሳየቱን በመግለፅ ለአንድ ተማሪ የሚሰጠውን የድጎማ መጠን ከ20 እስከ 25 ብር የነበረው ከ80 በላይ እንዲያድግ እድርጎታል ብለዋል፡፡ በስራ ላይ እንዲውል በተደረገው በዚህ በጀት በየትምህርት ቤቶቹ አጠቃላይ የትምህርት ጥራት ማረጋገጫ ፓኬጅ መርሀ ግብሮችን ለማሳለጥ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ኃላፊው አብራርተዋል፡፡ የድጎማ በጀቱ የየትምህርት ቤቱን የበጀት እጥረት ችግር ሙሉ በሙሉ እንደማይቀርፍ በመገንዘብ ትምህርት ቤቶችና ቀበሌዎች ህብረተሰቡን በማሳተፍ ለትምህረት ቤቶች መሻሻልና ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ እያደረጉ ያለው ድጋፍ እጅግ አበረታች በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል፡፡ ከመንግስ

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከሁለት ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የማስፋፊያ ግንባታዎችን እያካሄደ ነው

Image
ሐዋሳ ጥቅምት 23/2006 የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎችን የቅበላ አቅም ለማሳደግ ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የማስፋፊያ ግንባታዎችን እያካሄደ መሆኑን ገለጸ። የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዮሴፍ ማሞ እንደገለጹት ይርጋለም ፣ ሀዋሳና ወንዶ ገነት በሚገኙ ካምፓሶች የሚካሄዱት የማስፋፊያ ግንባታዎቹ በ2007 የትምህርት ዘመን በመደበኛ ፕሮግራም የሚቀበሏቸው ተማሪዎች ቁጥር 30 ሺህ ለማድረስ ያስችላቸዋል፡፡ ከማስፋፊያ ግንባታዎቹ መካከል የመማሪያ ክፍሎች ፣ቤተ ሙከራዎች ፣የተማሪዎች ማደሪያና ቤተ መጽሀፍት እንዲሁም ለኢንጅነሪንግ ተማሪዎች የተግባር መለማመጃዎች ያሉት የቴክኖሎጂ ተቋም ዋና ዋናዎች መሆናቸውን አስረድተዋል። በተለይ የቴክኖሎጂ ተቋሙ በሁለት ምዕራፍ ተከፋፍሎ የመጀመሪያው ግንባታ የመማሪያ ክፍሎች ፣አዳራሾች ቤተሙከራዎች ፣ቢሮዎች የመመገቢያ አዳራሾችና ሌሎች አገልግሎት መስጫ ማዕከላትን አካቶ መያዙን ዶክተር ዮሴፍ አመልክተዋል። ሁለተኛው ምዕራፍ ደግሞ የተማሪዎች ማደሪያ ፣ የመመገቢያ አደራሽ ፣የቴክኖሎጂ ቤተ ሙከራዎች እንደሚገኙበት ጠቁመው ሁሉም ግንባታዎች አካል ጉዳተኞችን ግምት ውስጥ ያስገባና ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑን ተናግረዋል። መንግስት በመደበው ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የሚገነቡት እነዚህ ማስፋፊያዎች ዘንድሮ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ለማዘጋጀት ስራቸው በመፋጠን ላይ እንደሚገኝ ዶ/ር ዮሴፍ አስታውቀዋል። የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በተያዘው ዓመት 5400 አዲስ መደበኛ ተማሪዎችን ተቀብሎ በተለያዩ መስኮች ማስተማር እንደሚጀምርና በአሁኑ ወቅት ከ30ሺህ በላይ ተማሪዎች በመደበኛ፣ በማታና በተከታተይ የትምህርት ፕሮግራሞች እያሰለጠነ መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል። http://www.ena.gov.et/Story.aspx?ID=13163&K=1

የሲዳማ ዞን መንግስት ለዞኑ ቡና ነጋዴዎች የገንዘብ ብድር ሊያመቻች ይገባል ተባለ

Image
በሲዳማ ወቅቱ የቡና ነው፤ በርካታ የቡና ንግድ እንቅስቃሴ የምታይበት ጊዜ ነው። የሲዳማ ቡና ኣምራቾች በቡና ምርታቸው ገንዘብ የሚያገኙበት እና ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት የምልኩበት፤ ለቤተሰቦቻቸው የሚያስፈልጋቸውን ቁሳቁሶች ጨምሮ ማንኛውንም ኣቅም የፈቀደውን ለማድረግ የገንዘብ ኣቅም የሚኖራቸውን ወቅት ነው። ሆኖም ኣንድችግር ኣለ ይላል የጥቻ ወራና ዘገባ፤ ይሄውም የቡና ዋና ካለፈው ኣመት ኣንጻር ስነጻጸር በመውረዱ ነው። ለቡና ዋጋ መውረድ እንደምክንያት ከምነሱት ጉዳዮ ኣንደኛው የቡና ነጋደዎች በብዛት ወደ ቡና ንግዱ ኣለመግባታቸው ሲሆን፤ ለዚህም ቢሆን ምክንያቱ ባንኮች ብድር ባለመልቀቃቸው ነው ተብሏል። እንደ ዘገባው ከሆነ፤ባንኮቹ ለሲዳማ ቡና ነጋዴዎች ብድር ለመገደባቸውም እንደምክንያት የሚያነሱት ባለፈው ኣመት ለነጋደዎቹ ያበደሯቸውን ገንዘብ በገቡት ውል መሰረት በወቅቱ ባለመመለሳቸው ነው። በዚህ በሲዳማ ውስጥ ከፍተኛ የገበያ ልውውጥ በምካሄድበት በዚህ ወቅት ባንኮች ብድር መገደባቸው እና ማዘገየታቸው ብዙዎችን ነጋዴዎችን ያዛዘነ ጉዳይ ሲሆን፤ የዞኑ መንግስት በጉዳዩ ላይ ጠልቃ በመግባት መፍትሄ ከመፈለግ ይልቅ በዝምታ ማየቱ ኣነጋጋሪ ሆኗል። ሆኖም ሰሞኑን ባንኮች ለኣንዳንድ የቡና ነጋደዎች ትንሽ ገንዘብ ማበደራቸውን ለማወቅ የተቻለ ሲሆን ብድሩን ያገኙትም በመንግስት ልማታዊ ባለሃብት የምባሉት መሆናቸው ታውቋል። ዘንድሮ ቡና ኣምራች ኣርሶ ኣደሮችን ኣንድኪሎ ቡና በስድስት ብር ከሃምሳ ሳንቲም በመሸጥ ላይ ቢሆኑም በቡና ዋና ደስተኞች ኣለመሆናቸውን በመናገር ላይ ሲሆኑ እንደምክንያት የሚያነሱትም ባለፈው ኣመት በተመሳሳይ ወቅት ኣንድ ኪሎ ቡና ከስምንት ብር እስከ ኣስራ ሁለት ብር የሸጡ በመሆኑ እና ዘንድሮ