Posts

የፍቼ ጫምባላላ በዓል የሲዳማ ብቻ ሳይሆን የዓለም ቅርስ ሊሆን ይገባል፤

Image
የሲዳማ ዞን ከምድር ወገብ በስተሰሜን አካባቢ ይገኛል። በሰሜናዊ ምስራቅና በደቡባዊ ምስራቅ የኦሮሚያ ክልል በደቡብ ጌዲኦ ዞንና የኦሮሚያ ክልል፣ በምእራብ በኩል ደግሞ የወላይታ ዞን ያዋስኑታል። ዞኑ በሶስት የአየር ንብረቶች የሚካተት ሲሆን  30 በመቶ ደጋ፣  60  በመቶ ወይና ደጋ፣ 10  በመቶ በቆላ ይሸፈናል። የዞኑ አጠቃላይ የቆዳ ስፋት  7 ሺ  200  ካሬ ኪሎ ሜትር ሲሆን በ 19  የገጠር ወረዳዎችና በሁለት የከተማ አስተዳደሮች የተዋቀረ ነው። በ 1999  ዓ . ም በተካሄደው የህዝብና የቤቶች ቆጠራ መሰረት በዞኑ የሚገኘው የሲዳማ ህዝብ ብዛት  3 ነጥብ 2 ሚሊዮን እንደሚሆን ተገምቷል። የሲዳማ ብሄር በሰሜናዊ ምስራቅ አፍሪካ ከሚገኙ የኩሽ ቋንቋ ተናጋሪዎች መካከል ተጠቃሽ ሲሆን በደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል ከሚገኙ ዞኖች አንዱ ነው። የሲዳማ ብሄር የራሱ የሆነ የጊዜ አቆጣጠር ቀመር ያለው ሲሆን ቀመሩን ተከትሎ የፍቼ የዘመን መለወጫ በዓል በድምቅት ይከበራል። የፍቼ በዓል የሚከበርበትን ቀን  « አያንቶ » ( የተመረጡ አዛውንቶች )  ክዋክብት በጨረቃ ዙሪያ የሚያደርጉትን ኡደት በመቃኘት ይወስናሉ። በጎሳ መሪው  ( ሞቴው )  ውሳኔ መሰረት የበዓሉ ቀን ከታወጀ በኋላ ሁሉም በየፊናው ዝግጅቱን ያጧጡፋል። በዓሉም እስከ ሁለት ሳምንታት ለሚደርስ ጊዜ በየአካባቢው በሚገኙ  « ጉዱማይሌዎች » ( አደባባዮች )  በድምቀት ይከበራል። ጉዱማይሌ በዞኑ በሚገኙ መንደራት ሁሉ የሚገኝ ሲሆን ትልቅ ክብር የሚሰጠው ቦታ ነው። አራስ የመታረሻ ጊዜዋ አብቅቶ ከመውጣቷ በፊት ከልጇ ጋር በቅድሚያ የምታየው ጉዱማይሌውን ነው። ሙሽሮች ከሰርጋቸው ማግስት ጀምሮ ጉዱማይሌን ሳያዩ ወደአዲሱ ኑሯቸው አይቀላቀሉም። የሲዳማ ብሄር ተወላጆች እንደየእድሜያቸውና በ

ሥራችሁም እንደ አፋችሁ ይሁን!

Image
የሕገ መንግሥቱን የበላይነት በሚመለከት ሰሞኑን ጠቃሚና ዓበይት ቃላት ከባለሥልጣናት አንደበት ሲነገሩ እየተደመጡ ናቸው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ኢሕአዴግና የኢሕአዴግ ባለሥልጣናት ሕገ መንግሥቱን በማክበር አርዓያ መሆን አለባቸው ብለዋል፡፡ ፓርላማውም ይህን መቆጣጠር አለበት በማለት በአፅንኦት ሲገልጹ ተደምጠዋል፡፡  የመንግሥት መሪና ሥልጣን የያዘው ገዥ ፓርቲ ሊቀመንበር እንደመሆናቸው መጠን፣ እንደ ፓርቲም እንደ መንግሥትም ሕገ መንግሥቱን እናክብር ቁጥጥር ሊደረግብንም ይገባል ማለታቸው ጎሽ! የሚያሰኝ ነው፡፡  የተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አቶ አባዱላ ገመዳም ተመሳሳይ አፅንኦት ሰጥተዋል፡፡ ፓርላማው ሕገ መንግሥቱ መከበሩን ሊቆጣጠር ይገባል ብለዋል፡፡ ኢሕአዴግ እንደ ገዥ ፓርቲና እንደ መንግሥት መሪ በአርዓያነት ሕገ መንግሥቱን ሊተገብር ይገባል፣ ለሕጎች ተገዥ መሆን አለበት፡፡ ይህንን በተግባር ለመተርጎም የሚያዳግተው አይሆንም፣ አርዓያም ይሁን በማለት በአፅንኦት ገልጸዋል፡፡  የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አቶ ካሳ ተክለ ብርሃንም በቅርቡ ከመገናኛ ብዙኃን ጋር ልዩ ስብሰባ እንዲዘጋጅ በማድረግ ለሁለት ቀናት በተደረገ ውይይት በአፅንኦት ያነሱት ጉዳይ አለ፡፡ መገናኛ ብዙኃን ስለሕገ መንግሥቱ ኅብረተሰቡን ማስተማር እንዳለባቸውና የፌዴሬሽን ምክር ቤት ሕገ መንግሥቱን የማስተግበር የበላይ ኃላፊነት የተሰጠው ስለሆነ፣ በቅርብ እየተገናኙ ስህተትንና ጉድለትን እያሳዩ ሥራቸውን መወጣት አለባቸው ብለዋል፡፡ በተግባር ሥራ ላይ ያልዋለ ሕገ መንግሥት ሊያስከትለው የሚችለውን አደጋም አስረድተዋል፡፡ በአጭሩ  ሲታይ ከመንግሥት መሪ፣ ከገዥው ፓርቲ ኃላፊ፣ ከተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባዔና ከፌዴሬሽን ምክር አፈ ጉባዔ ሕገ መን

ጥቂት ስለ ሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ

Image
ሲዳማ ቡና  ሙሉ ስም ፡  ሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ  ምስረታ ፡  1999 ስታዲየም ፡   ይርጋለም ስታዲየም  ሀዋሳ ስታዲየም የክለቡ የወቅቱ አሰልጣኝ ፡  ታረቀኝ አሰፋ   ዳኜ ክለቡ ያገኛቸው ክብሮች ፡  የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሊግ ሻምፒዮን 2001 ሲዳማ ቡና በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ እየተሳተፈ ያለ ክለብ ነው፡፡ ክለቡ ከተመሰረተ ጥቂት አመታት ብቻ ቢቆጠሩም በብሔራዊ ሊግ ሻምፒዮን ሆኗል፡፡ በፕሚየርሊጉም ጥሩ ተፎካካሪ እየሆነ ይገኛል፡፡ ምስረታ  ሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ የተመሰረተው በ 1999 ዓ/ም ነበር በደቡብ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ላይ ሲዳማ ዞንን በመወከል ሥስት ክለቦች ይሳተፋሉ ከእነዚህ ውስጥ አንዱ ዳራ ከነማ ነበር፡፡ ዳራ በውድድሩ ለፍፃሜ በመድረስ ውጤታማ ይሆናል፡፡ ይህም ክልሉን በመወከል ሀዋሳ ላይ ወደተካሄደው የኢትዮጵያ የክልል ክለቦች ሻምፒዮና ከተሳተፉ አራት ቡድኖች አንዱ ለመሆን አበቃው፡፡ በዚህ ውድድር ቀዳሚዎቹን አራት ደረጃዎች የሚይዙ ቡድኖች ወደ ብሔራዊ ሊግ ሲያልፉ ዳራም ሦስተኛ ደረጃን አግኝቶ ስለነበር ብሔራዊ ሊጉን ተቀላቀለ፡፡ እናም ዳራ ከተማን ብቻ ይወክል የነበረው ክለብ መላውን የሲዳማ ዞንን እንዲወከል በማሰብ ሲዳማ የሚለውን ስያሜ አገኘ፡፡ ሲዳማ ቡና በብሔራዊ ሊግ ሲዳማ ቡና ሁለት አመት በብሔራዊ ሊግ አሳልፏል፡፡ በመጀመሪያው አመት ቆይታው በ 2000 አራተኛ ደረጃን ይዞ ነው ያጠናቀቀው፡፡ በሁለተኛው አመት 2001 ውድድሩ በሁለት ምድብ ተከፍሎ ሲካሔድ በምድብ ሁለት የነበረው ሲዳማ በመጨረሻው ጨዋታ ከአየር ሀይል ጋር ያለ ግብ በመለያየት ከምድቡ ከሜታ አቦ ቢራ ቀጥሎ ሁለተኛ ደረጃን አግኝቷል፡፡ በዚህ ጨዋታ ቢሸነፍ ኖሮ ይህን ደረጃ አያገኝም፡፡ በቀጣይ

በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የመክፈቻ ጫዎታ ሲዳማ ቡና ከኢትዮጵያ መድህን በመጫዎት ላይ ናቸው

Image
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ2006 ዓ/ም የጨዋታ መርሃ ግብር በመጪው ቅዳሜ ጥቅምት 16/2006 ዓ/ም በአዲስ አበባና በክልል ከተሞች በሚካሄዱ 5 ጨዋታዎች ይጀመራል፡፡ በፕሪሚየር ሊጉ የመጀመሪያ ጨዋታ የተገናኙትና በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የደደቢትና የኢትዮጵያ ቡና ጨዋታ ህዳር 7 ዋሊያዎቹ ከናይጀሪያ ጋር ላለባቸው ወሳኝ ጨዋታ ተጫዋቾች ለብሔራዊ ቡድን በመጠራታቸው እንደተራዘመ ታውቋል፡፡ ከ10 በላይ ተጨዋቾችን ለዋሊያዎቹ ዝግጅት የተነጠቀው ቅዱስ ጊዮርጊስም ቅዳሜ ከሙገር ሲሚቶ ጋር የሚኖረው ጨዋታ ተራዝሟል፡፡ ፕሪሚየር ሊጉን በዚህ ዓመት የተቀላቀለው ዳሽን ቢራ በሜዳው ሐረር ቢራን የሚያስተናግድ ሲሆን እንደ ዳሽን ሁሉ በዚህ ዓመት ሊጉን የተቀላቀለው ወላይታ ዲቻ አዲስ አበባ ላይ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን ይገጥማል፡፡ መብራት ሃይል በበኩሉ ወደ ሃዋሳ በማቅናት ሃዋሳ ከነማን እሁድ ሲገጥም መከላከያ ሲዳማ ቡናን እንዲሁም ኢትዮጵያ መድህን አርባ ምንጭን የሚያሰተናግዱበት ጨዋታ በመጀመሪያው ሳምንት ይጠበቃል፡፡ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ባለፈው ዓመት የተከሰተው የጨዋታዎች መቆራረጥ በዚህ ዓመትም ሊቀጥል እንደሚችል ቢሰጋም የውድድር መርሃ ግብሩ የተዘጋጀው እነዚን ውድድሮች ከግምት በማስገባት መሆኑን ፌደሬሽኑ ገልጿል፡፡ በውድድር ዓመቱ ዋሊያዎቹ የዓለም ዋንጫ የመጨረሻ ማጣሪያን ጨምሮ ለቻን አፍሪካ እንዲሁም ለሴካፋ የሚሳተፉ ይሆናል፡፡

ኣንድ ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ሁለተኛ ጋዜጣ ክስ ተመሰረተበት _ ሃዋሳ ዩኒቨርስቲ በ“ኢትዮ ምህዳር” ላይ የ300ሺ ብር ክስ አቀረበ

Image
ሃዋሳ ዩኒቨርስቲ በ“ኢትዮ ምህዳር” ላይ የ300ሺ ብር ክስ አቀረበ ዩኒቨርሲቲው ቀደም ሲል “አዲስ አድማስ”ን መክሰሱ ይታወቃል የ“ሪፖርተር” ጋዜጣ ዋና አዘጋጅም ታስሮ ወደ ሃዋሳ ተወስዶ ነበር   “ኢትዮ ምህዳር” ጋዜጣ “የሃዋሳ ዩኒቨርስቲ የማኔጅመንት አባል በሙስና እጅ ከፍንጅ ተያዘ” በሚል ርዕስ ካወጣው ዜና ጋር በተያያዘ ስሜ ጠፍቷል በማለት 300ሺ ብር ካሳ እንዲከፈለው ዩኒቨርስቲው ክስ ያቀረበ ሲሆን፣ ፍ/ቤት ብይን ለመስጠት ለሚቀጥለው ረቡዕ ቀጠሮ ሰጠ፡፡  የጋዜጣው አሳታሚ፣ ዋና አዘጋጅ እና ስራ አስኪያጅ እያንዳንዳቸው 100ሺ ብር ካሳ ሊከፍሉኝ ይገባል በማለት ዩኒቨርስቲው ክስ ያቀረበው፣ በሃዋሳ ለሚገኘው የሲዳማ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ሲሆን ተከሳሾቹ ሰኞ እለት የመቃወሚያ መልስ አቅርበዋል፡፡ በእለቱ ያስከስሳል ወይስ አያስከስስም የሚል ብይን እንዲሰጥላቸው ተከሳሾቹ ቢጠይቁም፣ ዩኒቨርስቲው “የመልስ መልስ ለመስጠት ጊዜ ይሰጠኝ” በማለቱ ለሚቀጥለው ረቡዕ ተቀጥሯል፡፡ “ኢትዮ ምህዳር” ጋዜጣ በፊት ለፊት ገፁ ላይ “የሃዋሣ ዩኒቨርስቲ የማናጅመንት አባል በሙስና እጅ ከፍንጅ ተያዙ” የሚል ዜና ያወጣው ሰኔ 19 ቀን 2005 ዓ.ም ሲሆን፣ የዩኒቨርስቲው የፍትሐ ብሄር ክስ በካሳ ጥያቄ ላይ ያተኮረ ሆኗል። ዜናው ታትሞ በተሰራጨበት ወቅት ዩኒቨርስቲው በደብዳቤው ምላሽ ሰጥቶ እንደነበር ይታወሳል፡፡ ዩኒቨርስቲው ለጋዜጣው ዝግጅት ክፍል በላከው ደብዳቤ፣ የሙስና ወንጀል መፈፀሙን እንዳልካደ የጋዜጣው ዋና አዘጋጅ አስታወሰው፤ “በሙስና የተያዘው ግለሰብ የማናጅመንት አባል ሳይሆን የቡድን መሪ ስለሆነ ማረሚያ እንድታወጡ” የሚል ደብዳቤ ነው የደረሰን ብሏል፡፡ ይህንንም ማረሚያ በጋዜጣችን አስተናግደናል ብሏል - ዋና አዘጋጁ፡፡ ቀደም ሲል ዩኒቨርስቲ