Posts

ከቱሪስት ከተማነት እስከ ታላላቅ የስፖርት ውድድሮች መናኸሪያነት_ሀዋሳ

Image
ከሃምሳ ዓመት በላይ ያስቆጠረችው የደቡብ ክልል መዲና ሐዋሳ ከኢትዮጵያ ከተሞች በቁንጅናዋ፣ በዕቅድ ከመከተሟም ጋር ተዛምዶ ለብዙ ነገር ትመረጣለች፡፡ ከቱሪስት ከተማነት እስከ ታላላቅ የስፖርት ውድድሮች መናኸሪያነት ትታጫለች፡፡  አትሌት ኃይሌ ገብረ ሥላሴ በሐዋሳ ስሙን መትከል የፈለገው በቢዝነስ ሥራ ብቻ አይደለም፡፡ በታላቁ ሩጫ ዓመት ጠብቆ የሚጐበኛትን የደቡብ መናገሻ፣ አሁን ደግሞ ለአገሪቱ የመጀመሪያ የሆነውን ማራቶን መሽቀዳደሚያ አውራና ተመራጭ አድርጓታል፡፡  ኃይሌ በሐዋሳ ያልተለመደውንና በስሙ የተሰየመውን የማራቶን ውድድር በከፍተኛ የገንዘብ ሽልማት አንበሽብሾታል፡፡ በሁለቱም ጾታ አሸናፊዎቹ እያንዳንዳቸው የ100 ሺሕ ብር ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡  የመጀመሪያው ‹‹ኃይሌ ማራቶን›› ጥቅምት 10 ቀን 2006 ዓ.ም. በደቡቧ መናገሻ ሐዋሳ እንደሚደረግ ይፋ በሆነ በጥቂት ወራት ከ16 አገሮች ከ200 በላይ ተሳታፊዎች በውድድሩ ለመሳተፍ ቅድመ ምዝገባ ማከናወናቸውን የገለፀው ዝግጅት ክፍሉ፣ በሚቀጥለው ዓመት ከተወዳዳሪ ቁጥር ጀምሮ የተሻለና ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ለማድረግ አበረታች ተሞክሮ ተገኝቷል ብሏል፡፡  በአገሪቱ ለታላላቅ አትሌቶች መገናኛ እንደሆነ የሚነገርለት ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ፣ በ10 ሺሕ ተሳታፊዎች ጀምሮ በአሁኑ ወቅት በተመሳሳይ የሩጫ ውድድሮች ከዓለም ምርጥ አሥሩ አንዱ ለመሆን በቅቷል፡፡ ዘንድሮም 37 ሺሕ ተሳታፊዎች ለማወዳደር ዝግጅቱን አጠናቆ እንደሚገኝ መገለጹ ይታወሳል፡፡ ውድድሩ ከአዲስ አበባ አልፎ በመላ አገሪቱ የተለያዩ ከተሞች ተወዳጅና ተናፋቂ እስከመሆን ደርሷል፡፡  42 ኪሎ ሜትር 195 ሜትር የሚሸፍነው ማራቶን በአውሮፓና በሌሎች ታላላቅ አገሮች ካልሆነ እንዲህ እንደ አሁኑ በኢትዮጵያ ይደረጋል

ኣንድ የሲዳማ ወጣት ከድህነት ተላቀቀ፤በዕድል ሎተሪ ኣንደኛ ዕጣ ኣሸናፊ በመሆን 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር ባለቤት ሆነ

Image
ነዋሪነቱ በኣለታ ወንዶ ከተማ የሆነው ወጣት ከፈለኝ ሞገስ በኣንድ ሆቴል ውስጥ በስጋ ቆራጭነት ይተዳደር የነበረ ሲሆን፤ የዕድል ሎተሪ ኣንደኛ ዕጣ ኣሸናፊ በመሆን 1 ሚሊዮን ሁለት መቶ ሺ ብር ቼክ ከብሄራዊ ሎተሪ ኣስተዳደሪ እጅ ተረክቧል። ወጣቱ በስነስርዓቱ ላይ ያሸነፈውን ገንዘብ ሳያባክን በሃዋሳ ከተማ ሆቴል ለመክፈት ማቀዱን ተናግሯል። የወራንቻ ኢንፎርሜሽን ኔትዎርክ ወጣት ከፈለኝን እንኳን ደስ ኣለህ ማለት ይወዳል።

“የሚፈልጉት የእምነት ቃል ነው” ማሰቃየት እና ጎጂ አያያዝ በኢትዮጵያ ማዕከላዊ ፖሊስ ጣቢያ

Image
የሪፖርቱ ይዘት ባጭሩ  አንዱ (ፖሊስ) በያዘው ረዥም ጥቁር ዱላ ከኋላ ጭንቅላቴን መታኝ ከዚያ አይኔን በጨርቅ  አሰረኝ፤ በመቀጠል ወደ ቢሯቸው ወሰዱኝ፤ ይህንን ያደረጉት መርማሪዎቹ ናቸው…ደጋግመው  በጥፊ መቱኝ፡፡ የምነግራቸውን ለመስማት መርማሪዎቹ ዝግጁ አይደሉም፤ በጥቁሩ ዱላ እና  በጥፊ ደግመው መቱኝ። እዚያው ክፍል እስከ እኩለ ሌሊት ድረስ አቆዩኝ፤ በጣም ተዳክሜ  ነበር። ከዚያ ወደ ታሰርኩበት ክፍል መለሱኝ እና ሌላ ሰው ወሰዱ፡፡ በሁለተኛው ቀን  ምርመራ ድብደባው የባሰ ነበር። የሚፈልጉት ጥፋተኛ ነኝ ብየ እንዳምን ነው ፡፡  በ2003ዓ.ም ዓመት አጋማሽ ማዕከላዊ ታስሮ የነበረ ጋዜጠኛ - ናይሮቢ፣ ሚያዚያ 2004ዓ.ም  በኢትዮጵያ ዋና ከተማ አዲስ አበባ መሃል ከአንድ ሆቴል እና አንድ የኦርቶዶክስ ቤቴክርስቲያን አጠገብ በመላ ሃገሪቱ በጣም  ታዋቂ የሆነ አንድ ፖሊስ ጣቢያ ይገኛል።ይህም የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ዘርፍ ሲሆን በተለምዶ ማዕከላዊ  በመባል ይታወቃል። ተቃዋሚ ፖለቲከኞች፣ ጋዜጠኞች፣ የተቃውሞ ሰልፍ አደራጆች፣ በብሄር የተደራጁ አማፅያንን  ይደግፋሉ የሚባሉ ሰዎች እና ሌሎችም በርካታ የኢትዮጵያ የፖለቲካ እስረኞች ሲያዙ በቅድሚያ የሚወሰዱት ወደ ማዕከላዊ  ነው፡፡ ማዕከላዊ ከገቡ በኋላ ምርመራ ይካሄድባቸዋል። በአብዛኞቹ ላይ ደግሞ ሁሉም ዓይነት እንግልት እና በደል  የሚደርስባቸው ሲሆን ይህም ማሰቃየትን ይጨምራል፡፡  በማዕከላዊ የሚገኙት መርማሪ ፖሊሶች ታሳሪዎች ጥፋታቸውን እንዲያምኑ፣ እንዲናገሩ ወይም ሌላ መረጃ እንዲያወጡ  የሚያደርጉት በሃይል የማስፈራራት መንገድን በመጠቀም ሲሆን ይህም እስከ ማሰቃየት እና ሌላ ጎጂ አያያዝ እስከ መፈጸም  ይደርሳል፡፡ አብዛኛውን ጊዜ እስረኞ

አዲሱ የጉድጓድ ውሃ መቆፈሪያ ቴክኖሎጂ እና በሲዳማ ዞን ሁላ ወረዳ ነዋሪ የሆነው የአቶ በቀለ ፉኤ ታሪክ

Image
አዲሱ የጉድጓድ ውሃ መቆፈሪያ ቴክኖሎጂ -ለመጠጥ ውሃ አቅርቦት ተደራሽነት አዲሱ የጉድጓድ ውሃ መቆፈሪያ ቴክኖሎጂ  50  ሜትር ጥልቀት ድረስ መቆፈር የሚያስችል ነው፤ ኑሮውን በውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ ሥራ ላይ ያደረገው የ 42  ዓመቱ አቶ በቀለ ፉኤ በሕይወት ዘመኑ በርካታ ነገሮችን አይቷል። በተለይም ከሥራው ጋር በተያያዘ ብዙ ፈተና አሳልፏል። ወገቡን በገመድ ታስሮ ቁልቁል የጉድጓድ ውሃ ሲቆፈር መሬት ተደርምሶ አፈር ተጭኖት በሰዎች ዕርዳታ ከሞት ተርፏል። ጥልቀት ያለው ጉድጓድ ቆፍሮ ውስጥ እንዳለ አየር አጥሮት ራሱን ስቷል። ወገቡን ታስሮ ቁልቁል የተላከበት ገመድ ተበጥሶ ሕይወቱ አደጋ ላይ ወድቋል። በደቡብ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልላዊ መንግሥት ሲዳማ ዞን ሁላ ወረዳ ነዋሪ የሆነው አቶ በቀለ እንጀራ ሆኖበት እንጂ የጉድጓድ ውሃ ቁፋሮ ሥራው በሞትና በሕይወት መካከል ያለ ነገር እንደሆነ ያምናል። የእለት ጉርሱን ከመሙላት አልፎ ቤተሰቡን የሚያስተዳድረው በእዚህ ሕይወትን የሚፈትን ሥራ ላይ ተሰማርቶ ነው። ሥራውን ለመተው ፍላጐት አለው። በርካታ ጊዜም የጉድጓድ ውሃ ቁፋሮ ሥራ እንዲሠራላቸው ጥያቄ ያቀረቡለትን ደንበኞቹን ጥያቄ ሳይቀበልም ቀርቷል።  « የጉድጓድ ውሃ የሚቆፍሩ አባቶች ልጆቻቸውን ስመው ነው ቁፋሮ የሚጀምሩት። እኔም ልጆቼን ስሜ ተሰናብቼ ብዙ ጊዜ ሥራዬን ጀምሬያለሁ። ፈተና እያለፍኩ እዚህ ደርሻለሁ። አሁን እግዚአብሄር የተመሰገነ ይሁን ለእጅ ውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ ወደጉድጓድ መግባት ቀርቶልኛል » ሲል ይናገራል። አሁን የአቶ በቀለ ሥራ አስጊነት ምን ዋስትና አግኝቶ ነው በቀለ ለአምላኩ ምሥጋናውን ለማቅረብ የበቃው ?  ብለን ስንጠይቅ ቀላል በሆነ ቴክኖሎጂ በእጅ የሚሠራ የውሃ ጉድጓድ ለመቆፈር የሚያስችል መሣሪያ በመፈጠሩ ነው።

በሃዋሳ ስም የተሰዬመችው የኢትዮጵያ ንግድ መርከብ በቅርብ ወራት ውስጥ ነዳጅ መጫን ትጀምራለች

Image
Ethiopia: New Ethiopian Ships to Carry Petroleum in Early 2014 The Ethiopian Shipping Lines & Logistics Service Enterprise's (ESLSE) two new petroleum carrying ships will finally go into business in early 2014. This comes after a year of carrying other goods, pending a deal to be concluded with the Ethiopian Petroleum Enterprise (EPE). To date, petroleum suppliers in the Gulf were also responsible for transporting the product. As the current contract is now approaching its closing date, the EPE has told these suppliers to make their new offers excluding transport, said Abayneh Awol, fuel supply manager at the EPE. These companies include - Kuwait Independent Petroleum Corporation and the Saudi-based Bekri International Petroleum. The Sudanese Petroleum Corporation supplies an overland transport service. The shipping enterprise ordered a total of nine vessels fromChina, at a total cost of 300 million dollars, in 2010. They have already received eight of them, with the