Posts

አዲሱ የጉድጓድ ውሃ መቆፈሪያ ቴክኖሎጂ እና በሲዳማ ዞን ሁላ ወረዳ ነዋሪ የሆነው የአቶ በቀለ ፉኤ ታሪክ

Image
አዲሱ የጉድጓድ ውሃ መቆፈሪያ ቴክኖሎጂ -ለመጠጥ ውሃ አቅርቦት ተደራሽነት አዲሱ የጉድጓድ ውሃ መቆፈሪያ ቴክኖሎጂ  50  ሜትር ጥልቀት ድረስ መቆፈር የሚያስችል ነው፤ ኑሮውን በውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ ሥራ ላይ ያደረገው የ 42  ዓመቱ አቶ በቀለ ፉኤ በሕይወት ዘመኑ በርካታ ነገሮችን አይቷል። በተለይም ከሥራው ጋር በተያያዘ ብዙ ፈተና አሳልፏል። ወገቡን በገመድ ታስሮ ቁልቁል የጉድጓድ ውሃ ሲቆፈር መሬት ተደርምሶ አፈር ተጭኖት በሰዎች ዕርዳታ ከሞት ተርፏል። ጥልቀት ያለው ጉድጓድ ቆፍሮ ውስጥ እንዳለ አየር አጥሮት ራሱን ስቷል። ወገቡን ታስሮ ቁልቁል የተላከበት ገመድ ተበጥሶ ሕይወቱ አደጋ ላይ ወድቋል። በደቡብ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልላዊ መንግሥት ሲዳማ ዞን ሁላ ወረዳ ነዋሪ የሆነው አቶ በቀለ እንጀራ ሆኖበት እንጂ የጉድጓድ ውሃ ቁፋሮ ሥራው በሞትና በሕይወት መካከል ያለ ነገር እንደሆነ ያምናል። የእለት ጉርሱን ከመሙላት አልፎ ቤተሰቡን የሚያስተዳድረው በእዚህ ሕይወትን የሚፈትን ሥራ ላይ ተሰማርቶ ነው። ሥራውን ለመተው ፍላጐት አለው። በርካታ ጊዜም የጉድጓድ ውሃ ቁፋሮ ሥራ እንዲሠራላቸው ጥያቄ ያቀረቡለትን ደንበኞቹን ጥያቄ ሳይቀበልም ቀርቷል።  « የጉድጓድ ውሃ የሚቆፍሩ አባቶች ልጆቻቸውን ስመው ነው ቁፋሮ የሚጀምሩት። እኔም ልጆቼን ስሜ ተሰናብቼ ብዙ ጊዜ ሥራዬን ጀምሬያለሁ። ፈተና እያለፍኩ እዚህ ደርሻለሁ። አሁን እግዚአብሄር የተመሰገነ ይሁን ለእጅ ውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ ወደጉድጓድ መግባት ቀርቶልኛል » ሲል ይናገራል። አሁን የአቶ በቀለ ሥራ አስጊነት ምን ዋስትና አግኝቶ ነው በቀለ ለአምላኩ ምሥጋናውን ለማቅረብ የበቃው ?  ብለን ስንጠይቅ ቀላል በሆነ ቴክኖሎጂ በእጅ የሚሠራ የውሃ ጉድጓድ ለመቆፈር የሚያስችል መሣሪያ በመፈጠሩ ነው።

በሃዋሳ ስም የተሰዬመችው የኢትዮጵያ ንግድ መርከብ በቅርብ ወራት ውስጥ ነዳጅ መጫን ትጀምራለች

Image
Ethiopia: New Ethiopian Ships to Carry Petroleum in Early 2014 The Ethiopian Shipping Lines & Logistics Service Enterprise's (ESLSE) two new petroleum carrying ships will finally go into business in early 2014. This comes after a year of carrying other goods, pending a deal to be concluded with the Ethiopian Petroleum Enterprise (EPE). To date, petroleum suppliers in the Gulf were also responsible for transporting the product. As the current contract is now approaching its closing date, the EPE has told these suppliers to make their new offers excluding transport, said Abayneh Awol, fuel supply manager at the EPE. These companies include - Kuwait Independent Petroleum Corporation and the Saudi-based Bekri International Petroleum. The Sudanese Petroleum Corporation supplies an overland transport service. The shipping enterprise ordered a total of nine vessels fromChina, at a total cost of 300 million dollars, in 2010. They have already received eight of them, with the

Ethiopia's first marathon draws crowds to 'land of runners'

Image
Photo from  http://sports.yahoo.com/news/ethiopias-first-marathon-draws-crowds-land-runners-165923969--spt.html   HAWASSA: The sun had barely risen but the cool morning air was buzzing with excitement: 350 participants had gathered in Ethiopia, the land of runners, for the country's first international marathon organised by athletics legend Haile Gebrselassie.  Sunday's race, which drew 150 elite Ethiopian athletes and about 150 foreign "fun runners", promises to boost professionalism in a country that has produced scores of world-class runners, many of whom started running barefoot along dusty country roads.  "Believe me, we can produce more big names, we can produce more marathon runners, more Olympic champions, world champion and world record holders," said Gebrselassie, two-time marathon record-breaker and 10,000 Olympic champion.  Race organisers sought to draw Ethiopia's top athletes to the race in Hawassa, 275 kilometres (170 miles) south o

በኣገሪቱ ከፍተኛ ወታደራዊ እርከኖች ላይ የሲዳማ ብሄር ተወላጆች ኣሉ?

Image
Photo from Internet እንደምታወቀው የሲዳማ ህዝብ ካለው ከፍተኛ የህዝብ ብዛት የተነሳ በተለያዩ ጊዜያት በኣገሪቱ ህዝባዊ ስራዊት ውስጥ እየተመለመለ በፍቃደኝነት የሰራዊቱ ኣባል የምሆነው የሲዳማ ተወላጆች ቁጥር ከፍተኛ ነው። ሲዳማውያን በኣገሪቱ ጦር ሰራዊት በብዛት ከመሳተፍ ባለፈ በተለያዩ የጦር ሜዳ ውጊያዎችን ኣኩር ድሎችን በማስመዝገብ ዝና የተረፉ ናቸው። ሲዳማውያን የኣገሪቱን ህገመንግስት በመጠበቅ ብሎም የኣገሪቱን ሎዕላዊነት በማስከበር ለህገመንግስቱ መከበር ያላቸውን የማወላዳ ኣቋም በተለያዩ ጊዚያት ኣሳይተዋል። ነገር ግን ባለፉት ኣንድ መቶ  ኣመታት ሲዳማዎች በኣገሪቱ ጦር ሰራዊት ውስጥ ያለ ማቋረጥ የተሳተፉ ሆኖ ሳለ በከፍተኛ ወታደራዊ ማዕረግ ወይም በከፍተኛ ወታደራዊ ኣመራርነት ስማቸው የምጠቀሱ ሲዳማዎች ብዙ ኣይደሉም ምክንያቱ ምን ይሁን?ለኣብነት ያህል በኣጭር ጊዜ ውስጥ በተደጋጋሚ የኣገሪቱ መንግስት ለከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖች ከፍተኛ ወታደራዊ ሹመቶችን መስጠቱ የምታወስ ሲሆን፤ በእነዚህ ከፍተኛ ወታደራዊ ሹመቶች ውስጥ ምን ያህል የሲዳማ ተወላጅ ተካተው ይሁን ? መረጃው ያላችው ጀባ በሉን።

ከሀዋሳ ዲላ ያለው መንገድ ስራ እስኪጠናቀቅ ነሪዎች ትብብር እንዲያደርጉ ጥሪ ቀረበ

Image
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 8፣ 2006 (ኤፍ ቢ ሲ)  ከሀዋሳ ዲላ ያለው መንገድ ርዝመቱ 90 ኪሎ ሜትር ይደርሳል ። ይህ መንገድ ከተማዎቹን አቋርጠው ለሚወጡ የንግድና የማህበራዊ አገልግሎቶች ከፍተኛ ደርሻ አለው። መንገዱ ረዘም ላለ አመታት ያገለገለና ጠንካራ ጥገናም ያልተደረገለት ነው። አሁን ላይ መንገዱ ለረጅም ጊዜ ከማገልገሉ ጋር ተያይዞ አገልግሎት መስጠት የማይችለበት ደረጃ ላይ መድረሱን በመንገዱ የሚገለገሉ ሰዎች ይናገራሉ። የአካባቢው ነዋሪዎች መንገዱን ለዚህ ያደረሰው አልፎ አልፎ  የሚደረግለት  መጠነኛ ጥገና በመቋረጡ  ባጠቃላይ ለአንቅስቃሴ አስቸግሯል ባይ ናቸው። አንዳንዴ ለመኪኖች የርእስ በእርስ ግጭትም ምክንያት መሆኑን ነዋሪዎቹ ይናገራሉ። ከዚህ ባለፈም የመንገዱ ምቹ አለመሆን የተሽከርካሪ እቃዎች ላይ የሚያደርሰው ችግርን የከፋ አድርጎታል። ባለንብረቶችም ይህም  ያሳሰበ ጉዳይ ሆኖብናል እናም የሚመለከተው አካል መፍትሄ እንዲሰጠው ይላሉ። በኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር  አቶ ሳምሶን ወንድሙ  እንደሚሉት ከሀዋሳ በሀገረ ማርያም እስከሞያሌ የሚደርስ መንገድ አለ። ይህ መንገድ ደግሞ በስድስት ኮንትራክተሮች ተከፋፍሎ የሚሰራ ሲሆን አሁን ቅሬታ የተነሳበት ከሀዋሳ እስከ ዲላ ያለው መንገድም  ከሀዋሳ ሀገረ ማርያም በሚደርሰው የመንገድ ከፍል ግንባታው በያዝነው አመት የተጀመረ ነው ይላሉ። በርግጥ አሁን ከሀዋሳ እስከዲላ ያለው መንገድ ረዘም ላሉ አመታት የአገልግሎት የሰጠ መሆኑን የሚያስታውሱት አቶ ሳምሶን ይህ ደግሞ መንገዱ አሁን መስጠት የሚገባውን አገልግሎት እንዳይሰጥ አድርጎታል ባይ ናቸው። በመሆኑም በነዋሪው የሚነሳው ቅሬታ ተገቢ መሆኑ ላይ ይስማማሉ። አቶ ሳምሶን  ይህ መንገድ ከፍተ