Posts

የጠቅላይ ሚኒስትሩ የሰልፍ ክልከላ ቀጭን መስመር

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ መስከረም 24 ቀን 2006 ዓ.ም. ከጋዜጠኞች ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ለሁለተኛ ጊዜ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በበርካታ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ገለጻ ያደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች ሰልፍ የማድረግ ሕገ መንግሥታዊ መብት ዙሪያ የሰጡት ምላሽ ግን አነጋጋሪ ሆኗል፡፡  የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ ኤልሳቤጥ እቁባይ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ያቀረበችው ጥያቄ የሚከተለው ነበር፡- ‹‹የትግል እንቅስቃሴአቸውን አገር ውስጥ እያደረጉ ያሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች በተለያዩ ጊዜዎች በተለያዩ ከተማዎች ከመንግሥት ምላሽ ይፈልጋሉ ባሏቸው ጉዳዮች ላይ ሰላማዊ ሰልፎችን አድርገዋል፡፡ ምንም እንኳን ሰልፎቹን አስመልክቶ በመንግሥት ኮሚኒኬሽን በኩል የተሰጡ መግለጫዎች ቢኖሩም ሰላማዊ ሰልፉ ላይ ከቀረቡ ጥያቄዎች ‹ምላሽ ያሻቸዋል፣ አግባብነት አላቸው› ብለው መንግስትም በተለያየ መንገድ ከሚሰበስባቸው መረጃዎች የወሰዷቸው ጥያቄዎች አሉ ወይ››  ለጥያቄው በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተሰጠው ምላሽ ለብዙዎች የሚያረካ ነበር ለማለት ያስቸግራል፡፡ ይልቁንም ምላሹ ሌሎች ተጨማሪ በርካታ ጥያቄዎችን አስነስቷል፡፡ በመልሳቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግ ሕገ መንግሥታዊ መብት መሆኑን፣ መንግሥታቸው በጫና ሐሳቡን የሚቀይር እንዳልሆነ፣ ተመሳሳይ ጥያቄዎች በተደጋጋሚ ከተጠየቁ መንግሥት አንድ ቦታ ላይ እንደሚያቆመው፣ የፓርቲዎች መብዛት ሰልፉን እንዳበዛው፣ ሰልፉ የሚታወቀው ውጭ ባሉ የእቅዱ ባለቤቶች እንደሆነ ገልፀዋል፡፡  ሰላማዊ ሰልፍ እንደ ሕገ መንግሥታዊ መብት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ‹‹ተቃዋሚዎች ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግ ሕገ መንግሥታዊ መብታቸው ነው፡፡ ሕገ መንግሥቱ የሰጣቸው መብት እንጂ ማንም በችሮታ የሰጣቸው

መልካም ኢድ_ኣል ኣድሃ ኣረፋ

Image
New

ለኢሕአዴግ ካድሬዎች ማሠልጠኛ ማዕከል አራት ምክትል ዳይሬክተሮች በሚኒስትር ኤዴታ ማዕረግ ተሾሙ

Image
የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር ኢሕአዴግ ካድሬዎች ለሚሠለጥኑበት ማዕከል በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ አራት ምክትል ዳይሬክተሮች ተሾሙ፡፡ የኢሕአዴግ ማሠልጠኛ ማዕከል በሚኒስትር ማዕረግ ዋና ዳይሬክተር የሆኑት አቶ አዲሱ ለገሰ ናቸው፡፡ ከአቶ አዲሱ ሥር አራት ክንፎችን ይዘው እንዲመሩ የተሾሙት ከኢሕአዴግ መሥራች ድርጅቶች የተወከሉ አመራሮች ናቸው፡፡ ከብአዴን አቶ ለገሰ ቱሉ፣ ከደሕዴን አቶ ወንድሙ ገዛኸኝ፣ ከሕወሓት አቶ ነጋ በርሄ ሲሆኑ፣ ከኦሕዴድ የተወከለው አመራር እስካሁን አልታወቀም፡፡  ማሠልጠኛ ማዕከሉ እስካሁን በስድስት ዙሮች በርካታ ካድሬዎችን አሠልጥኗል፡፡ እነዚህ ካድሬዎች ከሥልጠና በኋላ በመንግሥትና በፓርቲ መዋቅሮች ውስጥ በተለያዩ የአመራር ደረጃዎች ላይ ይመደባሉ፡፡  ምንጮች እንደገለጹት፣ ሥልጠና ማዕከሉ ከሚያተኩርባቸው የሥልጠና ዘርፎች መካከል የአምስት ዓመቱ የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ፣ የኢትዮጵያ ህዳሴና የኢሕአዴግ ታሪክ ተጠቃሾች ናቸው፡፡  ምንጮች ኢሕአዴግ በ2007 ዓ.ም ለሚካሄደው ምርጫና መንግሥት የጀመራቸውን የልማት ሥራዎች እንዲሁም መልካም አስተዳደርን የሚያሰፍኑና ሙስናን የሚዋጉ አመራሮችን ለማፍራት ዕቅድ ነድፏል ይላሉ፡፡ ይህንን ለማሳካት በአቶ አዲሱ ለገሰ በሚመራው የኢሕአዴግ ማሠልጠኛ ተቋም ላይ ከፍተኛ ኃላፊነት ተጥሏል፡፡ በዚህ ማሠልጠኛ ውስጥ የሚያልፉ ካድሬዎች የፓርቲያቸውን ዕቅድ የማሳካት ብቃት ይኖራቸዋል ተብሏል፡፡  ኢሕአዴግ በአሁኑ ወቅት የካድሬዎች ሥልጠናን አጠናክሮ ለመቀጠል የማሠልጠኛ ማዕከል ግንባታ በማካሄድ ላይ ይገኛል፡፡ ከዚህ የሥልጠና ማዕከል በተጨማሪ አራት ኪሎ አካባቢ ለሚገነባው የኢሕአዴግ ዋና የፖለቲካ ማዘዣ ጣቢያ ከ130 ሚሊዮን ብር በላይ ያስፈልጋል፡፡ ለ

Ethiopia Ranks 33rd Out of 52 in 2013 Ibrahim Index of African Governance

PRESS RELEASE London —  Since 2000, Ethiopia has progressed most in the category Human Development The 2013 Ibrahim Index of African Governance (IIAG), released today , shows that Ethiopia ranks 33rd out of 52 African countries. The 2013 IIAG provides full details of Ethiopia's performance across four categories of governance: Safety & Rule of Law , Participation & Human Rights , Sustainable Economic Opportunity and Human Development. Since 2000, Ethiopia has shown its biggest improvement in the category Human Development. Human Development measures welfare, education, and health . The 2013 IIAG shows that 94% of Africans including those in Ethiopia live in a country that has experienced overall governance improvement since 2000. The 6% of people living in a country that has experienced governance deterioration since 2000 are based in Madagascar, Eritrea, Guinea Bissau, Somalia, Libya and Mali. Despite improvements since 2000, Ethiopia's governance score

Ethiopia: Bombing Kills 2 in Ethiopian Capital

Ethiopian state media have reported that a bomb blast in the capital city Addis Ababa has killed at least two people. The attack took place Sunday in the city's Bole district, which is home to a large Somali population. There was no immediate claim of responsibility for the bombing, but Ethiopia says it has thwarted plots of attacks in the past two years and blames rebel groups based in the south and southeast, as well as Somalia's al-Shabab insurgents. Ethiopian troops have been fighting al-Qaida-linked al-Shabab militants in Somalia since 2011, alongside African Union forces from Uganda, Burundi and Kenya. Last month, al-Shabab led an attack on a shopping mall in Kenya in which at least 67 people were killed. The al-Qaida-linked group said the attack was retaliation for Kenya's military intervention in Somalia. http://allafrica.com/stories/201310140116.html