Posts

ሳውዝ ስታር ኢንተርናሽናል ሆቴል-የሀዋሳ ፈርጥ

Image
  ለግንባታው 246 ሚ. ብር ወጥቷል  የኦሎምክፒክ ደረጃ ያለው መዋኛ፣ ሲኒማ ቤቶች፣ ናይት ክለብ … ይገነባሉ  8 ሰዎች የሚይዘው ጃኩዚ ውሃ የማያበላሸው LCD ቲቪ አለው ሳውዝ ስታር ኢንተርናሽናል ሆቴል በደቡብ ኢትዮጵያ ከአዲስ አበባ 275 ኪ.ሜ ላይ በሀዋሳ ከተማ ተገንብቶ በቅርቡ ሥራ የጀመረ አዲስ ዘመናዊ ሆቴል ነው፡፡ “ሀዋሳ፣ የቱሪስት መዳረሻ እየሆነች ነው፡፡ የውጭ አገርና የአገር ውስጥ ቱሪስቶች፣ በግል፣ በቡድን፣ በቤተሰብ የሚመጡባት ከተማ ሆናለች፡፡ እንግዶቻችን ሲመጡ የሚያርፉበት ብቻ ሳይሆን፣ በቆይታቸው የሚዝናኑበትና የተሟላ ምቾት የሚያገኙበት ዘመናዊ ሆቴል አዘጋጅተን እየጠበቅናቸው ነው” ይላሉ፤ የሳውዝ ስታር ኢንተርናሽናል ሆቴል ባለቤት ተወካይ አቶ መኳንንት አሰፋ፡፡   “በአካባቢያችን ከሚገኙ ሆቴሎች የምንለይበት ብዙ ነገሮች አሉ፡፡ 4 ባር እና 4 ሬስቶራንቶች የተለያየ መጠቀሚያ ዕቃዎችና (ፋሲሊቲ) ዋጋ ያላቸው 5 ዓይነት መኝታ ክፍሎች፣ … አሉን፡፡ ስለዚህ እንግዳው ሳውዝ ስታር ኢንተርናሽናል ሆቴል ገባ ማለት፣ በፈለገው ቦታ፣ በፈለገው ሁኔታ መዝናናት፣ በፈለገው ደረጃና ዋጋ ክፍሎችን መያዝ ይችላል፡፡   “ለምሳሌ ስታንዳርድ፣ ትዊን፣ ፋሚሊ፣ ዴሉክስ፣ ኤግዚኩቲቭ ዴሉክስ ሱት ቤድሩም፣ የተሰኙ ክፍሎች አሉን፡፡ እንግዳው እንደአቅሙ መከራየት እንዲችል አማራጮች ቀርበውለታል፡፡ ከቁርስ እስከ እራት የሚስተናገድበት ኦል ዴይ ሬስቶራንት አለ፡፡ በቡድን (ግሩፕ) የሚመጡ ሰዎች እየተወያዩ ምሳም ሆነ እራት የሚበሉበት ፕራይቬት ዳይንግ ሩም፣ ቡና ለመጀመሪያ ጊዜ በተገኘባት ስፍራ ማንኪራ የተሰየመ ማንኪራ ጋርደን ካፌ፣ አናት (ቴራስ) ላይ እስከ 200 ሰዎች መያዝ የሚችል ሬስቶራንት አለን፡፡   “አራተኛ ፎቅ ላይ ታቦር ተራራን፣ ቅ

የሪፖርተር ጋዜጣ አዘጋጅ አዋሳ ተወስዶ ታሰሮ ተፈታ _ የክልሉ መንግስት ሚዲያን በተመለከተ ስሱ ሆኖ ይሁን?

በተለያዩ ኣጋጣሚዎች ሚዲያዎች በየትኛውም ኣገር የተሳሳተ ዜና ይዘው ልወጡ ይችላሉ፤ መቼም ሰዎች ነንና ስህተት ኣይጣፋም። ለዚህም ይመስላል በጋዜጠኝነት ስራ ላይ ይህን መሰል ስህተት ስፈጠር ጋዜጣው ወይም ዜናውን ያሰራጨው ሚዲያ ዘጋባው ስህተት መሆኑን ከተቀበለ በተመሳሳይ የጋዜጣው ኣምድ ላይ ለምሳሌ የተሳሳተ መረጃ በዜና መልክ ተሰራጭቶ  ከሆነ በዜና ኣምዱ ላይ የተሰራጨው ዜና ስህተት መሆኑን ገልጾ፤ ማረሚያ  መስጠት ያስፈልጋል።በዚህ ነገሩ ይቋጫል። እንግድህ በሪፖርተር ጋዜጣ ላይ “በደቡብ ክልል ሶስት ምክትል ርዕሳነ መስተዳድሮች ከስልጣናቸው ተነሱ” በሚል ከወጣው ዘገባ ጋር ተያይዞ ጋዜጣው ዘገባው ስህተት መሆኑን ኣምኖ ማስተካከያ የሰጠ ቢሆንም ሰሞኑን የጋዜጣው ማኔጂን ኤዲተር ከአዲስ አበባ ወደ አዋሳ ተወስዶ ለአንድ ቀን ታሰረው ተለቋል፡፡ እንደጋዜጣው ዘገባ ከሆነ ፦ከትላንት በስቲያ ሐሙስ ሶስት ሰዎች “በተጠረጠሩበት ወንጀል ይፈለጋሉ” የሚል መጥሪያ በመስጠት አዘጋጁን ከቢሮው እንደወሰዱትና እንደታሰረ የተገለፀ ሲሆን፤ ትላንት ጠዋት ፍ/ቤት ይቀርባል ተብሎ ቢጠበቅም “ዳኞች አልተሟሉም፤ ስንፈልግህ እንጠራሃለን” ተብሎ መለቀቁ ታውቋል፡፡ እንግድህ ጋዜጣው ስህተቱን ኣምኖ ማስተካከያ ስጥቶ እያለ በክልሉ መንግስት በጋዜጣ ኣዘጋጁ ላይ የተወሰደው ይህን መሰል እርምጃ ክልሉ ሚዲያን በተመለከተ ምን ያህል ስሱ መሆኑን ያሳያል።     ምንጭ፦ http://www.addisadmassnews.com/index.php?option=com_k2&view=item&id=13046:%E1%8B%A8%E1%88%AA%E1%8D%96%E1%88%AD%E1%89%B0%E1%88%AD-%E1%8C%8B%E1%8B%9C%E1%8C%A3-%E1%8A%A0%E1%8B%98%E1%8C%8B%E1%8C%85

A delegation of professors from the southern states of the US, including former US Ambassador to Ethiopia,has been to Hawassa University

Image
A delegation of professors from the southern states of the US, including former US Ambassador to Ethiopia, Tibor Najy, met with Foreign Minister Dr. Tedros today (October 10). The delegation, from universities which specialize in science and technology, has been on a week-long tour to Addis Ababa ,Dire Dawa, Adama and Hawassa Universities, to explore ways to forge partnerships between universities in Ethiopia and the US. The delegation members expressed their admiration at the tremendous leap Ethiopia has made in increasing the number of universities from 2 to 32 over the past two decades. They noted the importance of supplementing this massive expansion in higher education with efforts focused on the development of the associated faculties. They noted the need to address problems in relation to a lack of instrumentation, the importance of a strategy to retain staff and the need to poay competitive salaries. Dr. Tedros said that partnership with US universities specializing in

ስለ ኢትዮጵያ ብሮድካስተር ምን ያህል ያውቃሉ? ኣንጋፋው ሬድዮ ሲዳማ በኣገሪቱ የማህበረሰብ ሬድዮ ዝርዝር ውስጥ ኣልተካተተም፤ ምስጥሩ ምን ይሁን?

Image
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ባለስልጣን ባወጣው የኣገሪቱ የብሮድካስቲንግ ሚዲያ ዝርዝር ውስጥ 16 የማህበረሰብ ሬድዮዎች የተካተቱ ሲሆን፤ በኣገሪቱ የማህበረሰብ ሬድዮ ስርጭት በመጀመር በተለይ በደቡብ ኢትዮጵያ ቀዳሚ የሆነው ሬድዮ ሲዳማ በዝርዝሩ ውስጥ ኣልተካተተም። ሬድዮ ሲዳማ፤ እኣኣ በ1990 ዎቹ ላይ በኣይሪሽ መንግስት ድጋፍ በይርጋኣለም ከተማ በቀድሞው ፉራ የልማት ምርምር ማዕከል ውስጥ በ954 ኪሎሄርዝ መካከለኛ ሞገድ ስርጭት መጀመሩ የሚታወስ ነው። ሬድዮ ጣቢያው ከስኞ እስከ ኣርብ በኣብዘኛው የትምህርት ፕሮግራሞችን የምያስተላልፍ ሲሆን፤ ቅዳሜ እና እሁድ ደግሞ የተለያዩ ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ፕሮግራሞችን በማዘጋጀት ኣየር ላይ ያውላል። ሬድዮ ሲዳማ የሲዳማን ባህል እና ቋንቋ በማሳደግ በኩል ከፍተኛ ሚና ያለው ሲሆን፤ ከኣራት እስከ ስድስት ሚሊዮን ለሚቆጠረው የሲዳማ ህዝብ በቋንቋው ባህሉ የተተረከለት፤ የተዘፈነለት፤ በቋንቋው ድራማ የመሳሰሉ የሰነ ጥበብ ስራዎች የተሰሩለት ብሎም በተለያዩ ማህበራዊ ጉዳዮቹ ላይ በቋንቋው እንድወያይ እድል የተከፈተለት በሬድዮ ሲዳማ ነው። ጣቢያውን በባለበትነት ያስተዳድር የነበረው የቀድሞው የሲዳማ ልማት ፕሮግራም በኃላ ላይ ደግሞ የሲዳማ ልማት ኮፔሬሽን በመንግስት ጠልቃ ገብነት በሲዳማ ያካህዳቸው የነበሩት የልማት ስራዎች ሲቋረጥ፤ ሬድዮ  ሲዳማ የባጄት ችግር ኣጋጥሞት ያስተላልፋቸው የነበሩትን ፕሮግራሞች በኣግባቡ ማስተላለፍ ኣለመቻሉ ይታወሳል። በወቅቱ ፕሮግራሞችን በመደጋገም ኣድማጮችን እስከ ማሰልቸት ደርሶ ነበር። በኃላ ላይ ሬድዮ ጣቢያው በሲዳማ ዞን ትምህርት መምሪያ ስር የሆነ  ሲሆን እስከ ኣሁን ድረስ የቀድሞ ዝናውን በሲዳማ ህዝብ ዘንድ መመለስ ኣልቻለም።  የወራንቻ ኢንፎርሜሽን ኔትዎርክ ወደፊት በሬድ

የዝናብ ስርጭቱ በጥቅምትና ህዳር ወር የመከሰት እድሉ ሰፊ በመሆኑ የሲዳማ አርሶ አደር ጥንቃቄ ያድርግ

አዲስ አበባ መስከረም 30/2006 በመላው አገሪቱ ሰሞኑን እየታየ ያለው ወቅቱን ያልጠበቀ የዝናብ ስርጭት እየቀነሰ ቢሆንም በጥቅምትና ህዳር ወር የመከሰት እድሉ ሰፊ በመሆኑ አርሶ አደሩ ጥንቃቄ እንዲያደርግ የብሄራዊ ሚቲዎሮሎጂ ኤጀንሲ አሳሰበ። ኤጀንሲው እንዳለው ከመስከረም 20 ቀን ጀምሮ አብዛኛውን የሃገሪቱን ክፍል የሸፈነ የዝናብ ስርጭት እምብዛም ያልተለመደ ነው። በቀጣይም እንደባለፈው ሳምንት የተስፋፋ ዝናብ ባይጠበቅም በአንዳንድ አካባቢዎች ያልተጠበቀ ዝናብ ሊከሰት ስለሚችል የደረሱ ሰብሎችን በመሰብሰብ ረገድ አርሶ አደሩ ጥንቃቄ እንዲያደርግ ጥሪ ቀርቧል። የኤጀንሲው የሚቲዎሮሎጂ ትንበያና ቅድመ ማስጠንቀቂያ ዳይሬክተር አቶ ድሪባ ቆሪቻ በተለይ ለኢትዮጰያ ዜና አገልግሎት እንደተናገሩት በመላው አገሪቱ ባለፉት ዘጠኝ ቀናት ከባድ የሚባል የዝናብ መጠን ተመዝግቧል። በተለይም በአማራ ፣ ኦሮሚያ ፣ ደቡብና ሃረሪ ክልሎች እንዲሁም በሶማሌ ክልል ሰሜናዊ አጋማሽ ድሬዳዋን ጨምሮ ይህ ያልተለመደ ዝናብ ያለማቋረጥ መዝነቡን ተናግረዋል። የአማራ መካከለኛው ምስራቅ፣ ደቡብ ኦሮሚያ እና የደቡብ ክልል ሰሜናዊ አጋማሽ ከበድ ያለ ዝናብን ያስተናገዱ አካባቢዎች እንደነበሩ አስታውቀዋል። በእነዚህ አካባቢዎች በ24 ሰዓት ጊዜ ውስጥ ከ40 እስከ 80 ሚሊ ሜትር ዝናብ መመዝገቡን ገልጸዋል። የወቅቱ ዝናብ ዘግይተው ለተዘሩ ሰብሎች ጥቅም እንደሚኖረው አቶ ድሪባ ተናግረው እርጥበቱ በተለይ ሽምብራና ምስር የመሳሰሉትን እህሎች ቶሎ ለመሰብሰብ ከማገዝ ባለፈ በቂ የእንስሳት መኖ እንዲኖር ያደርጋል ብለዋል። በቆላም አካባቢ ለሚገኙ አርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች ለመጠጥ ውሃ አቅርቦትና ለግጦሽ የሚሆን ሳር ለማግኘት ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው አቶ ድሪባ ተናግረዋል። በተጨማሪ በተለያዩ የአገ