Posts

‹‹በኢሕአዴግ ውስጥ መከፋፈል አለ የተባለው ምኞት ነው›› ተባለ

-የሃይማኖት አክራሪነት ትግል ፖለቲካዊ ነው አሉ  -የተቃዋሚዎች የሰላማዊ ሠልፍ ጥያቄ ከቀጠለ እንደሚቆም ገለጹ -በኬንያ የደረሰው ጥቃት በኢትዮጵያ ላይ እንደደረሰ ይሰማናል ብለዋል የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን ሕልፈት ተከትሎ በ2005 ዓ.ም. መስከረም ወር ላይ በይፋ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በጠቅላይ ሚኒስትርነት የተሾሙት አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ የሥልጣን ቆይታ አንድ ዓመት አስቆጥሯል፡፡ የአንድ ዓመት የሥልጣን ቆይታቸው ከተቆጠረ ሁለት ሳምንታት በኋላ ባለፈው ዓርብ ለአገር ውስጥና ለውጭ የመገናኛ ብዙኃን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡  ይህ ጋዜጣዊ መግለጫቸው ወደ ሥልጣን የመጡበትን አንደኛ ዓመት ለማስታወስ ባይሆንም፣ ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ በአገሪቱ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማኅበራዊ እንዲሁም በአኅጉራዊና በዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ላይ መግለጫ በመስጠት ከጋዜጠኞች ለቀረቡ ጥያቄዎችም ምላሽ ሰጥተዋል፡፡  በዋናነት ካነሷቸው ፖለቲካዊ ጉዳዮች ዋነኞቹ በኢትዮጵያ የሃይማኖት አክራሪነትና ሽብርተኝነት፣ በኢሕአዴግ ውስጥ አለ ስለሚባለው አለመግባባትና የተቃዋሚ ፓርቲዎች በሰላማዊ ሠልፍ የሚያነሷቸው ጥያቄዎች ይገኙበታል፡፡ በኢኮኖሚ ረገድ የአገሪቱ ኢኮኖሚ በተጠናቀቀው ዓመትም ፈጣን ዕድገት ማስመዝገቡን፣ የግል ባለሀብቶች ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ባላቸው ዘርፎች ለመሳተፍ አለመፈለግ፣ መሠረታዊ በሚባሉት የመጠጥ ውኃ፣ የሞባይል ስልክና የኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎቶች የሚስተዋሉ የአገልግሎት መቆራረጦች ሊቀረፍ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡  ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ጋዜጠኞች ለሚያነሷቸው ጥያቄዎች ዕድል ከመስጠታቸው በፊት ባለፈው የአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ አገሪቱ ስላስመዘገበቻቸው ውጤቶች አጠር ያለ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በእሳቸው ማብራ

የመንግሥትን አስቸኳይ ትኩረትና መፍትሔ የሚሹ ሰባት ዓበይት ችግሮች

Image
ይበዛ ያንስ፣ ይሰፋ ይጠብ፣ ይረዝም ያጥር፣ ይሻል ይባስ እንደሆነ እንጂ ምንጊዜም በየትም አገር ችግሮች ይኖራሉ፡፡ ዋናው ጉዳይ ችግር መኖሩ አይደለም፡፡ ችግሩን ለይቶ፣ አውቆና ትኩረት ሰጥቶ መፍትሔ መስጠት ያለመቻል ካለ ነው የሚያሳስበው፡፡ መፍትሔ ያላገኘ ችግር እየተባባሰ ሄዶ አገርንና ሕዝብን ለአደጋ ይዳርጋልና፡፡  ይህ ስለሆነም ነው ሁላችንም እንደ ሕዝብና እንደ ዜጋ፣ በተለይም መንግሥት ኃላፊነት የተሸከመ አካል እንደመሆኑ መጠን በየጊዜው የአገር ችግሮችን እየመረመረ፣ እየገመገመና ቅደም ተከተል እያስያዘ ለችግሮች መፍትሔ መስጠት ይኖርብናል፡፡  በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያችን እንደሌላው አገር ሁሉ የተለያዩ ችግሮች አሉ፡፡ ተገቢውን ትኩረት ካላገኙና አስቸኳይ መፍትሔ ካልተደረገላቸው በአገር ላይ አደጋ ሊያስከትሉ ይችላሉ፡፡ ችግሮቹ ተለይተውና ታውቀው ልዩ ርብርብ ሊደረግባቸው ያስፈልጋል፡፡ የግድ ይላል፡፡ የመንግሥትን ትኩረትና መፍትሔ የሚሹ ወቅታዊ፣ ልዩና አስቸኳይ ዓበይት የኢትዮጵያ ችግሮች የምንላቸው የሚከተሉት ናቸው፡፡  1.ሰብሰብ፣ ጠንከርና ነቃ ያለ የመንግሥት አመራር ያስፈልጋል የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር በሞት ሲለዩና አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሲሰየሙ ምንም ችግርና ብጥብጥ አልነበረም፡፡ ከዚያ በኋላም ሰላማዊ በሆነ ሁኔታ አገራችን እየተመራች ናት፡፡ ይህን የሚመለከት ችግር ስላለ አይደለም ሰብሰብ፣ ጠንከርና ነቃ ያለ መንግሥትና አመራር ያስፈልጋል እያልን ያለነው፡፡ ዓለም በኢኮኖሚ ቀውስ እየታመሰ ነው፡፡ እኛንም እየጐዳን ነው፡፡ ትላልቅና በርካታ ፕሮጀክቶች ተግባራዊ ሲደረጉ ከፍተኛ ፋይናንስ ያስፈልጋል፡፡ ከዚህ በፊት ያልነበረ የሃይማኖት ግጭትና ልዩነት እየታየ ነው፡፡ ችግሩ ካልተፈታ አስጊ ነው፡፡ የኢትዮጵያን ዕድገት የማይሹና

ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት ሆኑ

Image
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የፌዴሬሽን ምክር ቤት ሰኞ መስከረም 27 ቀን 2006 ዓ.ም. ባደረጉት የጋራ ስብሰባ በቱርክ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ሆነው እያገለገሉ ያሉትን ዶ/ር ሙላቱ ተሾመን በፕሬዚዳንትነት ሰየሙ፡፡ አዲሱ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሙላቱ፣ በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ተገኔ ጌታነህ አማካይነት ቃለ መሐላ ከፈጸሙ በኋላ ሥልጣኑን የተረከቡት፣ በሁለት ዙር ለ12 ዓመታት ፕሬዚዳንት ከነበሩት ከአቶ ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ ነው፡፡ በዕለቱ ከሰዓት በኋላ የስድስት ዓመት የፕሬዚዳንትነት የሥራ ዘመናቸውን በብሔራዊ ቤተ መንግሥት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝና የቀድሞው ፕሬዚዳንት ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ አቀባበል ካደረጉላቸው በኋላ መጀመራቸው ታውቋል፡፡   በቀድሞው ወለጋ ጠቅላይ ግዛት አርጆ ወረዳ በ1949 ዓ.ም. የተወለዱት ዶ/ር ሙላቱ፣ የመጀመርያና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በአርጆና በአዲስ አበባ ከተሞች የተከታተሉ ሲሆን፣ የመጀመርያ ዲግሪያቸውን ከቻይና ቤጂንግ ዩኒቨርሲቲ በፖለቲካል ኢኮኖሚ ፍልስፍና በ1974 ዓ.ም.፣ በዓለም አቀፍ ሕግ የማስተርስ ዲግሪያቸውን በዚያው ዩኒቨርሲቲ በ1980 ዓ.ም. አግኝተዋል፡፡ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲም በ1983 ዓ.ም. በዓለም አቀፍ ሕግ በዶክትሬት ዲግሪ ተመርቀዋል፡፡ የኦሮምኛ፣የአማርኛ፣እንግሊዝኛ፣ቻይናኛና ፈረንሳይኛ ቋንቋዎች ተናጋሪ የሆኑት ተሰያሚው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሙላቱ፣ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በቆንስልነትና በዳይሬክተርነት፣ በጃፓንና በቻይና በባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደርነት፣ በኢኮኖሚ ልማትና ትብብር ምክትል ሚኒስትርነት፣ በግብርና ሚኒስትርነትና በፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈጉባኤነት ያገለገሉ ሲሆን፣ፕሬዚዳንት እስከሆኑበት ዕለት ድረስ በቱርክ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር

በልማት “ማሳበብ” ከልማታዊ መንግስት አይጠበቅም!

Image
በመንግስት “ሳንባ” መተንፈስ ለ“ቲቢ” ያጋልጣል                 ፖለቲካዊ ወጋችንን የምንጀምረው በቀልድ ነው፡፡ ግዴለም ባትስቁም አልቀየማችሁም፡፡ ፈገግ ካላችሁ መች አነሰኝ! (ኑሮ “ሃርድ” ሲሆን ሳቅም ይገግማል አሉ) ይልቅስ ሳልረሳው ቀልዱን ቶሎ ልንገራችሁ፡፡ - ፡፡ አንድ የሰው አገር ሰው (ፀጉረ ልውጥ ማለቴ አይደለም!) ከጅቡቲ እየተጫኑ ወደ አዲስ አበባ የሚገቡትን የመኪኖች መዓት በትዝብት ሲመለከት ይቆይና እነዚህ ሁሉ መኪኖች የት ነው የሚገቡት?” ሲል ይጠይቃል፡፡ የቀድሞው ጠ/ሚኒስትር መለስ ዜናዊም (መሬት ይቅለላቸውና!) “የሌሎቹን አላውቅም…አይሱዙ ግን ገደል ነው የሚገባው” አሉ (አሉ ነው!)  በነገራችሁ ላይ… በመዲናዋ የሚርመሰመሰው የመኪና ብዛት እኮ ከነዋሪው እኩል ሊሆን ትንሽ ነው የቀረው፡፡ አንዳንዴ ሳስበው ግን ባለሀብቱም ሆነ ሌላው ትንሽ ገንዘብ እጁ ላይ ከተረፈው ዝም ብሎ መኪና የሚያስጭን ነው የሚመስለኝ። (ጀት ለማስጫን አቅም የለችማ!?) እናላችሁ… የመዲናዋ ተሽከርካሪዎች ከህዝቡ በልጠው መፈናፈኛ ከማጣታችን በፊት “አራርቆ መግዛት” የሚል ፖሊሲ ቢቀረጽ ሸጋ ይመስለኛል፡፡ (“አራርቆ መውለድ” እንደሚባለው) ትራፊክ ፖሊስና መንገድ ትራንስፖርት ጥናት አላደረጉ ይሆናል እንጂ የመኪና አደጋ እንዲህ ህዝብ የሚፈጀው የተሽከርካሪው ቁጥር ያለቅጥ በዝቶ ሊሆን ይችላል እኮ! (“የመኪና ምጣኔ” ሳያስፈልገን አይቀርም!)   እኔ የምላችሁ…ባለፈው ሳምንት የኢቴቪ “ዓይናችን” ፕሮግራም ላይ ከመንጃ ፈቃድ አወጣጥና የአሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ ት/ቤቶች አሰራር ጋር በተገናኘ የተጠየቁት የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ሃላፊ የሰጡትን ምላሽ ሰምታችሁልኛል? ሃላፊዋ የተናገሩትን በአማርኛ ተርጉሞ ለነገረኝ (የገባው ካለ ማለቴ ነው) ወሮታ

ጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም የተቃዋሚ ፓርቲዎች ሰልፍ ላይቀጥል ይችላል አሉ

Image
ተቃዋሚ ፓርቲዎች በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የሚያደርጓቸው የተቃውሞ ሰልፎች ተደጋጋሚና መንግስት አቋም የያዘባቸውን ጉዳዮች የሚያነሱ እንደሆኑ የጠቆሙት ጠ/ሚኒስትር ኃ/ማርያም ደሳለኝ፤ መንግስት ለእያንዳንዱ ሰልፍ ጥበቃ ማድረግ ስለማይችል ሰልፎቹ በተለመደው መልኩ ላይቀጥሉ እንደሚችሉ ተናግረዋል፡፡ ጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሳለኝ ትናንት በጽ/ቤታቸው ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፤ ተቃዋሚ ፓርቲዎቹ የሚያነሷቸው ጥያቄዎች የራሳቸው የፓርቲዎቹ ሳይሆኑ የሌሎች ሃይሎች እንደሆኑ ገልፀዋል፡፡ ፓርቲዎቹ ሰልፍ ማካሄድ ህገመንግስታዊ መብታቸው መሆኑን የጠቀሱት ጠ/ሚኒስትሩ፤ መንግስት በተደጋጋሚ ጥበቃ ሲያደርግ ቢቆይም፣ በሰልፎቹ የሚነሱት ጥያቄዎች ፋይዳ ቢስ ከመሆናቸውና ከፓርቲዎቹ ብዛት አንፃር መንግስት በቀጣይ ለሰልፎች ጥበቃ ለማድረግ የሚቸገርበት ሁኔታ ሊፈጠር እንደሚችል አስረድተዋል፡፡  ተቃዋሚ ፓርቲዎች፤ መንግስት በተደጋጋሚ ምላሽ የሰጠባቸውን ጥያቄዎች መላልሰው የሚያቀርቡት በመንግስት ላይ ጫና በመፍጠር አቋሙን ለማስቀየር በማሰብ ሊሆን ይችላል ያሉት ጠ/ሚኒስትሩ፤ ይሄ ግን በፍፁም የማይሳካ ሃሳብ ነው ብለዋል፡፡ “ግንቦት ሰባት” በቅርቡ መንግስትን ለመጣል ወታደራዊ እርምጃ እንደሚወስድ በይፋ መግለፁን በተመለከተ ተጠይቀው ሲመልሱም፣ የፓርቲው አመራሮችና ደጋፊዎች ተጨባጭ ያልሆነ ህልም ውስጥ ሆነው የተናገሩት ነገር እንደሆነና ከህልማቸው ሲነቁ እውነታውን እንደሚገነዘቡት ጠ/ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡ ኢህአዴግ ውስጥ መከፋፈልና የሃይል መጠባበቅ አለ የሚለውን መረጃ በተመለከተም “ይህ የአንዳንድ አፍራሽ ሃይሎች ከንቱ ምኞትና ተጨባጭ ያልሆነ አሉባልታ ነው” ሲሉ አጣጥለውታል፡፡ http://www.addisadmassnews.com/index.php?option=com_k2&am