Posts

Study finds growth not helping Africa's poor

Image
Survey says African countries have failed to reduce poverty despite economic growth experienced over the past decade. I mproved economic growth over the past decade in Africa has failed to reduce poverty in a majority of countries on the continent, a new study has revealed. The Afrobarometer survey, released on Tuesday, said that despite playing host to some of the world's highest economic growth rates, many Africans still reported shortages of basic needs, including water, food, healthcare and cash. "Meeting their basic daily needs remains a major challenge for a majority of Africans, even at a time when their countries are reporting impressive economic gains," the survey found, citing data retrieved from the citizens of 16 African countries over the past 10 years. In a second part of the study, the report surveyed the opinions of more than 50,000 citizens of 34 countries across the continent between 2011-2013 and concluded that " lived" pover

ጥቂት ስለ ዋራ _የኣካባቢው ህዝብ ብዛት እየጨመረ ከመምጣቱ ጋር በተያያዘ ወደ እርሻ መሬትነት እየተቀየረ ነው

Image
Wara Sidama በሲዳማ ትልቁ ሜዳ የሆነው ዋራ የኣካባቢው ህዝብ ብዛት እየጨመረ ከመምጣቱ ጋር በተያያዘ  ወደ እርሻ መሬትነት እየተቀየረ በመምጣቱ ስፋቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያነሰ መጥቷል። የዋራ ሜዳ በሲዳማ ህዝብ ዘንድ ታሪካዊ ፋይዳ ያለው ቦታ ሲሆን፤ በታሪክም የዛሬ 400 ኣመታት በፊት ሲዳማ እና ሆፋ የተባለ ጎሳ፤ ዛሬ የሲዳማ ህዝብ የሰፈረበትን መሬት በባለቤትነት ለመያዝ ታሪካዊ ጦርነት ያደረገበት ቦታ ነው። የታሪክ ድርሳናት እንደሚያወሱት፤ የዋራ ሜዳ ለሲዳማ ከብት ኣርብዎች ሁነኛ የግጦሽ ማዕከል ነው። በኣሁኑ ጊዜ የኣከባቢው ህዝብ ባለበት የመሬት ጥበት የተነሳ የከብት እርባታን በመተው የእርሻ ስራን በማስፋፋት ላይ በመሆኑ የዋራ ሜዳ ስፋት እንድቀንስ ሆኗል። የዋራ ሜዳ ከታሪካዊ ፋይዳው በተጨማሪ የሲዳማ ክልል የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ለምታዘጋጀው ዓለም ኣቀፋዊ ክሩሴይድ ከግማሽ ሚሊዮን ህዝብ በላይ ከመላው ኣለም የምሰባሰብበት ቦታ ነው።

ማጅራት ገትርና መከላከያው፣

Image
የወባን(ንዳድ)ን ያክል ባይሆንም ፤ አፍሪቃ ውስጥ ልጆችንና ወጣቶችን ይበልጥ በመጠናወት ፣ በብዛት ሲገድል የቆየ በሽታ ፤ ማጅራት ገትር ነው። ይሁንና ፤ ይህን ቀሳፊ በሽታ መከላከልም ሆነ መግታት የሚቻልበት ብልሃት ስለመረጋገጡ ከሰሞኑ የወጡ የምርምር ውጤቶች ማስገንዘባቸው የሚታወስ ነው። ማጅራት ገትር፣ በተለያዩ ክፍላተ ዓለም ቢገኝም ፣ ይበልጥ የተስፋፋውና ሰውም በብዛት ሲፈጅ የቆየው፤ አፍሪቃ ውስጥ ፣ ከሰሐራ ምድረበዳ በስተደቡብ ፣ ከምድር ሰቅ በስተሰሜን ከሞላ ጎደል ፤ በ 5 እና 15 ዲግሪ ከፍተኛ መሥመር መካከል ፣ ከሴኔጋል እስከ ኢትዮጵያና ኤርትራ፣ የሳሔል መቀነት በተሰኘው የክፍለ ዓለሙ ቀጣና በሚገኙ 26 ያህል አገሮች ነው። እነዚህ አገሮች ደግሞ በከፊል ድርቅ የሚያጠቃቸው መሆናቸው የታወቀ ነው። በሽታውን የሚያስተላልፉት ተኀዋስያን ፤ ባክቴሪያዎች የተለያዩ በዓይን የማይታዩ ኢምንት ነፍሳትም መንስዔዎች ሊሆኑ ይችላሉ። ማጅራት ገትር እንደሚታወቀው፤ አንገት እንዳይንቀሳቀስ ቀስፎ የሚይዝ፣ በራስ ምታትና ትኩሳት ታጅቦ ፣ ከማጅራት እስከ ኅብለ -ሠረሠር ፣ ማዕከላዊውን የነርብ አውታር የሚጠናወት በሽታ ነው። አእምሮን እንደመሳት ያደርጋል፤ ያጥወለውላል፤ በበሽታው የተያዘ ሰው ብርሃንና ኃይለኛ ድምፅ በእጅጉ ያውኩታል። አንገትን አግርሮ የማያንቀሳቅሰው፤ ከማጅራት እስከ ኅብለ ሠረሠር ነርቦችን የሚጠናወተው፤ አፍንጫ ፤ ጆሮና ላንቃን የሚያሳምመው በሽታ፤ ሊደነቁር ፤ የሠራ-አካላትን ሊያሽመደምድና ለሞት ሊደርግ የሚችል ሕመም ነው። በጎልማሦች ዘንድ የህመሙ ዋና መለያ ዘጠና ከመቶ ማለት ይቻላል፤ ብርቱ ራስ ምታት ነው። 70 ከመቶ መንስዔውም በባክቴሪያ ሳቢያ የሚዛመተው የማጅራት ገትር በሽታ አንደኛው ከፊል ነው። በአፍሪቃ በሰፊው የ

የ2015 ዲቪ ሎተሪ ተጀመረ

Image
የ2015 የዲቪ ሎተሪ መርሐ ግብር (ዲቪ 2015) ከመስከረም 21 ቀን 2006 ዓ.ም. ጀምሮ ለሚቀጥሉት 32 ቀናት ማለትም እስከ ጥቅምት 23 ቀን 2006 ዓ.ም. ድረስ ማመልከት እንደሚቻል፣ በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ መስከረም 20 ቀን 2006 ዓ.ም. አስታወቀ፡፡ በተፈቀደው የማመልከቻ ቀን ውስጥ በድረ ገጽ “dvlottery.state.gov” በመሙላት ማመልከት እንደሚቻል ያስታወቀው ኤምባሲው፣ የወረቀት ማመልከቻዎች ተቀባይነት እንደማይኖራቸው አስታውቋል፡፡ ኤምባሲው እንደገለጸው፣ ኢትዮጵያ የዲቪ 2015ን ዕድል ለመሳተፍ የሚያስፈልጉ መስፈርቶችን ታሟላለች፡፡ ቀደም ባሉ አምስት ዓመታት ውስጥ ከ50 ሺሕ በላይ ዜጐቻቸውን ወደ አሜሪካ የላኩ አገሮች የዕድሉ ተጠቃሚ እንደማይሆኑና ኢትዮጵያ ግን ያንን ያህል ስላላከች የዕድሉ ተጠቃሚ መሆኗን አስታውቋል፡፡ አንድ አመልካች ወይም ግለሰብ ማመልከት የሚችለው በሚኖርበት አገር ሳይሆን በተወለደበት ቦታ ወይም አገር መሆኑንም ኤምባሲው አስታውቋል፡፡ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የዲቪን ሒደትን ቀልጣፋና አስተማማኝ ለማድረግ እ.ኤ.አ. ከ2005 ጀምሮ የኤሌክትሮኒክ ምዝገባን ተግባራዊ ማድረጉንና በሕገወጥ መንገድ ወደ አሜሪካ ለመግባት፣ ለማጭበርበር የሚሞክሩ ወይም ከአንድ በላይ ማመልከቻ የሚያስገቡ ሰዎችን መለየት የሚችሉ ቴክኖሎጂዎችንና ሌሎች ሥልቶችን በሥራ ላይ ማዋሉን ገልጿል፡፡  መሥሪያ ቤቱ የዲቪ 2015 ዕድለኞች መመረጣቸውንም ሆነ የቪዛ ማመልከቻና ቃለ መጠይቅ ስለሚያደርግበት ሁኔታ የሚያሳውቀው በኢንተርኔት በመሆኑ፣ አመልካቾች በድረ ገጹ ማወቅ እንደሚችሉ ኤምባሲው አስታውቋል፡፡  የተመረጡ አመልካቾች ለራሳቸውና ለቤተሰቦቻቸው ኢሚግራንት ቪዛ ስለሚጠይቁበት ሒደት የሚገልጽ መመርያ እንደሚ

‹‹ቢዝነስ ለመሥራት ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው አንደኛው ችግር ቢሮክራሲ ነው››

Image
አቶ ሔኖክ አሰፋ፣ የፕሪሳይስ ኮንሰልት ኢንተርናሽናል ማኔጂንግ ዳይሬክተር  ፕሪሳይስ ኮንሰልት ኢንተርናሽናል፣ ከስድስት ዓመታት በፊት የተቋቋመ በማኔጅመንት፣ በቢዝነስና በኢንቨስትመንት ዘርፎች የማማከር ሥራ ላይ የተሰማራ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ነው፡፡ በአገር ውስጥ ከሚገኙ የግል ኩባንያዎች አንስቶ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚገኙት ኤጀንሲዎችንና ድርጅቶችን የሚያማክረው ይህ ተቋም፣ 25 ቋሚ ሠራተኞች፣ ፕሮጀክት በመጣ ቁጥር እንዳስፈላጊነቱ የሚሠሩ 60 ባለሙያዎችና አሜሪካ፣ ካናዳ እንዲሁም ጀርመን አገር የሚገኙ የሥራ አጋሮች አሉት፡፡ መቀመጫውን አዲስ አበባና ኒውዮርክ ያደረገው ፕሪሳይስ ኩባንያን የመሠረቱትና ተቋሙን በማኔጂንግ ዳይሬክተርነት የሚመሩት አቶ ሔኖክ አሰፋን  ምዕራፍ ብርሃኔ  አነጋግራቸዋለች፡፡  ሪፖርተር፡- ስለትምህርት ደረጃዎና ሲሠሯቸው ስለነበሩት ሥራዎች ይንገሩን፡፡ አቶ ሔኖክ ፡- የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቴን ያጠናቀቁት በካቴድራል ትምህርት ቤት ነው፡፡ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቴን ደግሞ አሜሪካ ኒውጄርዚ ከተማ ውስጥ በሚገኝ ትምህርት ቤት ተምሬያለሁ፡፡ የመጀመሪያ ዲግሪዬንና ማስተርሴን እዚያው አሜሪካ ከሚገኘው ፎርድሃም ዩኒቨርሲቲ፣ ኢንተርናሽናል ትሬድ ኤንድ ፋይናንስና ኢኮኖሚክስ ላይ ሠርቻለሁ፡፡ ትምህርቴን ከጨረስኩ በኋላ ኒውዮርክ ከተማ ውስጥ ብሩክሊን በሚባል አካባቢ የሚገኘው ብሩክሊን ንግድ ምክር ቤት ውስጥ፣ አነስተኛ የብሩክሊን አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርቶቻቸውን ለወጭ ገበያ ለማቅረብ በሚያስችላቸው ፕሮግራም ውስጥ ዓለም አቀፍ የንግድ ባለሙያ ሆኜ አገልግያለሁ፡፡ በንግድ ምክር ቤቱ በነበረኝ የአራት ዓመታት ቆይታም፣ በጊዜው ከነበሩት ዳይሬክተሮች ውስጥ አንዱ ለመሆን በቅቼ ነበር፡፡ ከዚያም በተጨማሪ የንግድ ምክ