ሥራን የማይንቀው ዳያስፖራ
በጌታቸው ንጋቱ ዘመን በተለወጠ ቁጥር የተቻለኝን ሁሉ በማድረግ በአገር ምድር ከዘመድ አዝማድ ጋር አዲስ ዓመትን ለማክበር ከምኖርበት አገር አቀናለሁ፡፡ ከአገር ከወጣሁ ጀምሮ አንድም ዓመት የዘመን መለወጫን ከኢትዮጵያ ውጪ አሳልፌ አላውቅም፡፡ ዘመድና ጓደኛም ስለ አሜሪካ ኑሮ ይጠይቃሉ፡፡ እኔም የተቻለኝን ሁሉ እመልሳለሁ፡፡ ከሁሉም ግን አንድ የሚገርመኝ ጥያቄ ከአንዲት ጓደኛዬ ነው የመጣው፡፡ ‹‹ኑሮ በአሜሪካ እንዴት ነው? መቼም አሜሪካ የሚኖር ሰው ምንድነው የምትሠራው አይባልም፡፡ ሁሉም ተጠግርሮ ነው የሚኖረው፤›› አለችኝ፡፡ ጓደኛዬ ስለ ሥራና የሥራ ክቡርነት ያላትን አመለካከት ለማረቅ ብሞክርም ይህ የአንድ ሰው ብቻ ሳይሆን የብዙዎች የግንዛቤ ችግር ስለመሰለኝ ይህንን ለመጻፍ ተነሳሁ፡፡ 1.ሥራ ክቡር ነው ቢያንስ በሐሳብ ደረጃ ሥራ ክቡር ነው እንላለን፤ ነገር ግን ስንቶቻችን ነን ሥራ ክቡር ነው፤ ብለን በተሰማራንበት የሥራ መስክ ውጤታማ ለመሆን የምንጥረው የሚለው አጠያያቂ ነው፡፡ ሥራ ክቡር ነው የሚለው አባባል በሰሜን አሜሪካ በተግባር ላይ ውሎ የሚታይ አባባል ነው፡፡ የምትሠራው ሥራ ሳይሆን በምትሠራው ሥራ ምን ያህል ውጤታማ ነህ፤ ታክስህን በሥነ ሥርዓት ትከፍላለህ፤ የክሬዲት (ብድር) አጠቃቀምህ ምን ይመስላል፤ ሰላማዊና ጠንካራ ሠራተኛ ነህ ወይ? የሚለው ቅድሚያ ይሰጠዋል፡፡ አንዳንዶች ከአገር ወጥተው ኑሯቸውን በአሜሪካ ያደረጉ ኢትዮጵያውያን ታክሲ በማሽከርከራቸው፤ ሆቴል በማስተናገዳቸው ወይም ‹‹ፓርኪንግ ሎት›› ውስጥ በመሥራታቸው ከአገር ቤት ባሉ ጓደኞቻቸው ትችት ሲሰነዘርባቸው ስሰማ አንዳንዶች ስለ ሥራ ባላቸው ግምት አዝናለሁ፡፡ ከቅርብ ሳምንታት በፊት በመሀል ዋሽንግተን ዲሲ አንዲት ወጣት ነጭ አሜሪካዊት በባር