Posts

‹‹የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ስድስት ዓመት ገለልተኛ ሆኖ ካገለገለ በኋላ ነፃ ሆኖ ሐሳቡን መግለጽ መቻል አለበት››

Image
ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ፣ የመጀመሪያው የኢፌዲሪ ፕሬዚዳንት ከሽግግር መንግሥቱ በኋላ በኢትዮጵያ በሦስት ዙር (ተርም) ሁለት ርዕሰ ብሔሮች [ፕሬዚዳንቶች] ተሰይመዋል፡፡ ላለፉት 12 ዓመታት በሥራ ላይ የሚገኙት ፕሬዚዳንት ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ በ2005 ዓ.ም. የሥራ ዘመናቸው ያበቃል፡፡ በ2006 ዓ.ም. በመስከረም ወር መጨረሻ አካባቢ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የፌዴሬሽን ምክር ቤት የጋራ ጉባዔ ሲከፈት ለሚቀጥሉት ስድስት ዓመታት የሚያገለግሉ አዲስ ፕሬዚዳንት ይሰየማሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ወደተንጣለለው ብሔራዊ ቤተ መንግሥት ማን ሊገባ ይችላል የሚለው ጉዳይ እስካሁን ባይታወቅም፣ የተለያዩ የኅብረተሰቡ ክፍሎች የተለያዩ ሰዎችን ሰብዕና በመምዘዝ እየተነጋገሩ ነው፡፡ ገዥው ፓርቲም በዚህ ጉዳይ ላይ መጠመዱ ተሰምቷል፡፡ ኢትዮጵያ ፓርላሜንታዊ ሥርዓት የምትከተል አገር ተደርጋ የኢፌዲሪ መንግሥት ሲመሠረት፣ የመጀመሪያው ፕሬዚዳንት ሆነው መንበሩን የተቆናጠጡት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ነበሩ፡፡ ከፕሬዚዳንትነታቸው ቆይታ፣ ከቤተ መንግሥት ሕይወትና ከቀጣዩ የአገሪቱ ፕሬዚዳንት አሿሿምና ተግባር ጋር በተያያዘ የአሁኑን የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ ሊቀመንበር ዶ/ር ነጋሶን  ውድነህ ዘነበ   አነጋግሯቸዋል፡፡  ሪፖርተር፡- የኢፌዲሪ መንግሥት ሲመሠረት የመጀመሪያው ፕሬዚዳንት ሆነው የተሰየሙት እርስዎ ነበሩ፡፡  የተመረጡበት ሒደት እንዴት ነበር? የተጠቆሙ ሰዎችስ ነበሩ? ዶ/ር ነጋሶ ፡- በ1987 ዓ.ም. ከምርጫው በፊት ነው የሆነው፡፡ ሒደቱ አሁን ተለውጦ ከሆነ አላውቅም፡፡ የዚያን ጊዜ በሥራ አስፈጻሚ ተነጋግረን ሦስት ሐሳቦች ቀረቡ፡፡ አንደኛ ወ/ሮ ገነት ዘውዴ፣ ሁለተኛ ፕሮፌሰር ጀማል አብዱልቃድር [የኦሕዴድ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል የነበሩ]፣ ሦስተኛ አም

Yirgalem

Image
I have now started my summer placement in Yirgalem; I am teaching English to the children from the Stride Athletics Club. Yirgalem is in Southern Ethiopia and it is located 260km south of Addis Ababa in the Sidamo Zone of the Southern Nations, Nationalities and People’s Region. The town has a population of around 45,00 and the local language is Sidamo. The town is around eighty years old and was previously the first provincial capital of the Sidamo Province. Despite its previous status, it has not developed at a fast rate; there are a number of derelict houses and businesses in the town and there is also a great deal of poverty. However, the town does have several schools, a hospital, a technical and vocational college, an education and training institute, a sports stadium and a couple of hotels. It also has hot springs which are used for swimming, washing clothes and the public showers. A lot of coffee is grown in Yirgalem and there are also many banana trees. http://jelford

A Child’s Life in Yirgalem

Image
During my English classes, the older students have been doing an extended writing project. They started by photographing different aspects of their lives (e.g. family, school, work and hobbies) using a disposable camera. Then, they did some writing to go with their photographs. In their writing they have described their family life. The majority of them come from large families with up to ten siblings! Most of them are in grades 6 to 12 and are aged between 12 and 18. They all help their families in different ways. This includes: chopping wood, fetching water, cooking, cleaning, sewing, buying groceries from the market and looking after younger brothers and sisters. Some of the boys clean shoes to earn extra money. Others help on the farm or work in shops and cafes. As well as attending Stride Athletics, they have a variety of other hobbies. This includes: playing football, basketball and table tennis, reading, watching films, swimming in the river and riding their bicycles. Reli

በሲዳማ ዞን ዳራ ወረዳ ሲቪል ሰርቪስ ጽህፈት ቤት በውጤት ተኮር እቅድና የለውጥ ተግባራት እንዲሁም በመልካም አስተደደር ሥራዎች አተገባበር የተሻለ አፈፃፀም ላሳዩ ሴክተር መስሪያ ቤቶችና የገጠር ቀበሌያት የእውቅና ሽልማት መስጠቱ ተገለፀ፡፡

በሲዳማ  ዞን ዳራ ወረዳ ሲቪል ሰርቪስ ጽህፈት ቤት በውጤት ተኮር እቅድና የለውጥ ተግባራት እንዲሁም በመልካም አስተደደር ሥራዎች አተገባበር የተሻለ አፈፃፀም ላሳዩ ሴክተር መስሪያ ቤቶችና የገጠር ቀበሌያት የእውቅና ሽልማት መስጠቱ ተገለፀ፡፡ የወረዳው ሲቪል ሰርቪስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አሰፋ ዲንጋማ እንደተናገሩት ተቋማት የመፈፀምና የማሰፈፀም አቅማቸውን በማጎልበት የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎች በተቀላጠፈ አሰራር በመተግበር የለውጥ ሰራዊት እንዲሆኑ እየተሰራ ይገኛል፡፡ የወረዳው ዋና አስ ተዳዳሪ አቶ ደስታ ደኒሶ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት በሁሉም ተቋማት የውጤት ተኮር እቅድ ትግበራና የመንግስት ሠራተኞች ምዘና ሥርዓትን ከግብ በማድረስ የተነደፈውን የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ተግባራዊ ማድረግ ይገባቸዋል፡፡ በከተማም ሆነ በገጠር ቀበሌያት የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎችን በአግባቡ በማከናወን ለህብረተሰቡ ተገቢው አገልግሎት መስጠት እንዳለበት የጠቆሙት ዋና አስተዳዳሪው ወደ ኃላ የቀሩትም በቀጣይ እንዲበረታቱ ጠይቀዋል፡፡ በበጀት አመቱም በለውጥና የመልካም አስተዳደር ሥራው የወረዳው ግብር፣ ህብረት ስራ ንግድና ኢንዱስትሪና ትምህርት ጽህፈት ቤቶች እንዲሁም ከገጠር 3 ቀበሌያት ከ1 እስከ 3 በመውጣት የዓይነትና የማበረታቻ የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል፡፡ የወረዳው ባህልና ቱሪዝም የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጽህፈት ቤት እንደዘገበው፡፡ ምንጭ፦ http://www.smm.gov.et/_Text/16NehTextN605.html

33ቱ ፓርቲዎች የጋራ ህዝባዊ ስብሰባ ነገ ያካሂዳሉ

“ፍርሃትን፣ ሙስናን፣ አፈናን፣ አምባገነንነትን በጋራ በቃ ካልን፣ ያበቃል” ለአገሪቱ ችግሮች የጋራ መፍትሔ ለማፈላለግ 33 ተቃዋሚ ፓርቲዎች በጥምረት ኮሚቴ አደራጅተው እየሰሩ መሆናቸውን የገለፁት የኮሚቴው አስተባባሪ አቶ አስራት ጣሴ፤ ፓርቲዎቹ ነገ በመኢአድ ጽሕፈት ቤት “በቃ እንበል” የተሰኘ ህዝባዊ ስብሰባ እንደሚያካሄዱ አስታወቁ፡፡  ለህዝባዊ ስብሰባው “በቃ እንበል” የሚል መሪ ቃል ለምን እንደተመረጠ አቶ አስራት ሲያስረዱ፣ ህዝቡ የአገሪቱን ችግሮች የማስቆምና የማስወገድ አቅም እንዳለው የሚያሳይ አባባል መሆኑን ተናግረዋል፡፡  ህዝቡ ምን ቢያደርግ ችግሮችን መፍታት እንደሚችል መወያየትና መላ ማበጀት የስብሰባው አላማ እንደሆነ አቶ አስራት ጠቅሰው፤ ችግሮችን ለማስወገድ “በቃ እንበል” የሚል አቋም እንደያዙ ተናግረዋል፡፡  ገዢዎቻችን ፍርሃት ይፈጥሩብናል፤ ነገር ግን በጋራ “በቃ” ካልን ያበቃል፤ እናም በሰላማዊ ትግል የመብታችን ባለቤት እንሆናለን ብለዋል-አቶ አስራት፡፡ ሙስናን በጋራ በቃ ካልን፣ ሙስና አብቅቶ ጤናማ የስራና የንግድ ውድድር ይፈጠራል በማለትም ስብሰባው የአገሪቱ ዋና ዋና ችግሮችን እንደሚዳስስ አስረድተዋል፡፡  ኢፍትሃዊነትንና ውርደትን በጋራ በቃ ካልን ያበቃል፤ ፍትህ ከመንበሯ ላይ ተቀምጣም ክብራችን ይመለሳል ያሉት አቶ አስራት፤ በእምነት ነፃነት ላይ ጣልቃ መግባትንና በሽብር ስም በሀሰት መወንጀልን በቃ ካልን ያበቃል፤ መብታችን ይከበራል፤ እንደየእምነታችንም በነጻ እናመልካለን ብለዋል፡፡ በጥምረት እየሰሩ ያሉት 33ቱ ፓርቲዎች በጋራ የሚሰሩት ይህን አቋም በመያዝ እንደሆነም አስተባባሪው ተናግረዋል፡፡ የገዢውን ፓርቲ የዘረኝነት፣ የመከፋፈልና የማጋጨት ፖሊሲ በቃ ካልን ያበቃል፣ በምትኩም ትብብር ይነግሳል ሲሉ የፓርቲዎቹን አቋም የገለፁት አቶ