Posts

Year after leader dies, Ethiopia little changed

Image
ADDIS ABABA, Ethiopia (AP) — Residents in Ethiopia's capital awoke to the sound of a 21-gun salute Tuesday to mark the first year anniversary of the death of long-time ruler Meles Zenawi. The ritual underscores the approach Meles' successors have employed during the last year: a continued lionization of the late prime minister, whose portrait still appears in every public office across the country. Candlelit vigils and the launch of over two dozen parks were organized across the country for the late leader. In the capital a cornerstone for the Meles Zenawi Memorial Museum was laid in a televised ceremony. During the ceremony, attended by regional leaders such as the presidents of Somalia and Sudan, Meles was praised as "Africa's voice." His successor Prime Minister Prime Minister Hailemariam Desalegn praised Meles as a "champion of the poor." "Meles did a remarkable endeavor in the green economic development. He also led a successful par

ካላ በቀለ ዋዪ የቀድሞ የሲዳማ ኣርነት ንቅናቄ ከፍተኛ ኣመራር ከሰይፌ ነበልባል ሬድዮ ጋር በወቅታዊ የሲዳማ ፖለቲካዊ ጉዳይ ላይ ያደረጉትን ቃለ ምልልስ በተመለተከ ያላችሁን ጥያቄ እና ኣስተያየት ይላኩልን

Image
ፎቶ  https://www.facebook.com/bekele.wariyo/photos ካላ በቀለ ዋዪ የቀድሞ የሲዳማ ኣርነት ንቅናቄ ከፍተኛ ኣመራር ከሰይፌ ነበልባል ሬድዮ ጋር በወቅታዊ የሲዳማ ፖለቲካዊ ጉዳይ ላይ ያደረጉትን ቃለ ምልልስ በተመለተከ ያላችሁን ጥያቄ እና ኣስተያየት በሚከተለው ኣድራሻ ይላኩል፤ ምላሻቸውን ጠይቀን እናቀረባለን፦ nomonanoto@gmail.com  እናመሰግናለን።  ካላ በቀለ ዋዪ በቃለ ምልልሱ የተነሱ ኣንኳር ጉዳዮች በሲዳማ ህዝብ ላይ የሚደርስውን ኣስተዳደራዊ በደል  የሲዳማ ህዝብ የመልካም ኣስተዳደር  ጥያቄ የሲዳማ ህዝብ የራስ ገዝ የክልል ኣስተዳደር ጥያቄ በመንግስት ሰለመታፈን   ካላ በቀለ ዋዪ በወቅታዊው የሲዳማ የፖለቲካ ሁኔታ እና የክልል ጥያቄ በተመለከተ ከሰይፌ ነበልባል ሬድዮ ጋር ያደረጉት ቃለ ምልልስ

እነ “ሻኪራ” በአሞራ ገደል

Image
የዛሬ ሳምንት ሀዋሳ ነበርኩኝ፡፡ የወትሮዋ ሳቂታዋ ሀዋሳ አልነበረችም፡፡ አኩርፋለች፡፡ ሌላ ችግር ገጥሟት ግን አይደለም፡፡ ክረምቱ ነው ያስኮረፋት፡፡ ዝናቡ፣ ቅዝቃዜውና ደመና የሸፈነው ሰማይ ተጫጭነዋት ነበር፡፡ እንደኔ እንደኔ ሀዋሳ ደርሶ አሞራ ገደልን ሳይጐበኙ መመለስ ካለመሄድ እኩል ነው፡፡ እዚህ ስፍራ ዓሳ እንደጉድ ይበላል፡፡ ያውም ቁጥር - ልክ እንደ ስጋ፡፡ የአሳ ቁርጥ ተመጋቢዎች በእንጨት ግድግዳ በተከበበው ዳስ መሳይ ቤት ውስጥ ግፊያውና መረጋገጡን ተያይዘውታል፡፡ በሀዋሳ ሀይቅ ዳር ባለው በዚህ ስፍራ ሰው ከአንድ ቦታ አሳውን ይገዛና እዛው ዳስ ቤት ውስጥ የአሳውን እሾክ እያስወጣ ቁርጡን በሳህን እየያዘ ማባያውን ለማግኘት ሁለት ጐን ለጐን የተቀመጡ ማባያ አቅራቢዎች ጋር መገናኘት ይጠበቅበታል፡፡ አንዱ “ዳጣ” የተባለው እና ከሚጥሚጣ እንዲሁም ከሌሎች ቅመሞች የተሰራ የሚያቃጥል ማባያ ሲሆን (እኔ በጣም ከማቃጠሉ የተነሳ “እንላቀስ” ብየዋለሁ) ሁለተኛው ትንንሽ ክብ የበቆሎ ቂጣዎች ናቸው፡፡ ሁለት ወጣቶች የአሳ ቁርጥ ከግፊያው ውስጥ ይዘው ወጥተው አንዱ ሌላውን፣ “ሂድና ሲዲ ይዘህ ና፣ ታዲያ ስክራች እንዳይኖረው” ሲል አስጠነቀቀው፡፡ ሲዲ ምንድነው ስል ጠየቅሁት አንዱን ወጣት፡፡ “ሲመጣ ታይዋለሽ” አለና ዳጣ ሊያስጨምር መስከረም ወደ ተባለች ዳጣ ሻጭ አመራ፡፡ እኔም ስክራች እንዳይኖረው የተባለውን ሲዲ በጉጉት መጠበቅ ጀመርኩ፡፡ ለካስ ሲዲ የሚሉት የበቆሎውን ቂጣ ነው፡፡ “ስክራች” የተባለው ደግሞ ያረረ እና የተሰነጣጠቀ እንዳይሆን ለማለት የተጠቀሙበት አገላለፅ ነው፡፡ ከወጣቶቹ የእንብላ ግብዣ ቀረበልኝ፡፡ የአሳ ቁርጥ በልቼ ስለማላውቅ ብፈራም “ሲዲ”ውን በዳጣ ግን አልማርኩትም፡፡ ወጣቶቹ ቁርጡን እየበሉ ሳሉ አንዱ “ሲዲውን በርን (burn)

በሲዳማ ዞን ከ424 ሺህ ለሚበልጡ ህፃናት የተለያዩ በሽታዎች መከላከያ ክትባት ተሰጠ ተባለ

ሃዋሳ ነሐሴ 15/2005 በሲዳማ ዞን በተጠናቀቀው የበጀት አመት ከ424 ሺህ ከሚበልጡ ህፃናት የተለያዩ በሽታዎች መከላከያ ክትባት መሰጠቱን የዞኑ ጤና መምሪያ አስታወቀ ። በመምሪያዉ የጤና ልማት እቅድ የስራ ሂደት ኦፊሰር አቶ አበበ በካዬ ሰሞኑን ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጡት መንግሰት ለህፃናትና እናቶች ጤና መጠበቅ በሰጠው ትኩረት በሽታን አስቀድሞ የመከላከሉ ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል ። በዞኑ 19 ወረዳዎችና ሁለት የከተማ አስተዳደሮች እድሜያቸው ከአንድ አመት በታች ለሆናቸዉ 424 ሺህ 126 ህፃናት የፖሊዮ ፣ የቲቢ፣ የኩፍኝና የሳንባ ምች በሽታ መከላከያ ክትባት መሰጠቱን አስታዉቀዋል ። በዞኑ በመደበኛ የክትባት አገልግሎት በበጀት አመቱ 105 ሺህ 910 ህፃናት መከተባቸውንም አስረድተዋል። በተጨማሪ 15 ሺህ ለሚሆኑ ከፍተኛ ምግብ አጥረት ችግር ላለባቸው ነፍስጡር እናቶችና ህፃናት የተለያዩ አልሚ ምግቦች እንደተሰጣቸውና ከ 80 ሺህ ለሚበልጡ ህፃናት የቫይታሚን ኤ እደላ መደረጉንም አስረድተዋል። http://www.ena.gov.et/Story.aspx?ID=11072&K=1

የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ኅብረትና የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራቲክ ፓርቲዎች ውህደት ፈፀሙ

አዲስ አበባ ነሐሴ 15/2005 የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ኅብረትና የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራቲክ ፓርቲዎች ውህደት መፈጸማቸውን ትናንት አስታወቁ። የኢትዮጵያ ማሕበረ ዴሞክራሲ-ደቡብ ኅብረት አንድነት ፓርቲ (ኢማዴ-ደህአፓ) በሚል አዲስ ስያሜ ውህደቱን ይፋ ያደረገው ይኸው ፓርቲ የፀረ-ሽብር ሕጉን እንደሚቃወም አስታውቋል። የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጥላሁን እንደሻው ውህደቱን አስመልክቶ በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንዳሉት ሁለቱ ፓርቲዎች በአገሪቱ ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ዙሪያ በነበራቸው የጋራ አቋም ራዕያቸውን በጋራ ለማሳካት ጥረት ሲያደርጉ ቆይተዋል። የኢትዮጵያ ማሕበረ ዴሞክራሲ-ደቡብ ኅብረት አንድነት ፓርቲ (ኢማዴ-ደህአፓ) ሕጋዊ ሰውነት እንዲያገኝ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጥያቄ በማቅረብ ቦርዱ ሰኔ 3 ቀን 2005 ዓ.ም የሕጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት መስጠቱን ገልጸዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ውህደቱን በትናንትው ዕለት ይፋ ያደረገው ይኸው ፓርቲ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፀድቆ በአገሪቱ ተግባራዊ የሆነውን የፀረ-ሽብር ሕግን እንደሚቃወም አስታውቋል። እንደ አቶ ጥላሁን ገለፃ የፀረ-ሽብር ሕጉ ሠላማዊ የሕዝቦች ተቃውሞን የማፈን ባህሪይ ስላለው ፓርቲያቸው እንደ ሌሎች የመድረክ አባላት ሁሉ ሕጉን ይቃወማል። ፓርቲው በማኒፌስቶው በግልጽ እንዳስቀመጠው የፀረ-ሽብር ሕጉ የዜጎችን ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶችን የሚጋፋ በመሆኑ ሕጉን አጥብቆ እንደሚቃወም ገልጸዋል። በዚህም በኢትዮጵያ ሕገ-መንግሥታዊ ፍርድ ቤት እንዲቋቋም ፓርቲው ከመፈለግ ባሻገር ትግል እንደሚያደርግ አስረድተዋል። የኢትዮጵያ ማሕበረ ዴሞክራሲ-ደቡብ ኅብረት አንድነት ፓርቲ የኃይማኖት አክራሪነትን፣ የኃይማኖታዊ መንግሥት መቋቋምን እንዲሁም ኃይማ