Posts

ኮሚሽኑ የተሿሚዎችን፣የተመራጮችንና የመንግሥት ሠራተኞች የሀብት ምዝገባ የሚይዝበትን ስምምነት ተፈራረ

Image
አዲስ አበባ ነሐሴ 14/2005 የፌዴራል የሥነ ምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የተሿሚዎችን፣የተመራጮችንና በሕግ ግዴታ የተጣለባቸውን የመንግሥት ሠራተኞች የሀብት ምዝገባ በመረጃ ቋት የሚይዝበትን ስምምነት ከአንድ ኩባንያ ጋር ዛሬ ተፈራረመ። ኮሚሽኑ ሲ ኤስ ኤም ሳይበርቴክ ሶፍት ዌር ኤንድ መልቲ ሚዲያ ከተባለው የሕንድ የግል አማካሪ ተቋም ጋር የተደረገው ስምምነት ለሀብት ምዝገባው የሚያስፈልገውን ሶፍት ዌር ለማሰራት ያስችላል። ለፍትህ ሥርዓት ማሻሻያ ሥርዓት ከተመደበው 198ሺህ 530 ዶላር ድጋፍ የሚሰራው ሶፍት ዌር በፌዴራል ደረጃ የተመዘገቡ 60ሺህ አስመዝጋቢዎችን ሀብት ምዝገባ ውጤት ለሕዝብ ክፍት እንደሚያደርግም ኮሚሽኑ አመልክቷል። የሶፍት ዌር ሥራው ሲጠናቀቅ በሀብት ምዝገባው ዓዋጅ መሠረት ውጤቱን ለሕዝብ ተደራሽ ለማድረግ ከማገዙም በላይ፤በቀጣይ ሀብታቸውን የሚያስመዝግቡ ግለሰቦች ባሉበት ሆነው የመመዝገቢያውን ቅጽ በማውጣት መመዝገብ ይችላሉ። ኮሚሽኑ ከክልሎች የሥነ ምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽኖች ጋር ያለውን የመረጃ ልውውጥ እንደሚያቀላጥፈው መግለጹን የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዘገባ አስታውቋል። http://www.ena.gov.et/Story.aspx?ID=11046&K=1

ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ውግዘትና የመንግሥት ክርክር

በመስፍን መንግሥቱ ኢሕአዴግ ሥልጣን ከያዘበት ጊዜ ጀምሮ መንግሥት በዓለም አቀፍ ሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች የገዛ ዜጎቹን መብቶች ያለገደብ የሚጥስና ሰብዓዊ መብት የሚጥስ እየተባለ ያልተከሰሰበት ጊዜ የለም ማለት ይቻላል፡፡ ይሁን እንጂ ይህ መንግሥት በዜጎች ላይ ይፈጽመዋል በሚባለው የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ዓለም አቀፍ ትኩረትን በሚመለከት የመጀመሪያ ምዕራፍ አይደለም፡፡ የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ መንግሥት ከተገረሰሰ በኋላ በኢትዮጵያ የተፈጸሙ የዜጎች ጅምላ ግድያዎችን ዓለም በከፍተኛ መገረም ተከታትሎ አውግዟቸዋል፡፡ ፕሬዚዳንት መንግሥቱ ኃይለ ማሪያም አገዛዛቸው በኢትዮጵያ የከፍተኛ ጭካኔና የመብት ጥሰት ዘመን ሆኖ በዓለም አቀፍ ደረጃ ባተረፈው ታዋቂነት ምክንያት የውግዘት ዒላማ ሆኖ አልፏል፡፡  የደርግ መውደቅ በኢትዮጵያ በዚህ ረገድ የፍፃሜ ምዕራፍ ይሆናል ተብሎ ተስፋ ተደርጎ ነበር፡፡ ነገር ግን አልሆነም፡፡ ከኢሕአዴግ ወደ ሥልጣን መምጣት በኋላም ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች በተለይም ሒዩማን ራይት ዎችና አምነስቲ ኢንተርናሽናል ያኔ አዲስ የነበረውን የኢትዮጵያ መንግሥት በሰብዓዊ መብት ጥሰት በማብጠልጠል ነበር የተቀበሉት፡፡ ባለፉት ሃያ ዓመታት ይህ ሥራቸው ሆኖ ዘልቋል፡፡ ጋዜጠኞችን ከመንግሥት ጥቃት በመከላከል ላይ የተሰማሩ ዓለም አቀፍ ድርጀቶችም የኢትዮጵያን መንግሥት በየጊዜው መክሰስ ሥራቸው ሆኗል፡፡ ከእነኝህ ዓለም አቀፍ  ድርጅቶች በተጨማሪ የአሜሪካ  መንግሥት ውጭ ጉዳይ መሥርያ ቤትም በየጊዜው በሚያወጣው ዓመታዊ መግለጫው የኢትዮጵያ መንግሥትን በሰብዓዊ መብት ጥሰትና የፖለቲካ መብቶችን ማፈን ሳይከስ ያለፈበት ጊዜ የለም፡፡ አሁን አሁን የእነኚህን አካላት መግለጫዎች የታወቁ ዓለም አቀፍ መገናኛ ድርጅቶች በመቀባበል

Ethiopia's Consumer Price Rose to 8% in July

Image
Monday, 19 August 2013 15:33 Ethiopia's consumer price rose to 8 percent in July up from 7.4 percent in June, Fortune reported citing the latest Consumer Price Index released by the Central Statistical Agency. The year-on-year food inflation in July was 5.8 percent from 3.7 percent in June, while non-food inflation was 10.5 percent in July from  11.9 percent in June. The increment in non-food inflation was primarily fueled by rise in prices of clothing & footwear, firewood, household goods and furnishings. Ethiopia's year-on-year inflation has dropped to single digits starting from March this year, inflation has started to climb steadily after two months. Source: Fortune

Los Angeles’ Little Ethiopia Prepares for 2013 Cultural Street Festival

Image
Tadias Magazine By Aida Solomon Published: Monday, August 19, 2013 Los Angeles  (TADIAS) – It was 11 years ago this month on August 7, 2002 that the city of Los Angeles designated through a unanimous council vote that the neighborhood on Fairfax Avenue, between Olympic and Pico Boulevard, be recognized as Little Ethiopia, making it the first street in the United States to be named after an African nation. For the last 12 years the Little Ethiopia Business Association has been hosting a popular cultural street festival that attracts a diverse crowd from L.A. and beyond to the area. Organizers say this year’s celebration is scheduled to take place on Sunday, September 8th, 2013 between Olympic and Whitworth Avenue with events including live music, vendors, fashion show, comedy, and much more. The 2013 festival will also feature Alemtsehay Wodajo, an accomplished actress, poet and songwriter, as well as city and state officials. According to Berhanu Asfaw, President of the Lit

የ10ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ለማየት ያጋጠመው ችግር እየተቃለለ ነው

Image
ሀገር  አቀፍ  የትምህርት  ምዘናና  ፈተናዎች  ኤጀንሲ  የ 2005  ዓም  የትምህርት  ዘመን  የሁለተኛ  ደረጃ ትምህርት  ማጠናቀቂያ  ፈተና  ውጤት  11/12/2005  ከቀኑ  10  ሰዓት  ጀምሮ  ይፋ   መሆኑን  አስታውቆ ነበር፡፡  ተፈታኞቹ  ውጤታቸውን  በተቋሙ  ድረ  ገፅ  በ www.nae.gov.et   እና  በተንቀሳቃሽ  ስልካቸው አጭር  መልዕክት  በመላከ  ማወቅ  እንደሚችሉ  ገልፆ ነበር፡፡ ይሁንና የተወሰኑ ተጠቃሚዎች መረጃውን ያገኙ ቢሆንም በርካታ ተጠቃሚዎች ግን ወደ ኢሬቴድ በመደወል የተባለውን መረጃ ለማግኘት እንደተቸገሩ ነግረውናል፡፡ በጉዳይ ላይ ማብራሪያ የጠየቅናቸው የኤጀንሲው የስራ ሃላፊ ችግሩ ሁሉንም ጠያቂዎች ባንድ ላይ ማስተናገድ ባለመቻሉ የተፈጠረ ነው ብለዋል፡፡ ሃላፊው እንዳሉት አሁን በአጭር የስልክ መልዕክት መረጃውን የሚያደርሰው የመረጃ ቋት በአንድ ደቂቃ ማስተናገድ የሚችለው ከ5ሺ እስከ 7ሺ ጥያቄዎችን ነው፡፡ ይሁንና ወደ መረጃ ቋቱ ከ 20ሺ በላይ ጥያቄዎች በአንድ ደቂቃ ዉስጥ ይደርሳሉ፡፡ ለአንድ ተማሪ ዉጤት ከ20 እስከ 30 ሰዎች ያክል ጥያቄ ማቅረባቸው ደግሞ ችግሩን አባብሶታል ብለዋል ሃላፊው፡፡ ይህም በማዕከሉ ላይ መጨናነቅ በመፍጠሩ በርካታ ተጠቃሚዎች አገልግሎቱን እንዳላገኙ ተረድተናል ብለዋል፡፡ በድረ ገፅ የሚጠቀሙ ያጋጠማቸው ችግር አሁን ሙሉ በሙሉ የተቃለለ በመሆኑ  ተፈታኞቹ  ውጤታቸውን  በተቋሙ  ድረ  ገፅ  በ www.nae.gov.et  አሁን ጀምረው ማየት እንደሚችሉ ተናግረዋል፡፡ በአጭር ስልክ መልዕክት የሚጠቀሙ መጨናነቁ አሁን እየተቃለለ በመሆኑ በትዕግስት እንዲጠብቁ ጠይቀዋል፡፡  የአጭር  መልዕክቱን    rtn  ብለው  ከፃፉ  በኋላ  የመፈተኛ    የመለያ  ቁጥር በማስገባት