መሬትን ሳያርሱ በማልማት በምርምር የተገኘውን ተሞክሮ ወደ አርሶ አደሩ ለማስፋት የሚያስችል መድረክ ተመሰረተ
ሃዋሳ ነሐሴ 8/2005 በወንዶ ገነት ግብርና ምርምር ተቋም የሃዋሳ መለስተኛ የበቆሎ ምርምር ማዕከል መሬትን ሳያርሱ የማልማት ምርምር ስራ የተገኘውን ተሞክሮ ወደ አርሶ አደሩ ለማስፋት የሚያስችል የባለ ድርሻ አካላት የጋራ መድረክ ተመሰረተ ። መሬትን ሳያርሱ የማልማት ምርምር ስራዉን ወደ አርሶ አደሩ ለማስፋት እንዲቻል የጋራ መድረኩ የተመሰረተዉ ትናንት በሃዋሳ በተካሄደ ምክክር ላይ ነዉ ። በሀዋሳ የበቆሎ ምርምር መለስተኛ ማዕከል ዳይሬክተርና የምርምር ፕሮጀክቱ አስተባባሪ አቶ ጎሽሜ ሙሉነህ በዚሁ ጊዜ እንደተናገሩ ምርምሩ ኢትዮጵያን ጨምሮ በምስራቅና ደቡብ አፍሪካ በሚገኙ አምስት ሀገራት እየተካሄደ ነዉ ። መሬትን ሳያርሱ በማልማት በምርምር በተገኘው ተሞክሮ የቦሎቄና በቆሎን ምርታማነት በማሳደግ በምግብ ሰብል ራስን ለመቻል ያለመ ነው ብለዋል ። በክልሉ ሲዳማ ዞን በአንድ ወረዳ ከሁለት ዓመት በፊት በአምስት አርሶ አደሮች የተጀመረው መሬትን ሳያርሱ የማልማት የግብርና የምርምር ስራ በተጨማሪ በአራት ወረዳዎች በማስፋት ምርምሩ ውጤታማ እንደሆነም ተገልጧል ። የምርምር ማዕከሉ የቦሎቄና በቆሎ ተረፈ ምርት በማሳው ላይ እንዳለ በማቆየት የአፈር ለምነትን በመጠበቅ ምርታማነትን ማሳደግ እነደሚቻልም መረጋገፈጡ ተገልጧል ። በሀገራችን በተለያዩ አካባቢዎች እስካሁን እየተሰራበት ያለ መሬትን ሳያርሱ የማልማት ልማዳዊ አሰራር ቢሆንም ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ በመጠቀም ቢሰራበት ምርታማነትን ከማሳደግ ባለፈ ለአፈር ለምነት የሚኖረው ጠቀሜታ የጎላ መሆኑን አቶ ጎሽሜ ተናግረዋል። በደቡብ ክልል በሀድያ ሲዳማና ጉራጌ ዞኖች የሚገኙ የሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ፣ የሎካ አባያ የቦርቻ የመስቃንና የምስራቅ ባድዋቾ ወረዳዎች በምርምሩ መታቀፋቸዉንና ባለፉት ሶስስት ዓመታት የተገኘው ውጤት አርሶ