የፍቼ ጫምበላላ በሃዋሳ ተከበረ
የሲዳማ ብሔር ባህል፣ ቋንቋና ታሪክን ጠብቆ በማስተዋወቅ የቱሪዝም ኢንዱስትሪውን ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት ሁሉም ባለድርሻ አካላት ድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አስገነዘቡ፡፡ የሲዳማ ብሔር ዘመን መለወጫ ፍቼ ጫምባላላና የብሔሩ 19 ኛው የቋንቋና ባህል ሲምፖዚየም ትናንትናና ከትናንት በስቲያ በሃዋሳ በድምቀት ተከብሯል፡፡ የሲዳማ ብሔር የዘመን መለወጫ ጫምባላላ ባህላዊ የአከባበር ሥነ ሥርዓትን በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት ( ዩኔስኮ ) ለማስመዝገብ የቅድመ ዝግጅት ሥራ በመጠናቀቅ ላይ መሆኑም ተገልጿል፡፡ ርዕሰ መስተዳድሩ ደሴ ዳልኬ እንደገለጹት፣ የሲዳማ ህዝብ ለረጅም ዓመታት ማንነቱ፣ ባህሉና ቋንቋው ተረስቶ መቆየቱን በማስታወስ ባለፉት 21 ዓመታት ሥርዓቱ ባመጣው መልካም አስተዳደር ባህሉና ቋንቋው ተክብሮ የመናገር፣ የመዳኘትና የመማር ዕድል ባለቤት ለመሆን በቅቷል፡፡ የብሔሩን ባህል፣ ቋንቋ፣ ታሪክና ቅርስን በማጥናትና በማልማት የበለጸገና ያደገ ህብረተሰብ ለመፍጠርና የቱሪዝም ኢንዱስትሪውን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ የሲዳማ ብሔር ከሌሎች የሀገሪቱ ብሔረሰቦች ጋር አምባገነኑን ሥርዓት በመገርሰስ ልማት፣ መልካም አስተዳደርና ዴሞክራሲ እንዲሰፍን ባደረገው ትግል ያስገኘው ጣፋጭ ውጤት ለብሔሩ ቋንቋ፣ ባህልና ማንነት መከበር ጉልህ ድርሻ ማበርከቱን ተናግረዋል፡፡ በዚህ የልማት ተሳትፎና ተጠቃሚነት ከጊዜ ወደ ጊዜ በከፍተኛ ፍጥነት እያደገ መጥቷል ብለዋል፡፡ የዞኑ ህዝብ ከሌሎች የክልሉና የሀገሪቱ ብሔር ብሔረሰቦች ጋር በመቀናጀት የተጀመረውን የልማት፣ የመልካም አስተዳደርና ዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ አጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል፡፡ ቀደምት የሲዳማ