Posts

ሲዳማን ጭምሮ በደቡብ ክልል መሬትን ሳያርሱ የማልማት ዘዴ የተሳተፉ አርሶ አደሮች ከፍተኛ ምርት ማግኘታቸውን አስታወቁ

አዋሳ ሐምሌ 15/2005 በደቡብ ክልል መሬትን ሳያርሱ የማልማት ዘዴ የተሳተፉ አርሶ አደሩች ከፍተኛ ምርት ማግኘታቸውን አስታወቁ፡፡ በአውስትራሊያ መንግስት ድጋፍ በወንዶ ገነት ግብርና ምርምር ተቋም የሀዋሳ መለስተኛ የበቆሎ ምርምር ማዕከል መሬትን ሳያርሱ የማልማት ምርምር ስራ እያካሄደ ነው። በክልሉ ሀድያ፣ ሲዳማና ጉራጌ ዞኖች በሚገኙ ሶስት ወረዳዎች ከሁለት ዓመት በፊት በአምስት አርሶ አደሮች የተጀመረው መሬትን ሳያርሱ የማልማት የዕቀባ ግብርና በተያዘው ዓመት በ200 አርሶ አደሮች እየተከናወነ ይገኛል። ትናንት በምስራቅ ባድዋቾ ወረዳ ጨፋ 01 ቀበሌ በተከናወነ የመስክ ቀን ላይ ማሳቸው የተጎበኘላቸውና በምርምሩ የታቀፉ አርሶ አደሮች እንደገለጹት በግብርና ምርምር ተቋሙ በተደረገላቸው ድጋፍ መሬት ሳያርሱ በቆሎና ቦሎቄ በማልማት ቀደም ሲል ከሚያገኙት ምርት ብልጫ ያለው መሰብሰብ ችለዋል። አርሶ አደር ሞላ አመሌና እንደገለጹት በምርምሩ ታቅፈው መሬት ሳያርሱ በማልማታቸው ቀደም ሲል በሄክታር ሲያገኙ ከነበረው ምርት በ50 በመቶ ብልጫ ያለው ምርት ማግኘት እንደቻሉ ገልጸዋል። መሬት ሳያርሱ ለዘር የሚሆን መስመር በማዘጋጀት ብቻ የበቆሎና ቦሎቄ በማሰባጠር ዘርተው ቦሎቄ አንድ ዙር እንደሰበሰቡና በቆሎው እስኪደርስ ድረስ ሁለተኛ ዙር ቦሎቄ ዘርተው ቡቃያው በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ሌላው ወጣት አርሶ አደር ደግነት ደሳለኝ በበኩሉ እንዳለው ሳያርሱ በመዝራት ዘዴ አሰባጥሮ በማልማት የመሬቱን ለምነት መጠበቅ እንደሚቻል በተደረገው ምርምር ያገኘውን ዕውቀት መሰረት አድርጎ ወደ ልማቱ መግባቱንና በቆሎ ተሰብስቦ እስኪያልቅ በስሩ ቦሎቄ ሁለት ጊዜ በማምረት የቦሎቄ ዘር በማቅረብ ተጠቃሚ መሆን ችሏል። የቤተሰቡ የእርሻ ማሳ በከፍተኛ ደረጃ በጎርፍ የሚጠቃና ውሃ ይ

የአውሮፓ ኅብረት የፓርላማ ቡድን በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት አሳሳቢ ነው አለ

Image
-    የቃሊቲን እስር ቤት እንዳይጎበኝ መከልከሉን ገለጸ  ለሦስት ቀናት በኢትዮጵያ ጉብኝት ያደረገው የአውሮፓ ኅብረት ፓርላማ የሰብዓዊ መብቶች ንዑስ ኮሚቴ በአገሪቱ ውስጥ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት አሳሳቢ ደረጃ መድረሱን አስታወቀ፡፡ ጋዜጠኞችና የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት በአስቸኳይ እንደፈቱም ጠይቋል፡፡ ከሐምሌ 8 እስከ 10 ቀን 2005 ዓ.ም. በኢትዮጵያ ጉብኝት ያደረገው የአውሮፓ ኅብረት የልዑካን ቡድን፣ በኢትዮጵያ የነበረውን ጉብኝት ካጠናቀቀ በኋላ ሰሞኑን በሒልተን ሆቴል በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ነበር ይህንን የገለጸው፡፡  እንደ ቡድኑ ድምዳሜ በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና ዕንባ ጠባቂ ተቋም መቋቋማቸውና በቅርቡ የፀደቀው አገራዊ የሰብዓዊ መብት መርሐ ግብር የሚበረታታ ዕርምጃ መሆኑን ገልጾ፣ መንግሥት ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት እየፈጸመ መሆኑን አስረድቷል፡፡  ከመንግሥትና ከተቃዋሚ ተወካዮች እንዲሁም ከሲቪል ማኅበረሰብ አካላት ጋር ሰፋ ያለ ምክክርና ውይይት ያደረገው ቡድኑ፣ በአገሪቱ ዲሞክራሲ ማበብ ከፍተኛ ሚና ይጫወታሉ ተብሎ የሚተመንባቸው ነፃ ሚዲያና ሲቪክ ማኅበረሰባት በከፍተኛ ደረጃ እንዳይሠሩ የተደረጉ መሆናቸውን ገልጿል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ፀረ ሽብረተኝነት አዋጁን ጨምሮ የአገሪቱን የፖለቲካ ድባብ አፍነው ይዘውታል ያሉዋቸው ሕጎች እንዲከለሱ ቡድኑ መንግሥትን ጠይቋል፡፡ ለዚህም በእስር ላይ የሚገኙት የተቃዋሚ ፓርቲዎች አባላትና ጋዜጠኞች ሐሳባቸውን በነፃነት የመግለጽ መብታቸውን በመጠቀማቸው ለእስር የተዳረጉ መሆናቸውን በመግለጽ፣ በአስቸኳይ እንዲፈቱ መንግሥትን ጠይቋል፡፡ እስረኞችን በመጎብኘት የመጀመርያ መረጃ ለማግኘት አቅዶ እንደነበረ ያስታወቀው ቡድኑ፣ ቃሊቲ እስር ቤትን እንዳይጎበኝና እስረኞችን

ሃዋሳን ጨምሮ “አንድነት” በህዝብ ጥያቄ በ16 ከተሞች የተቃውሞ ሰልፍና ስብሰባ እጠራለሁ አለ

ባለፈው ሳምንት በጐንደርና በደሴ ሠላማዊ ሰልፍ ያካሄደው አንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ፤ ተመሳሳይ ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ ለማካሄድ ከበርካታ ከተሞች የህዝብ ጥያቄ እንደቀረበለት በመጥቀስ በ16 ከተሞች የተቃውሞ ሰልፉንና ህዝባዊ ስብሰባዎች ለማካሄድ እንደወሰነ ገለፁ፡፡ በአዲስ አበባ ሐምሌ 28 ቀን ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ ታቅዶ እንደነበር የተናገሩት የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊው አቶ ዳንኤል ተፈራ፣ ከጐንደርና ከደሴ የተቃውሞ ሰልፍ ጋር ተመሳሳይ ሰልፍ ለማካሄድ ከተለያዩ የኦሮሚያና የደቡብ አካባቢዎች ተደጋጋሚ የህዝብ ጥያቄ ስለቀረበለት ፓርቲው አዲስ ፕሮግራም ለማውጣት እንደወሰነ ተናግረዋል፡፡ የአዲስ አበባውን ለማዘግየትና መስከረም 5 ቀን 2006 ለማድረግ እንደታሰበ ነግረውናል፡፡ በደቡብ በኦሮሚያ፣ በትግራይ፣ በአማራ፣ በቤንሻንጉል፣ በጋምቤላ እና በሀረሪ ክልሎች ተከታታይ ሠላማዊ ሠልፎችና የአደባባይ ስብሰባዎችን ለማካሄድ ፓርቲው ወስኗል ያሉት አቶ ዳንኤል፤ የአዲስ አበባው ሰላማዊ ሰልፍ ወደ መስከረም ተራዝሟል ብለዋል፡፡ ይሁንና ፓርቲው በአዲስ አበባ በቀጣዮቹ ሦስት ሳምንታት የአደባባይ ወይም የአዳራሽ ስብሰባዎችን ይጠራል ተብሏል፡፡ የፓርቲው ስራ አስፈፃሚ ሐሙስ እለት ተወያይቶ መርሃግብር እንዳዘጋጀ አቶ ዳንኤል ጠቅሰው፤ በ16 ከተሞች ሰላማዊ ሰልፍ ወይም ህዝባዊ ስብሰባ የሚካሄደው ከሐምሌ 28 ጀምሮ ነው ተብሏል፡፡ በጂንካ፣ በአርባ ምንጭና በባህርዳር ሠላማዊ ሰልፍ በሚካሄድበት በዚሁ እለት፣ በወላይታና በመቀሌ የአደባባይ ስብሰባ እንደሚዘጋጅ ተገልጿል፡፡ ነሐሴ 12 ቀን፣ በወሊሶ፣ በናዝሬት፣ በፍቼ እና በባሌ ሠላማዊ ሰልፍ እንደሚካሄድ አቶ ዳንኤል ጠቅሰው፤ ነሐሴ 26 በድሬዳዋ እና በጋምቤላ የአደባባይ ስብሰባ እንዲሁም በአሶሳ ሰላማ

ሕዝብ ‹‹ችግር ፈቺ አካልን ያየህ ወዲህ በለኝ›› እያለ ነው!

Image
በተደጋጋሚ እንደምንገልጸው በአሁኑ ጊዜ መንግሥት የሙስና ወንጀልን ለመከላከልና ሙሰኞችን ለመቅጣት አዎንታዊ እንቅስቃሴ እያደረገ ነው፡፡ መቋጫው ለፍርድ ቤት የሚተው ቢሆንም ጅምሩ የሚያበረታታ ነው፡፡ ብቃት የላቸውም፣ ሌላ ሥራ ቢሠሩ ወይም ሌላ ኃላፊነት ቢሰጣቸው ይሻላል ተብለው የሚነሱትንና የሚዛወሩትንም እያስተዋልን ነን፡፡ እንቅስቃሴው የሚመዘነው በውጤቱ ቢሆንም ደፈርና ፈጠን ብሎ ዕርምጃ ለመውሰድ መራመዱ ራሱ በአዎንታ የሚታይ ነው፡፡   ይህንን የመንግሥት እንቅስቃሴ በትኩረት እየተከታተለ ያለው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ከእንቅስቃሴው ጋር በተያያዘ ለመንግሥት አንድ ግልጽና ግልጽ የሆነ ጥያቄ እየቀረበ ነው፡፡ ‹‹እነዚህ ሙሰኞች፣ ወንጀለኞች፣ ብቃት የለሽ ሹሞች በሥልጣን ላይ በነበሩበት ጊዜ የፈጸሙብኝ በደል መፍትሔ ያገኛል ወይ?›› የሚል ግልጽ ጥያቄ ነወ፡፡ ሙሰኞችም፣ አቅመ ቢሶችም፣ አስመሳዮችም፣ ፀረ ሕዝቦችም ሌሎች ሌሎች ወንጀለኞችም ሥራቸውን በሚገባ አልሠሩም ሲባል ትርጉሙ ግልጽ ነው፡፡ ሕግ ጥሰዋል፣ የሕዝብ ጥያቄ አልመለሱም፣ የሕዝብ ቅሬታ አልተቀበሉም፣ በሕዝብ የተሰጣቸውን ኃላፊነት አልተወጡም ማለት ነው፡፡ ይህ ማለትም በእነሱ ምክንያት ሕዝብ በደል ደርሶበታል ማለት ነው፡፡   በመሆኑም እነሱ ከሥልጣናቸው ሲነሱ፣ ሲታሰሩና ሲጠየቁ ለመሆኑ የፈጸሙት ምንድነው? ያደረሱት በደል ምንና ምን ያህል ነው ተብሎ ይመረመራል? የፈጠሩትን ችግር የሚፈታ ዕርምጃ ይወሰዳል? ወይስ እነሱ ይነሳሉ፣ በደልም ይረሳል፣ ሰሚ እንዳጣ ይቀጥላል ማለት ነው? መንግሥት እየወሰደው ካለው ዕርምጃ ጎን ለጎን ‹‹ችግር ፈቺ አካል›› ማቋቋም አለበት፡፡ ችግርና አቤቱታ እየመረመረ መፍትሔ የሚሰጥ ቡድን ወይም አካል ሊያቋቋም ይገባል፡፡ አለበለዚያ ‹‹ጉልቻ ቢቀያየር ወጥ አያጣፍጥም

በቅርቡ በምካሄደው የሲዳማ ዞን ምክር ቤት ጉባኤ ላይ የዞኑ ካቢኔ ሽግሽግ እንደምኖር ተሰማ

Image
ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ለወራንቻ ኢፎርሜሽን ኔትዎርክ እንደተናገሩት የሲዳማ ዞን ኣሰተዳደር ኣቶ ሚሊዮን ማቲዎስ በሃዋሳ ከተማ ከንቲባ በኣቶ ዮናስ ዮሰፍ ይተካሉ ተብሏል። በኣቶ ዮናስ ቦታ የሃዋሳ ከተማ ኣዲስ ከንቲባ የምሾምላት ሲሆን የወቅቱ የከተማዋ ትምህርት መምሪያ ሃላፊ ኣቶ ቃሬ የከተማዋ ከንቲባ ይሆናሉ ተብሎ ይጠበቃል። ዝርዝሩን እንደደረሰን እናቀርባለን