Posts

ሃዋሳን ጨምሮ “አንድነት” በህዝብ ጥያቄ በ16 ከተሞች የተቃውሞ ሰልፍና ስብሰባ እጠራለሁ አለ

ባለፈው ሳምንት በጐንደርና በደሴ ሠላማዊ ሰልፍ ያካሄደው አንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ፤ ተመሳሳይ ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ ለማካሄድ ከበርካታ ከተሞች የህዝብ ጥያቄ እንደቀረበለት በመጥቀስ በ16 ከተሞች የተቃውሞ ሰልፉንና ህዝባዊ ስብሰባዎች ለማካሄድ እንደወሰነ ገለፁ፡፡ በአዲስ አበባ ሐምሌ 28 ቀን ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ ታቅዶ እንደነበር የተናገሩት የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊው አቶ ዳንኤል ተፈራ፣ ከጐንደርና ከደሴ የተቃውሞ ሰልፍ ጋር ተመሳሳይ ሰልፍ ለማካሄድ ከተለያዩ የኦሮሚያና የደቡብ አካባቢዎች ተደጋጋሚ የህዝብ ጥያቄ ስለቀረበለት ፓርቲው አዲስ ፕሮግራም ለማውጣት እንደወሰነ ተናግረዋል፡፡ የአዲስ አበባውን ለማዘግየትና መስከረም 5 ቀን 2006 ለማድረግ እንደታሰበ ነግረውናል፡፡ በደቡብ በኦሮሚያ፣ በትግራይ፣ በአማራ፣ በቤንሻንጉል፣ በጋምቤላ እና በሀረሪ ክልሎች ተከታታይ ሠላማዊ ሠልፎችና የአደባባይ ስብሰባዎችን ለማካሄድ ፓርቲው ወስኗል ያሉት አቶ ዳንኤል፤ የአዲስ አበባው ሰላማዊ ሰልፍ ወደ መስከረም ተራዝሟል ብለዋል፡፡ ይሁንና ፓርቲው በአዲስ አበባ በቀጣዮቹ ሦስት ሳምንታት የአደባባይ ወይም የአዳራሽ ስብሰባዎችን ይጠራል ተብሏል፡፡ የፓርቲው ስራ አስፈፃሚ ሐሙስ እለት ተወያይቶ መርሃግብር እንዳዘጋጀ አቶ ዳንኤል ጠቅሰው፤ በ16 ከተሞች ሰላማዊ ሰልፍ ወይም ህዝባዊ ስብሰባ የሚካሄደው ከሐምሌ 28 ጀምሮ ነው ተብሏል፡፡ በጂንካ፣ በአርባ ምንጭና በባህርዳር ሠላማዊ ሰልፍ በሚካሄድበት በዚሁ እለት፣ በወላይታና በመቀሌ የአደባባይ ስብሰባ እንደሚዘጋጅ ተገልጿል፡፡ ነሐሴ 12 ቀን፣ በወሊሶ፣ በናዝሬት፣ በፍቼ እና በባሌ ሠላማዊ ሰልፍ እንደሚካሄድ አቶ ዳንኤል ጠቅሰው፤ ነሐሴ 26 በድሬዳዋ እና በጋምቤላ የአደባባይ ስብሰባ እንዲሁም በአሶሳ ሰላማ

ሕዝብ ‹‹ችግር ፈቺ አካልን ያየህ ወዲህ በለኝ›› እያለ ነው!

Image
በተደጋጋሚ እንደምንገልጸው በአሁኑ ጊዜ መንግሥት የሙስና ወንጀልን ለመከላከልና ሙሰኞችን ለመቅጣት አዎንታዊ እንቅስቃሴ እያደረገ ነው፡፡ መቋጫው ለፍርድ ቤት የሚተው ቢሆንም ጅምሩ የሚያበረታታ ነው፡፡ ብቃት የላቸውም፣ ሌላ ሥራ ቢሠሩ ወይም ሌላ ኃላፊነት ቢሰጣቸው ይሻላል ተብለው የሚነሱትንና የሚዛወሩትንም እያስተዋልን ነን፡፡ እንቅስቃሴው የሚመዘነው በውጤቱ ቢሆንም ደፈርና ፈጠን ብሎ ዕርምጃ ለመውሰድ መራመዱ ራሱ በአዎንታ የሚታይ ነው፡፡   ይህንን የመንግሥት እንቅስቃሴ በትኩረት እየተከታተለ ያለው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ከእንቅስቃሴው ጋር በተያያዘ ለመንግሥት አንድ ግልጽና ግልጽ የሆነ ጥያቄ እየቀረበ ነው፡፡ ‹‹እነዚህ ሙሰኞች፣ ወንጀለኞች፣ ብቃት የለሽ ሹሞች በሥልጣን ላይ በነበሩበት ጊዜ የፈጸሙብኝ በደል መፍትሔ ያገኛል ወይ?›› የሚል ግልጽ ጥያቄ ነወ፡፡ ሙሰኞችም፣ አቅመ ቢሶችም፣ አስመሳዮችም፣ ፀረ ሕዝቦችም ሌሎች ሌሎች ወንጀለኞችም ሥራቸውን በሚገባ አልሠሩም ሲባል ትርጉሙ ግልጽ ነው፡፡ ሕግ ጥሰዋል፣ የሕዝብ ጥያቄ አልመለሱም፣ የሕዝብ ቅሬታ አልተቀበሉም፣ በሕዝብ የተሰጣቸውን ኃላፊነት አልተወጡም ማለት ነው፡፡ ይህ ማለትም በእነሱ ምክንያት ሕዝብ በደል ደርሶበታል ማለት ነው፡፡   በመሆኑም እነሱ ከሥልጣናቸው ሲነሱ፣ ሲታሰሩና ሲጠየቁ ለመሆኑ የፈጸሙት ምንድነው? ያደረሱት በደል ምንና ምን ያህል ነው ተብሎ ይመረመራል? የፈጠሩትን ችግር የሚፈታ ዕርምጃ ይወሰዳል? ወይስ እነሱ ይነሳሉ፣ በደልም ይረሳል፣ ሰሚ እንዳጣ ይቀጥላል ማለት ነው? መንግሥት እየወሰደው ካለው ዕርምጃ ጎን ለጎን ‹‹ችግር ፈቺ አካል›› ማቋቋም አለበት፡፡ ችግርና አቤቱታ እየመረመረ መፍትሔ የሚሰጥ ቡድን ወይም አካል ሊያቋቋም ይገባል፡፡ አለበለዚያ ‹‹ጉልቻ ቢቀያየር ወጥ አያጣፍጥም

በቅርቡ በምካሄደው የሲዳማ ዞን ምክር ቤት ጉባኤ ላይ የዞኑ ካቢኔ ሽግሽግ እንደምኖር ተሰማ

Image
ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ለወራንቻ ኢፎርሜሽን ኔትዎርክ እንደተናገሩት የሲዳማ ዞን ኣሰተዳደር ኣቶ ሚሊዮን ማቲዎስ በሃዋሳ ከተማ ከንቲባ በኣቶ ዮናስ ዮሰፍ ይተካሉ ተብሏል። በኣቶ ዮናስ ቦታ የሃዋሳ ከተማ ኣዲስ ከንቲባ የምሾምላት ሲሆን የወቅቱ የከተማዋ ትምህርት መምሪያ ሃላፊ ኣቶ ቃሬ የከተማዋ ከንቲባ ይሆናሉ ተብሎ ይጠበቃል። ዝርዝሩን እንደደረሰን እናቀርባለን 

ሐምሌ 6 ቀን 2005 ዓ.ም በደቡብ ክልል ምክር ቤት ሰባተኛ መደበኛ ጉባዔ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ሆነው የተመረጡት የቀድሞው የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር አቶ ደሴ ዳልኬ ሥራቸውን በይፋ ጀመሩ

Image
የሲዳማ ብሔር ተወላጅ የሆኑት አቶ ደሴ በቅርቡ የትምህርት ሚኒስትር ሆነው ከተሾሙት ከቀድሞው ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ላይ የክልሉን መንግሥት ኃላፊነት ተረክበዋል፡፡ አቶ ደሴ የበርካታ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ማዕከል የሆነውን የደቡብ ክልል ኃላፊነት ሲረከቡ እንደተናገሩት፣ ለሕዝቡ እኩል የልማት ተጠቃሚነትና ተሳትፎ ትኩረት ይሰጣሉ፡፡ የክልሉን ሕዝብ አንድነት ለማጠናከርና የተጀመሩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራት ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ለማድረግ እንደሚሠራ አስታውቀዋል፡፡ አዲሱ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደሴ ምንም እንኳን በክልሉ ሴክተር መሥርያ ቤቶች ከዚህ ቀደም ባይሠሩም፣ ከ1996 ዓ.ም እስከ 1998 ዓ.ም የይርጋ ዓለም ከተማ ከንቲባ፣ ከ1998 ዓ.ም እስከ 2000 ዓ.ም የሲዳማ ዞን ትምህርት መምርያ ኃላፊ፣ ከ2000 ዓ.ም እስከ 2003 ዓ.ም የሲዳማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሆነው ማገልገላቸው ታውቋል፡፡ ከ2003 ዓ.ም እስከ 2005 ዓ.ም ሰኔ ወር ድረስ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በመሆን የሠሩ ሲሆን፣ ከሐምሌ 6 ቀን ጀምሮ አዲሱን ኃላፊነታቸውን ተረክበዋል፡፡ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሳይንስ ፋኩልቲ በባይሎጂ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን፣ ከሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በለውጥ አመራር ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ያገኙት አቶ ደሴ፣ በአዲሱ ሹመት የተሻለ ለውጥ ያስመዘግባሉ ተብሎ እምነት ተጥሎባቸዋል፡፡ ከዚህ ቀደም በዞን ደረጃም ሆነ በፌደራል ደረጃ የነበራቸው የሥራ አፈጻጸም ለዚህ ኃላፊነት እንዳበቃቸው በክልሉ ምክር ቤት ጉባዔ ላይ ከተሳታፉ ግለሰቦች አስተያየት ለመረዳት ተችሏል፡፡ “አቶ ደሴ በተለይ በሲዳማ ዞን አስተዳዳሪነታቸው ወቅት ባሳዩት አመራር የተነሳ ክልሉን በፍትሐዊነት ያስተዳድራሉ ተብሎ ይጠበቃል፤” ሲሉ አንድ የክልሉ ባለሥልጣን ለሪፖር

በሲዳማ ዞን ከ186ሺህ በላይ ወጣቶች የሚሳተፉበት የክረምት የበጎ ፈቃድ ፕሮግራም በይፋ ተጀመረ፡፡

Image
photo http://www.flickr.com/photos/espsol/sets/72157632677473483/ አዋሳ ሐምሌ 11/2005 በደቡብ ክልል ሲዳማ ዞን ከ186ሺህ በላይ ወጣቶች የሚሳተፉበት የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ፕሮግራም ትናንት ተጀመረ ። የወጣቶችን የስራ ተነሳሽነትና ቁርጠኝነት እንዲጠናከር ሁሉም ባለድርሻ አካላት የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ የክልሉ ሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ጥሪ አቀረቡ፡፡ የፕሮግራሙ መጀመር ምክንያት በማድረግ በሲዳማ ዞን ቦርቻ ወረዳ ትናንት በተዘጋጀው መድረክ ላይ የዞኑ ሴቶች፣ ወጣቶችና ህፃናት ጉዳይ መምሪያ ኃለፊ ውይዜሮ ሻሎ ሮርሳ እንደገለጹት የዞኑ ወጣቶች ባለፉት አራት ዓመታት በበጎ ፈቃድ አገልግሎት በተደራጀ መንገድ በመሰማራት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ተግባሮችን ሲያከናዉኑ ቆይተዋል ። የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶችን ወጣቶቹ ጉልበታቸውን፣ እውቀታቸውን ለአካባቢው ልማት በማዋል መልካም ተግባሮችን ከማከናወናቸዉም ሌላ ከማህበረሰቡ የተለያዩ እሴቶችን የቀስሙበት እንደነበር አስታዉቀዋል ። በዘንድሮም ክረምት ከዞኑ የተለያዩ ባለድርሻ አካላትና ከወጣት አደረጃጀቶች ጋር በመተባበር እራሳቸውንና ህብረተሰቡን ጠቅመው የዞኑን ልማት በሚያፋጥኑ የልማት ተግባሮች ለመሰማራት እንቅስቃሴ መጀመራቸውን ወይዜሮ ሻሎ አብራርቷል፡፡ የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ /ደኢህዴን/ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አክልሉ አዱሎ በበኩላቸው የወጣቶች የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ስራ በከተማው ከተጀመረ ወዲህ ወጣቶች ለልማት ያላቸዉ ተነሳሽነትና ፍላጎት እየጨመረ መጥቷል ብለዋል፡፡ ወጣቶቹ በቆይታቸዉ የማጠናከሪያ ትምህርት በመስጠት ፣ የአካባቢ ጥበቃ፣ የጤና፣ የአካባቢ ፅዳትና ውበት፣ የትራፊክ ደህንነት፣ አረጋውያንና