Posts

ሰለ ሲዳማ ቡና

Image
Ethiopian Distinct Coffee  Sidamma The region of Sidama is in southern Ethiopia. It encompasses many individual origins, including, geographically, the area of Yirgacheffe. However, Yirgacheffe is classified as its own separate origin. In this section, we discuss Sidama as a designated coffee origin. The name Sidama is often spelled "Sidamo," and the two names are generally used interchangeably. Some of the confusion comes from earlier political designations that called Sidama the large federal region which stretches from the town of Shashemene in the north all the way to the Kenyan border; and which called Sidama a much smaller sub-region which contains the towns of Hawassa (Awassa), Yirga Alem, and Dila. All the coffee origins designated as Sidama are within the larger territory of Sidama, but not all are within the smaller state of Sidama. To avoid confusion, it's best to just consider all the central-southern Ethiopian coffees as Sidama, and then use the spe

ዩኒቨርስቲው 26 አዳዲስ ፕሮግራሞችን ለመክፈት እየሰራ ነው

Image
ሃዋሳ ሐምሌ 8/2005 በድህረና ቅድመ ምረቃ መርሃ ግብር ለ26 አዲስ ፕሮግራሞች ስርዓተ ትምህርት ቀርጾ ተግባራዊ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን የሃዋሳ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ገለጹ፡፡ በዩኒቨርስቲው የሀዋሳ ግብርና፣ ህከምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በተለያየ ሙያ በመጀመሪያ፣ በሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪ መርሀ ግብር ያሰለጠኗቸውን ከ900 የሚበልጡ ተማሪዎች ትናንት አስመርቀዋል፡፡ የዩኒቨርሰቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር ዮሴፍ ማሞ እንደገለጹት በተጠናቀቀው የትምሀርት ዘመን ለ18 አዳዲስ የድህረ ምረቃ ፕሮግራሞች ስርዓተ ትምህርት ቀረጻ ተጠናቆ አንዳንዶቹ ተማሪዎችን ተቀብለው ለማስተማር እንቅስቃሴ ጀምረዋል፡፡ ከፕሮግራሞቹ መካከል አግሪ ቢዝነስና ቫሊዩ ቼን ማኔጅመንት፣ በባዮቴክኖሎጂ ፣በአግሮ ኢኮሎጂና ሰስቴነብል አግሪካልቸር ይገኙበታል፡፡ በህክምና ትምህርት ቤት ደግሞ በውሰጥ ደዌ፣ በሀጻናት ህክምና፣ በቀዶ ጥገና ፣ በማህጸን ጽንስ ስፔሻሊቲ የስልጠና ፕሮግራም ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ ለመክፈት ዝግጅት መደረጉ ተመልክቷል፡፡ በቅድመ ምረቃ በቅርቡ ከተከፈተው የሲዳምኛ ቋንቋ በተጨማሪ ለ7 ፕሮግራሞች ስርዓተ ትምህርት ተቀርጾ በአንዳንዶቹ ተማሪዎችን ለመቀበል መዘጋጀታቸውን ዶክተር ዮሴፍ ጠቁመዋል፡፡ ይህም ዩኒቨርስቲው የቅበላ አቅሙን በመደበኛ ፕሮግራም ብቻ አሁን ያሉትን 17 ሺህ 080 ተማሪዎችን ቁጥር በ2007 ወደ 26 ሺህ ለማድረስ የተያዘው ፕሮግራም አንዱ አካል በመሆኑ ለዚህ ስኬት ከማስፋፊያ ግንባታዎች ባሸገር ቀልጣፋና ዘመናዊ አሰራር መዘርጋታቸውን ገልጠዋል፡፡ የመምህራንን አቅም በማጎልበት ረገድ በሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪ ከ400 በላይ መምህራን በሀገር ውስጥና በውጪ የከፍተኛ ትምህርታቸውን እየተማሩ ይገኛል ብለዋል፡፡ በመንግስት የተጀመረው የልማት እንቅስቃሴ በጥናትና ምር

የደቡብ ክልል ምክር ቤት 7ኛ መደበኛ ጉባኤ ከ15 ነጥብ 4ቢሊዮን ብር በላይ በጀት አፀደቀ

Image
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 07/2005 (ዋኢማ) - የደቡብ ክልል ምክር ቤት 7ኛ መደበኛ ጉባኤ ዘንድሮ በክልሉ ለሚከናወኑ የልማት ስራዎች ማስፈፀሚያ ከ15 ነጥብ 4ቢሊዮን ብር በላይ በጀት አፀደቀ ፡፡  ምክር ቤቱ ያፀደቀው በጀትም ከቀዳሚው ዓመት ከ1 ቢሊዮን 480 ሚሊዮን ብር በላይ ብልጫ እንዳለውም ተገልጿል፡፡  የክልሉ ገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ኃይለብርሃን ዜና በጀቱን ለክልሉ ምክር ቤት ጉባኤ አቅርበው ባጸደቁበት ጊዜ እንደተናገሩት በጀቱ ለመሰረተ ልማት ፣ ለድህነት ተኮር ፕሮግራሞች፣ ለምዕተ ዓመቱ የልማት ግቦችና ለመልካም አስተዳደር ስራዎች ማስፈጸሚያ ይውላል፡፡  ለክልሉ ከተመደበዉ በጀቱ ዉስጥ ከ8 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር የሚበልጠው ከፌዴራል መንግስት የቀመር ጥቅል ድርሻ፣ ከ3 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር በላይ ከክልሉ ከተለያዩ የገቢ ምንጮች የሚሰበሰብ ሲሆን ከ3 ቢሊዮን 015 ሚሊዮን ብር በላይ ደግሞ ለምዕተ ዓመቱ የልማት ግቦች ማስፈፀሚያ ከፌዴራል መንግስት ድጋፍ የሚገኝ ነዉ ።  እንዲሁም ከውጭ ሀገራት ይገኛል ተብሎ ከሚጠበቀው ገንዘብ 6 ሚሊዮን 882 ሺህ ብር በብድር ፣ 116 ሚሊዮን 842 ሺህ ብር ከእርዳታ መሆኑን ተናግረዋል፡፡  አጠቃላይ ከተመደበው በጀት ውስጥም ለታችኛው የአስተዳደር እርከን በዓላማ የተገደበ በጀት 76 በመቶ ሲሆን ቀሪው 24 በመቶ ለክልሉ ቢሮዎች የተያዘ መሆኑን አቶ ኃይለብርሃን ገልፀዋል፡፡ የበጀት ክፍፍል ሲደረግ ትምህርት፣ ጤና፣ ግብርና ልማት ስራዎች፣ መስኖና የንጹህ መጠጥ ውሃ ተቋማት ግንባታ፣ እንዲሁም የአስተዳደርና ሌሎች ሴክተሮች ወጪ በጥልቀት እንዲካተት መደረጉን አስታውቀዋል፡፡  የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ዴሴ ዳልኬ በሰጡት አስተያየትም የክልሉ በጀት የተደለደለዉ ህገ መንግስቱን መሰረት በማድረግ በፍ

በክልሉ የተጀመሩ የልማት፣ የመልካም አስተዳደርና የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ስራዎች ተጠናክሮ እንዲቀጥሉ ትኩረት ተሰጥቶ ይሰራል፡፡ የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር የተጀመሩ የልማት፣ የዴሞክራሲና የመልካም አስተዳደር ሰርዓት ግንባታ ለማጠናከር ትኩረት ይሰጣል

Image
አዋሳ ሐምሌ 07/2005 በደቡብ ክልል የተጀመሩ የልማት፣ የዴሞክራሲና የመልካም አስተዳደር ሰርዓት ግንባታ በማጠናከር ፍትሃዊ የልማት ተደራሽነትና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ አዲሱ የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ገለጹ፡፡ ርዕሰ መስተዳድሩ የክልሉ መንግስት የ2006 በበጀት ዓመት እቅድ ለምክር ቤቱ አባላት አቅርበዋል፡፡ ርእሰ መስተዳድሩ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት ባለፉት ሶስት የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ በየዘርፉ ታቅደው ያልተከናወኑ ተግባራትን በዝርዝር በመገምገምና መልካም ተሞክሮዎችን በመለየት በቀጣይ በሁሉም የልማት መስኮች ውጤታማ ስራዎችን ለማከናወንና የህብረተሰቡን ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ርብርብ ይደረጋል፡፡ በርብርቡ የሚካሄደው መንግስትና በድርጅት የቅርብ አመራር ሰጭነት፣ በባለሙያው ድጋፍና ክትትል እንዲሁም በህብረተሰቡ የተሟላ ተሳትፈፎና በቴክኖሎጂ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ነው ብለዋል፡፡ በመሆኑም በየስራ ዘርፉ የግንባር ቀደም ምርጥ ተሞክሮዎችን በማስፋት በገጠርም ሆነ በከተማ ድህነትን ለማስወገድ በሚያስችል መልኩ የጋራ ጥረት እንደሚደረግ አመልክተዋል፡፡ ባለፉት ዓመታት በክልሉ ታቅደው ላልተከናወኑ ተግባራት በርካታ ምክንያቶች ቢኖሩም የኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከትና ተግባር፣ የአስፈፃሚውና የፈፃሚው አቅም ውስንነት፣ቴክኖሎጂውን በተሟላ ሁኔታ ያለመጠቀም በዋናነት እንደሚጠቀሱ ተናግረዋል፡፡ እነዚህን ጉድለቶችን ለመቅረፍ የመንግስት፣ የድርጅትና የዝህብ ክንፎችን አቅም አቀናጅቶ በየደረጃው የልማት ሰራዊት በመገንባት የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድና የሚሌኒየም የልማት ግቦችን ለማሳካት የሚያስችሉ ስራዎች ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚከናወኑ ገልፀዋል፡፡ በግብርናው መስክ አርሶአደሩ የተሻሻሉ ቴክኖሎጅዎችን ተጠቅሞ ምርትና ምር

ሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ለሁለት መምህራን የፕሮፌሰርነት ማእርግ ሰጠ

Image
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ 4ሺህ723 ተማሪዎች አስመረቀ፡፡ ሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ለ14 ጊዜ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ያሰለጠናቸውን 4 ሺህ 723  ተማሪዎች በመጀመሪያና በሁለተኛ ዲግሪ አስመርቋል፡፡ከተመራቂዎች ውስጥ 556ቱ  በሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን የተከታተሉ ናቸው፡፡ ሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ለሁለት መምህራን ንጋቱ ረጋሳ እና ተስፋየ ሲመና   የፕሮፌሰርነት ማእርግ ሰጥቷል፡፡ በተመሳሳይ የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ 1ሺህ 352 ተማሪዎች በተለያዩ የትምህርት መስኮች በመጀመሪያና በሁለተኛ ዲግሪ  ሀምሌ 6/2005 ዓ/ም አስመርቋል፡፡ከተመራቂዎች በመጀመሪያ ዲግሪ 489 ወንዶችና 182 ሴቶች፣ በሁለተኛ ዲግሪ 515 ወንዶችና 166 ሴቶች ናቸው፡፡ http://www.ertagov.com/amharic/index.php/component/k2/item/1342-%E1%88%83%E1%8B%8B%E1%88%B3-%E1%8B%A9%E1%8A%92%E1%89%A8%E1%88%AD%E1%88%B2%E1%89%B2-%E1%88%88%E1%88%81%E1%88%88%E1%89%B5-%E1%88%98%E1%88%9D%E1%88%85%E1%88%AB%E1%8A%95-%E1%8B%A8%E1%8D%95%E1%88%AE%E1%8D%8C%E1%88%B0%E1%88%AD%E1%8A%90%E1%89%B5-%E1%88%9B%E1%8A%A5%E1%88%AD%E1%8C%8D-%E1%88%B0%E1%8C%A0