Posts

የደቡብ ክልል ምክር ቤት 7ኛ መደበኛ ጉባኤ ከ15 ነጥብ 4ቢሊዮን ብር በላይ በጀት አፀደቀ

Image
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 07/2005 (ዋኢማ) - የደቡብ ክልል ምክር ቤት 7ኛ መደበኛ ጉባኤ ዘንድሮ በክልሉ ለሚከናወኑ የልማት ስራዎች ማስፈፀሚያ ከ15 ነጥብ 4ቢሊዮን ብር በላይ በጀት አፀደቀ ፡፡  ምክር ቤቱ ያፀደቀው በጀትም ከቀዳሚው ዓመት ከ1 ቢሊዮን 480 ሚሊዮን ብር በላይ ብልጫ እንዳለውም ተገልጿል፡፡  የክልሉ ገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ኃይለብርሃን ዜና በጀቱን ለክልሉ ምክር ቤት ጉባኤ አቅርበው ባጸደቁበት ጊዜ እንደተናገሩት በጀቱ ለመሰረተ ልማት ፣ ለድህነት ተኮር ፕሮግራሞች፣ ለምዕተ ዓመቱ የልማት ግቦችና ለመልካም አስተዳደር ስራዎች ማስፈጸሚያ ይውላል፡፡  ለክልሉ ከተመደበዉ በጀቱ ዉስጥ ከ8 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር የሚበልጠው ከፌዴራል መንግስት የቀመር ጥቅል ድርሻ፣ ከ3 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር በላይ ከክልሉ ከተለያዩ የገቢ ምንጮች የሚሰበሰብ ሲሆን ከ3 ቢሊዮን 015 ሚሊዮን ብር በላይ ደግሞ ለምዕተ ዓመቱ የልማት ግቦች ማስፈፀሚያ ከፌዴራል መንግስት ድጋፍ የሚገኝ ነዉ ።  እንዲሁም ከውጭ ሀገራት ይገኛል ተብሎ ከሚጠበቀው ገንዘብ 6 ሚሊዮን 882 ሺህ ብር በብድር ፣ 116 ሚሊዮን 842 ሺህ ብር ከእርዳታ መሆኑን ተናግረዋል፡፡  አጠቃላይ ከተመደበው በጀት ውስጥም ለታችኛው የአስተዳደር እርከን በዓላማ የተገደበ በጀት 76 በመቶ ሲሆን ቀሪው 24 በመቶ ለክልሉ ቢሮዎች የተያዘ መሆኑን አቶ ኃይለብርሃን ገልፀዋል፡፡ የበጀት ክፍፍል ሲደረግ ትምህርት፣ ጤና፣ ግብርና ልማት ስራዎች፣ መስኖና የንጹህ መጠጥ ውሃ ተቋማት ግንባታ፣ እንዲሁም የአስተዳደርና ሌሎች ሴክተሮች ወጪ በጥልቀት እንዲካተት መደረጉን አስታውቀዋል፡፡  የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ዴሴ ዳልኬ በሰጡት አስተያየትም የክልሉ በጀት የተደለደለዉ ህገ መንግስቱን መሰረት በማድረግ በፍ

በክልሉ የተጀመሩ የልማት፣ የመልካም አስተዳደርና የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ስራዎች ተጠናክሮ እንዲቀጥሉ ትኩረት ተሰጥቶ ይሰራል፡፡ የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር የተጀመሩ የልማት፣ የዴሞክራሲና የመልካም አስተዳደር ሰርዓት ግንባታ ለማጠናከር ትኩረት ይሰጣል

Image
አዋሳ ሐምሌ 07/2005 በደቡብ ክልል የተጀመሩ የልማት፣ የዴሞክራሲና የመልካም አስተዳደር ሰርዓት ግንባታ በማጠናከር ፍትሃዊ የልማት ተደራሽነትና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ አዲሱ የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ገለጹ፡፡ ርዕሰ መስተዳድሩ የክልሉ መንግስት የ2006 በበጀት ዓመት እቅድ ለምክር ቤቱ አባላት አቅርበዋል፡፡ ርእሰ መስተዳድሩ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት ባለፉት ሶስት የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ በየዘርፉ ታቅደው ያልተከናወኑ ተግባራትን በዝርዝር በመገምገምና መልካም ተሞክሮዎችን በመለየት በቀጣይ በሁሉም የልማት መስኮች ውጤታማ ስራዎችን ለማከናወንና የህብረተሰቡን ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ርብርብ ይደረጋል፡፡ በርብርቡ የሚካሄደው መንግስትና በድርጅት የቅርብ አመራር ሰጭነት፣ በባለሙያው ድጋፍና ክትትል እንዲሁም በህብረተሰቡ የተሟላ ተሳትፈፎና በቴክኖሎጂ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ነው ብለዋል፡፡ በመሆኑም በየስራ ዘርፉ የግንባር ቀደም ምርጥ ተሞክሮዎችን በማስፋት በገጠርም ሆነ በከተማ ድህነትን ለማስወገድ በሚያስችል መልኩ የጋራ ጥረት እንደሚደረግ አመልክተዋል፡፡ ባለፉት ዓመታት በክልሉ ታቅደው ላልተከናወኑ ተግባራት በርካታ ምክንያቶች ቢኖሩም የኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከትና ተግባር፣ የአስፈፃሚውና የፈፃሚው አቅም ውስንነት፣ቴክኖሎጂውን በተሟላ ሁኔታ ያለመጠቀም በዋናነት እንደሚጠቀሱ ተናግረዋል፡፡ እነዚህን ጉድለቶችን ለመቅረፍ የመንግስት፣ የድርጅትና የዝህብ ክንፎችን አቅም አቀናጅቶ በየደረጃው የልማት ሰራዊት በመገንባት የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድና የሚሌኒየም የልማት ግቦችን ለማሳካት የሚያስችሉ ስራዎች ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚከናወኑ ገልፀዋል፡፡ በግብርናው መስክ አርሶአደሩ የተሻሻሉ ቴክኖሎጅዎችን ተጠቅሞ ምርትና ምር

ሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ለሁለት መምህራን የፕሮፌሰርነት ማእርግ ሰጠ

Image
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ 4ሺህ723 ተማሪዎች አስመረቀ፡፡ ሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ለ14 ጊዜ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ያሰለጠናቸውን 4 ሺህ 723  ተማሪዎች በመጀመሪያና በሁለተኛ ዲግሪ አስመርቋል፡፡ከተመራቂዎች ውስጥ 556ቱ  በሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን የተከታተሉ ናቸው፡፡ ሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ለሁለት መምህራን ንጋቱ ረጋሳ እና ተስፋየ ሲመና   የፕሮፌሰርነት ማእርግ ሰጥቷል፡፡ በተመሳሳይ የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ 1ሺህ 352 ተማሪዎች በተለያዩ የትምህርት መስኮች በመጀመሪያና በሁለተኛ ዲግሪ  ሀምሌ 6/2005 ዓ/ም አስመርቋል፡፡ከተመራቂዎች በመጀመሪያ ዲግሪ 489 ወንዶችና 182 ሴቶች፣ በሁለተኛ ዲግሪ 515 ወንዶችና 166 ሴቶች ናቸው፡፡ http://www.ertagov.com/amharic/index.php/component/k2/item/1342-%E1%88%83%E1%8B%8B%E1%88%B3-%E1%8B%A9%E1%8A%92%E1%89%A8%E1%88%AD%E1%88%B2%E1%89%B2-%E1%88%88%E1%88%81%E1%88%88%E1%89%B5-%E1%88%98%E1%88%9D%E1%88%85%E1%88%AB%E1%8A%95-%E1%8B%A8%E1%8D%95%E1%88%AE%E1%8D%8C%E1%88%B0%E1%88%AD%E1%8A%90%E1%89%B5-%E1%88%9B%E1%8A%A5%E1%88%AD%E1%8C%8D-%E1%88%B0%E1%8C%A0

የኢሜግሬሽንና ዜግነት ጉዳዮች ዋና መምሪያ አዋሳ በሚገኘው ቅርንጫፍ መስሪያ ቤቱ ከህገ ወጥ ደላሎች ጋር በመመሳጠር ተገልጋዮችን አንገላተዋል ያላቸውን 11 ሰራተኞች በህግ ቁጥጥር ስር ዋሉ

Image
አዲስ አበባ ፣ ሃምሌ 6 ፣ 2005 (ኤፍ.ቢ. ሲ) የኢሜግሬሽንና ዜግነት ጉዳዮች ዋና መምሪያ በስራዬ ላይ እንቅፋት ሆነዋል ባላቸው የተቋሙ ሰራተኞችና ህገወጥ ደላሎች ላይ ከሚመለከታቸው አካለት ጋር በመሆን በህግ ቁጥጥር ስር እንዲውሉ አደረገ፡፡ በህግ ቁጥጥር ስር እንዲውሉ የተደረጉት ተቋሙ አዋሳ በሚገኘው ቅርንጫፍ መስሪያ ቤቱ ከህገ ወጥ ደላሎች ጋር በመመሳጠር ተገልጋዮችን አንገላተዋል ያላቸውን አስራ አንድ ሰራተኞቹ ፡፡ የኢሚግሬሽን ዜግነት ጉዳዮች ዋና መምሪያ የሚሰጠው አገልግሎት ፈጣንና ቀልጣፋ አይደለም በዚህም ለእንግልት እየተዳረግን ነው የሚሉና መሰል አቤቱታዎች በተገልጋዩ ዘንድ የሚነሱ ቅሬታዎች ናቸው፡፡ ተቋሙ የችግሩ መንስኤዎች የህግ ወጥ የደላሎች መበራከትና አሁን ካለው የኪራይ ሰብሳቢነት ችግር ተያይዞ የመጣ መሆኑን በመግለፅ  ፤ ለዚህም ያካሄድኳቸው ግምገማዎችና ክትትሎች ማሳያ ናቸው ብሏል፡ የዋና መምሪው ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ሀይለ ጊዮርጊስ እንደሚሉት ፥ አዲስ አበባ በሚገኘው ዋናው ተቋም የሚስተዋለው የአገልግሎት መጨናነቅ ህገወጥ ደላሎች ለፓስፖርት ፈላጊዎች በሚሰጡት የተሳሳተ መረጃ ምክንያት የተከሰተ ነው ብለዋል፡፡ “በክልሎች ተመሳሳይ አገልግሎት የሚሰጡ  ስድስት መስሪያ ቤቶች ቢኖሩም ህገወጥ ደላሎቹ ተጨማሪ ብር ለማግኘት ትክክለኛው ፓስፖርት ያለው አዲስ አበባ ነው በማለትና ተገልጋዩን ቪዛ እናመጣላችዋለን እያሉ  ፓስፖርታቸውን እየቀሙ ይወስዳሉ " ብለዋል፡፡ በህገወጥ ደላሎችና በአንዳንድ የተቋሙ ሰራተኛች መካከል ተፈጥሮ የነበረው የጥቅም ትስስርም ሌላኛው የችግሩ መንስኤ መሆኑን ነው አቶ ጌታቸው ያስረዱት፡፡ ህገወጥ ደላሎቹ ከሰራተኛቹ ጋር በመመሳጠር ባለጉዳዮች ገንዘብ ከከፈሉ ፓስፖርት የሚወሰድበ

በደቡብ ክልል በተጠነቀቀው በጀት ዓመት በሁሉም የልማት መስኮች የተሻለ ውጤት ተመዝግቧል

Image
አዋሳ ሐምሌ 06/2005 በደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሁሉም የልማት መስኮች መላውን የክልሉን ነዋሪ ተጠቃሚ ያደረጉ አበረታታች ስራዎች መከናወናቸውን የትምህርት ሚኒስትር በመሆን የተሾሙት የቀድሞው ርዕሰ መስተዳድር አስታወቁ። ርዕሰ መስተዳድሩ አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ለክልሉ ምክር ቤት 4ኛ ዙር 7ኛ መደበኛ ጉባኤ ባቀረቡት ሪፖርት ላይ እንዳሉት በተጠናቀቀው በጀት አመት በግብርና በትምህርት በጤና በመንገድ በንግድ ኢንዱስትሪ፣በከተማ ልማትና ሌሎች መስኮች የተከናወኑ ስራዎች ውጤታማና መላውን ነዋሪ ተጠቃሚ ያደረጉ ናቸው። በግብርናው መስክ አርሶ አደሩ መስኖ ተጠቅሞ በበጋ ወራት በገበያ ተፈላጊ የሆኑና የተሻለ ዋጋ የሚያስገኙ ሰብሎችን እንዲያመርት እንዲሁም የራሱንና የቤተሰቡን ጉልበት በአግባቡ ልማት ላይ በማዋል ገቢውን እንዲያስድግ በተሰራ ስራ አበረታች ውጤት ከመመዝገቡ በተጨማሪ በአከባቢ አየር ለውጥ ምክንያት ወቅቱ፣ ስርጭቱና መጠኑ እየተዛባ ካለው የዝናብ ተፅዕኖ የሚያላቅቁ ስራዎች መከናወናቸውን ገልፀዋል፡፡ በአነስተኛ ወጪና ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም በሁለት ዙር የመስኖ ልማት 180ሺህ 905 ሄክታር መሬት በስራስር፣ ቦሎቄ፣ ቦቆሎ፣ እና የጓሮ አትክልቶች በመሸፈን 26 ሚሊዮን 606ሺህ 342 ኩንታል ምርት ማምረት መቻሉን አስረድተዋል፡፡ ከክልሉ የሚመረተውን ቡና ጥራትና ደረጃ በማስጠበቅ በብዛት አምርቶ ለውጪ ገበያ በማቅረብ ሀገሪቱ የምታገኘውን የውጪ ምንዛሪ ለማሳደግና አምራች አርሶ አደሩ ተጠቃሚ እንዲሆን 42 ሺህ 189 ቶን የታጠበና 40ሺህ 952 ቶን ያልታጠበ ቡና በግልና በማህበረት ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረብ ተችሏል ብለዋል። በክልሉ በከተማና ገጠር 704 የውሃ ተቋማትን በመገንባት፣የማስፋፊያና የጥገና ስራ በማከናወን 1