Posts

በደቡብ ክልል በተጠነቀቀው በጀት ዓመት በሁሉም የልማት መስኮች የተሻለ ውጤት ተመዝግቧል

Image
አዋሳ ሐምሌ 06/2005 በደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሁሉም የልማት መስኮች መላውን የክልሉን ነዋሪ ተጠቃሚ ያደረጉ አበረታታች ስራዎች መከናወናቸውን የትምህርት ሚኒስትር በመሆን የተሾሙት የቀድሞው ርዕሰ መስተዳድር አስታወቁ። ርዕሰ መስተዳድሩ አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ለክልሉ ምክር ቤት 4ኛ ዙር 7ኛ መደበኛ ጉባኤ ባቀረቡት ሪፖርት ላይ እንዳሉት በተጠናቀቀው በጀት አመት በግብርና በትምህርት በጤና በመንገድ በንግድ ኢንዱስትሪ፣በከተማ ልማትና ሌሎች መስኮች የተከናወኑ ስራዎች ውጤታማና መላውን ነዋሪ ተጠቃሚ ያደረጉ ናቸው። በግብርናው መስክ አርሶ አደሩ መስኖ ተጠቅሞ በበጋ ወራት በገበያ ተፈላጊ የሆኑና የተሻለ ዋጋ የሚያስገኙ ሰብሎችን እንዲያመርት እንዲሁም የራሱንና የቤተሰቡን ጉልበት በአግባቡ ልማት ላይ በማዋል ገቢውን እንዲያስድግ በተሰራ ስራ አበረታች ውጤት ከመመዝገቡ በተጨማሪ በአከባቢ አየር ለውጥ ምክንያት ወቅቱ፣ ስርጭቱና መጠኑ እየተዛባ ካለው የዝናብ ተፅዕኖ የሚያላቅቁ ስራዎች መከናወናቸውን ገልፀዋል፡፡ በአነስተኛ ወጪና ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም በሁለት ዙር የመስኖ ልማት 180ሺህ 905 ሄክታር መሬት በስራስር፣ ቦሎቄ፣ ቦቆሎ፣ እና የጓሮ አትክልቶች በመሸፈን 26 ሚሊዮን 606ሺህ 342 ኩንታል ምርት ማምረት መቻሉን አስረድተዋል፡፡ ከክልሉ የሚመረተውን ቡና ጥራትና ደረጃ በማስጠበቅ በብዛት አምርቶ ለውጪ ገበያ በማቅረብ ሀገሪቱ የምታገኘውን የውጪ ምንዛሪ ለማሳደግና አምራች አርሶ አደሩ ተጠቃሚ እንዲሆን 42 ሺህ 189 ቶን የታጠበና 40ሺህ 952 ቶን ያልታጠበ ቡና በግልና በማህበረት ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረብ ተችሏል ብለዋል። በክልሉ በከተማና ገጠር 704 የውሃ ተቋማትን በመገንባት፣የማስፋፊያና የጥገና ስራ በማከናወን 1

ሀዋሳ ዪኒቨርስቲ ከ4 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎችን በቅድመና ድህረ ምረቃ ኘሮግራም ዛሬ አስመረቀ

Image
አዋሳ ሐምሌ 06/2005 የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በ2006 የትምህርት ዘመን ለሚያካሄዳቸው ፕሮግራሞችና ፕሮጀክቶች ማስፈጸሚያ 1ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ከመንግስት የተመደበለት መሆኑን የዩኒቨርስቲው ፕሬዝደንት ገለጹ፡፡ ዩኒቨርስቲው በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸው ከ4 ሺህ 700 በላይ ተማሪዎች በቅድመና ድህረ ምረቃ ፕሮግራሞ ዛሬ አስመርቋል፡፡ በምረቃው ስነ ስርዓት ላይ የዩኒቨርስቲው ፕሬዝደንት ዶክተር ዮሴፍ ማሞ እንደገለጹት ዩኒቨርስቲው በ2006 የትምህርት ዘመን በአራት ፕሮግራሞች ሰባት ውጤቶች ላይ በማተኮር 57 ዋና ዋና ተግባራትን ለማከናወንና 40 ፕሮጀክቶችን ለማስፈጸም 1ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ተመድቦለታል፡፡ ዩኒቨርስቲው የመማር ማስተማር፣ ምርምር፣ የህብረተስብ አገልግሎትና የቴክኖሎጂ ሽግግር ከማካሄድ አኳያ በ2005 የበጀት አመት ከመንግስት በተመደበለት ከ975 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ መጠነ ሰፊ ስራዎችን ማከናወኑንም አስረድተዋል፡፡ እነዚህ ሰራዎች ዩኒቨርስቲው የቅበላ አቅሙን ለማሰደግና የትምህርት ጥራትን ለመጠበቅ ከፍተኛ አስተዋጾኦ እንዳለው አመልክተው መንግስት በሀገር አቀፍ ደረጃ የተነደፈው 70 በመቶ የቴክኖሎጂና ተፈጥሮ ሳይንስ መስክና 30 በመቶ ማህበራዊ ሳይንስ ሀገራዊ የተማሪ ቁጥር ምጣኔ ሙሉ በሙሉ መተግበሩን አስታውቀዋል፡፡ ከ2003 ዓ.ም ጀምሮ በሁሉም የትምህረት ዘርፎች ተግባራዊ ያደረጉት አዱሱን ተማሪ ተኮር የሞጁለር የትምህርት አሰጣጥ ዘዴና ተከታታይ የተማሪዎችን ውጤት ምዘና ስርዓት አጠናክሮ በመቀጠል ከዚህ ቀደም ከትምህርታቸው ይሰናበቱ የነበሩ ተማሪዎች ቁጥር መቀነስ መቻሉን ተናግረዋል፡፡ በዘመኑ ለመማር ማስተማር የሚያግዙ የተለያዩ የትምህርት ግብኣቶችን የማሟላትና የማደራጀት ስራዎች መከናወናቸውን ዶክተር ዮሴፍ ጠቁ

‹‹ኔትዎርክ የለም››

Image
ዘመናዊ የባንክ አገልግሎት ተግባራዊ ለማድረግ የአገሪቱ ባንኮች በግልና በኅብረት ሆነው እንቅስቃሴዎች እያደረጉ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን ጨምሮ ስድስት የግል ባንኮች የኤቲኤም አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል፡፡ ከዘመናዊ የባንክ አገልግሎቶች አንዱ በመሆን የሚጠቀሰው የኤቲኤም እዚህ እንደ አዲስ እንየው እንጂ በዓለም ላይ አገልግሎት መስጠት ከጀመረ ከ40 ዓመታት በላይ ሆኖታል፡፡ ሌሎች ዘመናዊ የምንላቸውን የባንክ የአገልግሎት ዓይነቶችም ገና በመግባት ላይ ናቸው ወይም ለማስገባት ዕቅድ ተይዟል፡፡ ለአገራችን አዳዲስ የምንላቸውን ዘመናዊ የባንክ አገልግሎቶች ለማግኘት ባንኮች ከወዲሁ ቅድመ ዝግጅት እያደረጉ ነው፡፡ ቅርንጫፎቻቸውን በኔትዎርክ አስተሳስረዋል፡፡ በሞባይል ገንዘብ ለማዘዋወር የሚያስችለውን ቴክኖሎጂም ሊጀምሩ ነው፡፡ ከኤቲኤም ጀምሮ ወደፊት ተግባራዊ ይሆናሉ ተብለው የሚጠበቁ ዘመናዊ የባንክ አገልግሎቶችን ወደተግባር ለመለወጥ ደግሞ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የቴሌን ድጋፍ ይፈልጋሉ፡፡ አገልግሎቶቹ ከኔትዎርክ ጋር የሚያያዙ በመሆኑ የኔትዎርክ ችግር ካለ አገልግሎቱን መስጠት አይችልም፡፡ ሰሞኑን እንደታዘብነው ግን የኔትዎርክ ችግር በትንሽ ደረጃ የተጀመረውን ዘመናዊ የባንክ ሥራ እየፈተነው ነው፡፡ በተደጋጋሚ እየተከሰተ ነው በሚባለው የኔትዎርክ ችግር የባንክ ደንበኞች ተገቢውን አገልግሎት እያገኘን አይደለም በማለት እያማረሩ ናቸው፡፡ ገንዘብ ለማስገባትና ለማስወጣት ብዙ እንግልት እየደረሰብን ነው የሚሉት የባንክ ደንበኞች በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ችግሩ በተደጋጋሚ መከሰቱን ይጠቁማሉ፡፡  ሰሞኑን በኔትዎርክ ችግር ምክንያት እየተጉላላን ነው ካሉ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ደንበኞች መካከል የአንድ ድርጅት ሠራተኛ ጨርቆስ አካባቢ በሚገኘው የኢት

የሰብዓዊ መብት ድርጊት መርሐ ግብርን ለመከታተል ስድስት ባለሥልጣናት ኃላፊነት ወሰዱ

የዜጐችን የሰብዓዊ መብት ለማስከበር መንግሥት ነድፎታል የተባለውን የሦስት ዓመታት የድርጊት መርሐ ግብር በበላይነት የሚከታተል ብሔራዊ ኮሚቴ ተመሠረተ፡፡ ስድስት ከፍተኛ ባለሥልጣናት የኮሚቴው አባል በመሆን ኃላፊነት ወስደዋል፡፡ የድርጊት መርሐ ግብሩን በበላይነት ለመከታተል የተቋቋመው ብሔራዊ ኮሚቴ ሰብሳቢ የፍትሕ ሚኒስትሩ አቶ ጌታቸው አምባዬ በመሆን የተመረጡ ሲሆን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ነጋ ፀጋዬ በምክትል ሰብሳቢነት ተመርጠዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ኮሚሽነር የሆኑት አምባሳደር ጥሩነህ ዜና የብሔራዊ ኮሚቴው ጸሐፊ ሆነዋል፡፡ የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር አብርሃም ተከስተ፣ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ሽመልስ ከማል፣ የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሙሉጌታ ውለታው የኮሚቴው አባላት ሆነው የመከታተል ኃላፊነቱን ወስደዋል፡፡  ብሔራዊ የሰብዓዊ መብት የድርጊት መርሐ ግብር በሚል ስያሜ መንግሥት ያዘጋጀው ሰነድ በሦስት ዓመታት ውስጥ የዜጐችን ሕገ መንግሥታዊ መብቶች በተሻለ ሁኔታ በማክበርና በማስከበር፣ በዚህ ረገድ የሚታይበትን ከፍተኛ ጉድለት ለመቅረፍ ያለመ መሆኑ ተገልጿል፡፡  በቅርቡ በፓርላማ የፀደቀው የድርጊት መርሐ ግብር ካካተታቸው ጉዳዮች መካከል የሕግ አስከባሪዎች ያላግባብ በተጠርጣሪዎች ላይ የሚፈጽሙት ድብደባ አንዱ ሲሆን፣ እንደዚህ ዓይነት ተግባር በሚፈጽሙ የፖሊስ አባላት ላይ ጥብቅ የሆነ ዕርምጃ ለመውሰድ በዕቅዱ ተካቷል፡፡  ከዚህ በተጨማሪ የተጠረጠሩ ግለሰቦችን በእስር በመያዝ ረዥም ጊዜ የሚፈጅ ምርመራ ማድረግ በሕግ አስከባሪው ዘንድ የሚታይ ጉድለት መሆኑን በመግለጽ፣ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር ውለው ምርመራ ለማድረግ የጊዜ ገ

የቡና ቦርድ በድጋሚ ሊቋቋም ነው

Image
መንግሥት ከዓመታት ቆይታ በኋላ በድጋሚ የቡና ቦርድ ለማቋቋም ወሰነ፡፡ በአሁኑ ወቅት የቡና ዘርፍ ራሱን የቻለ ባለቤት ስለሌለው ችግር ውስጥ ገብቷል በሚል ምክንያት በድጋሚ የቡና ቦርድ እንዲቋቋም መወሰኑን ምንጮች ገልጸዋል፡፡ እስካሁን መንግሥት ስትራቴጂ የሚላቸውን ዘርፎች የሚከታተል፣ ችግራቸውን የሚፈታና የሚቆጣጠር ኤጀንሲ ሲያቋቁም ቆይቷል፡፡ በእስካሁኑ ሒደትም የአበባና አትክልት፣ የጨርቃ ጨርቅና ጋርመንት፣ የቆዳና የቆዳ ውጤቶችን ዘርፍ የሚከታተሉ ተቋማት መመሥረታቸው ይታወቃል፡፡  በዚሁ ቅርጽ አገሪቱ የምትታወቅበትና ከፍተኛውን የውጭ ምንዛሪ የሚያስገባው ቡና ራሱን የቻለ ቦርድ እንዲቋቋምለት ሐሳቡ ቀርቦ በመንግሥት ተቀባይነት አግኝቷል፡፡  በአሁኑ ወቅት ቡና ከምርት ጀምሮ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ እስኪደርስ ድረስ በግብርና ሚኒስቴር ባለቤትነት ይካሄዳል፡፡ ከምርት ገበያ እስከ ኤክስፖርት ድረስ ያለው ሒደት በንግድ ሚኒስቴር ባለቤትነት ይከናወናል፡፡ ቡና በንግድ ሚኒስቴር ውስጥ እንደማንኛውም የግብርና ምርት የሚታይ በመሆኑና ትኩረት ያልተሰጠው በመሆኑ፣ በግብይት ሒደት ከፍተኛ ችግሮች መፈጠራቸውን መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ እነዚህን ችግሮች ለመፍታት የሚደረገው እንቅስቃሴ ዘገምተኛ መሆኑን በዘርፉ ውስጥ የተሰማሩ ሰዎች ይናገራሉ፡፡  እነዚህ አስተያየት ሰጪዎች እንደሚሉት፣ የቦርዱ መቋቋም ቢዘገይም አስፈላጊነቱ አያጠያይቅም፡፡ በንጉሡ ዘመን የቡና ቦርድ የሚባል ተቋም ነበር፡፡ በወታደራዊው መንግሥት የሥልጣን ዘመንም የቡናና ሻይ ሚኒስቴር በመባል ነበር፡፡ ኢሕአዴግ አገሪቱን ሲቆጣጠር የቡና ዘርፍ ትኩረት እያጣ መምጣቱን የሚናገሩት የቡና ነጋዴዎች፣ ዘርፉ ከጊዜ ወደ ጊዜ ማደግ ሲገባው እየቀጨጨ መምጣቱን ይናገራሉ፡፡  በአዲሱ ዓመት የቡና