በደቡብ ክልል የፕሬዚዳንትነትን ቦታ ለሲዳማ ብሄር ተወላጆች ክፍት በማድረግ ኢህኣዴግ የሲዳማን ክልል ጥያቄ በማፈን ላይ ነው
ሲዳማ ባለፉት 20 ኣመታት ህዝባዊ የፖለቲካ ጥያቄዎችን በተመለከተ ፖለቲካዊ ኣንድነትን ከመቼውም ጊዜ በላይ ያሳየው የደቡብ ክልል ፕሬዚዳንትነትን ቦታ በሌላው የደቡብ ብሄር በተነጠቀበት ወቅት ብቻ ነው ማለት ይቻላል። ይሄውም የቀደሞውን የክልሉ ፕሬዚዳንት ኣቶ ኣባተ ኪሾን በሙሲና ተከሰው ከስልጣን ላይ መነሳታቸውን ተከትሎ ወደ ክልሉ ፕሬዚዳንትነት የመጡት የኣሁን የኣገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ የክልሉ ፕሬዚዳንት በነበሩበት ጊዜ ብቻ ነው፤ ሲዳማ ህዝቡም ሆነ ህዝቡ የመረጣቸው የፖለቲካ መሪዎች በኣንድ ኣፍ የተናገሩት እና ለሁሉም ጥቅም መከበር ኣብረው የሰሩት። ከጊዜ ውጭ በተለይ የሲዳማ ተወላጆች የክልሉን ፕሬዚዳንትነትን በያዟቸው ወቅቶች በሙሉ ማለት ይቻላል በሲዳማ ህዝብ ጥቅሞች ላይ ኣንድ ኣይነት ኣቋም ተይዞ ኣልታየም። በተለይ የሲዳማን የክልል ጥያቄን በተመለከት የህዝቡ ፍላጎት እና የፖለቲካ ኣመራሮቹ ፍላጎት ለየቅል ሆነው ታይተዋል። ለኣብነት ያህል ኣቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ የክልሉ ፕሬዚዳንት በነበሩበት ጊዜ በወቅቱ የሲዳማ ዞን ዋና ኣስተዳዳሪ በነበሩት በኣቶ ገርመው ጋርጄ የምመራው የሲዳማ የፖለቲካ ኣመራር ለሲዳማ የክልል መንግስት ያስፈልገዋል በማለት ከከተማ እስከ ገጠር ድረስ ካድሬዎቹን በማሰማራት ህዝብ የማሳመን ስራ ስርቷል። የክልል ጥያቄ በህዝብ ውስጥ ስር እንዲሰድ እና በኣንድነት ሆ ! ብሎ እንድደግፋቸው ኣድርገዋል። በጊዜ የሲዳማ ህዝብም በኣመራሮች ለህዝባቸው መቆርቆር ከመደሰቱ እና ከመኩራቱ በላይ ለጥያቄው መሳካት በነብሱን ገብረውለታል። ይህ ጊዜ የሲዳማ ኣባቶች እና እናቶች በልጆቻቸው የኮሩበት፤ ምራቃቸውን ተፍተው የመረቋቸው ጊዜ እንደነበር የምታወስ ነው። በእርግጥም በወቅቱ በያዙት እና በፈጸሙት ጀግንነት መ