Posts

በደቡብ ክልል የፕሬዚዳንትነትን ቦታ ለሲዳማ ብሄር ተወላጆች ክፍት በማድረግ ኢህኣዴግ የሲዳማን ክልል ጥያቄ በማፈን ላይ ነው

Image
ሲዳማ ባለፉት 20 ኣመታት ህዝባዊ የፖለቲካ ጥያቄዎችን በተመለከተ ፖለቲካዊ ኣንድነትን ከመቼውም ጊዜ በላይ ያሳየው የደቡብ ክልል ፕሬዚዳንትነትን ቦታ በሌላው የደቡብ ብሄር በተነጠቀበት ወቅት ብቻ ነው ማለት ይቻላል። ይሄውም የቀደሞውን የክልሉ ፕሬዚዳንት ኣቶ ኣባተ ኪሾን በሙሲና ተከሰው ከስልጣን ላይ መነሳታቸውን ተከትሎ ወደ ክልሉ ፕሬዚዳንትነት የመጡት የኣሁን የኣገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ የክልሉ ፕሬዚዳንት በነበሩበት ጊዜ ብቻ ነው፤ ሲዳማ ህዝቡም ሆነ ህዝቡ የመረጣቸው የፖለቲካ መሪዎች በኣንድ ኣፍ የተናገሩት እና ለሁሉም ጥቅም መከበር ኣብረው የሰሩት። ከጊዜ ውጭ በተለይ የሲዳማ ተወላጆች የክልሉን ፕሬዚዳንትነትን በያዟቸው ወቅቶች በሙሉ ማለት ይቻላል በሲዳማ ህዝብ ጥቅሞች ላይ ኣንድ ኣይነት ኣቋም ተይዞ ኣልታየም። በተለይ የሲዳማን የክልል ጥያቄን በተመለከት የህዝቡ ፍላጎት እና የፖለቲካ ኣመራሮቹ ፍላጎት ለየቅል ሆነው ታይተዋል። ለኣብነት ያህል ኣቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ የክልሉ ፕሬዚዳንት በነበሩበት ጊዜ በወቅቱ የሲዳማ ዞን ዋና ኣስተዳዳሪ በነበሩት በኣቶ ገርመው ጋርጄ የምመራው የሲዳማ የፖለቲካ ኣመራር ለሲዳማ የክልል መንግስት ያስፈልገዋል በማለት ከከተማ እስከ ገጠር ድረስ ካድሬዎቹን በማሰማራት ህዝብ የማሳመን ስራ ስርቷል። የክልል ጥያቄ በህዝብ ውስጥ ስር እንዲሰድ እና በኣንድነት ሆ ! ብሎ እንድደግፋቸው ኣድርገዋል። በጊዜ የሲዳማ ህዝብም በኣመራሮች ለህዝባቸው መቆርቆር ከመደሰቱ እና ከመኩራቱ በላይ ለጥያቄው መሳካት በነብሱን ገብረውለታል። ይህ ጊዜ የሲዳማ ኣባቶች እና እናቶች በልጆቻቸው የኮሩበት፤ ምራቃቸውን ተፍተው የመረቋቸው ጊዜ እንደነበር የምታወስ ነው። በእርግጥም በወቅቱ በያዙት እና በፈጸሙት ጀግንነት መ

የደቡብ ክልል ምክር ቤት ጉባኤ ዛሬ በሃዋሳ ከተማ ተጀመረ የክልሉን ርዕስ መስተዳደር ሹመት ጽድቋል

Image
ከሃዋሳ በደረሰን ዜና መሰረት የቀደሞውን የደቡብ ክልል ፕሬዚዳንት ኣቶ ሽፈራው ሽጉጤ ተክተው ኣቶ    ደሴ ዳልኬ  ተሹመዋል። የኣቶ ደሴ ዳልኬ መሾም ሲዳማ በደቡብ ክልል መንግስት ውስጥ ያለውን የፖለቲካ ሚና ትልቅነት የሚያሳይ እና በክልሉ ያለው የፖለቲካ መሪነት ቀጣይነት ያረጋገጠ ነው ተብለዋል። ሲዳማን ጨምሮ በተለያዩ ክልሎች ተዋቅሮ የነበሩት ብሄርና ብሄረሰቦች እና ህዝቦች ወደውም ሆነ ሳይወዱ በኣንድ ክልል ከተጠቃለሉ ጊዜ ጀምሮ ሲዳማ የክልሉን ፖለቲካ በበላይነት መምራቱን ቀጥሎበታል። እስከ ኣሁን የደቡብ ክልልን ከመሩት እና በመምራት ካሉት ኣራት ርዕስ መስተዳደሮች መካከል ሶስቱ ከሲዳማ ናቸው። ኣቶ ደሴ ዳልኬ ባለፉት ኣስራ ሁለት ኣመታት በሲዳማ ዞን ውስጥ በተለያዩ የስራ ሃላፊነቶች ላይ የሰሩ እና ላለፉት ሶስት ዓመታት የሣይንስ እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ሆነው የቆዩ ናቸው። የኣቶ ደሴ ዳልኬ ወደ ደቡብ ክልል ተመልሰው መምጣት ለሲዳማ ያለው እድምታ ምን እንደሆነ ለጊዜው ግልጽ ባይሆንም በሲዳማ ዘንድ የተደበላለው ስሜት ፈጥሯል። ኣቶ ደሴ ዳልኬ በሲዳማ ህዝብ ዘንድ በየጊዜው እየተነሳ የቆየውን የሲዳማ ክልል ጥያቄን በተመለከተ የሚኖራቸውን ኣቋም ከዚህ በፊት ከነበሩት የክልሉ መሪዎች የተለየ እንደማይሆን የተገመተ ሲሆን ለክልል ጥያቄው ኣዎንታዊ ምላሽ እንዲሰጥ የሚያደርጉ ከሆነ የሲዳማ ህዝብ ድጋፊ እና ፍቅር ሊያገኑ ይችላሉ ተብሏል።

አቶ ደሴ ዳልኬ የደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ርእሰ መስተዳድር ሆኑ

ሃዋሳ ሐምሌ 06/2005 የክልሉ ምክር ቤት 4ኛ ዙር 7ኛ መደበኛ ጉባኤ አቶ ደሴ ዳልኬን የደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል መንግስት ርእሰ መስተዳድር አድርጎ መረጠ፡፡ ርእሰ መስተዳድሩ ከቀድሞው ርእስ መስተዳድር ከአቶ ሽፈራው ሽጉጤ የክልሉን መንግስት ቁልፍ በመረከብ በይፋ ስራ ጀምረዋል፡፡ ርእሰ መስተዳድሩ አቶ ደሴ ዳልኬ እንዳስገነዘቡት ክልሉ የበርካታ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ማእከል በመሆኑ ለእኩል የልማት ተጠቃሚነትና ተሳትፎ ትኩረት ሰጥተው ይሰራሉ፡፡ መላ የክልሉን ሕዝብ በአንድነት ለማጠናከር የተጀመሩ የልማትና መልካም አስተዳደር ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል፡፡ ርእሰ መስተዳድሩ የሲዳማ ብሔር ተወላጅ ሲሆኑ የትምህርት ዝግጅታቸው በስነ ህይወት ሳይንስ የመጀመሪያና በለውጥ አመራር ሁለተኛ ዲግሪ ያላቸውና ከወረዳ ጀምሮ እስከ ፌዴራል በተለያየ የሃላፊነት እርከን ያገለገሉ መሆናቸው ተገልጿል፡፡ የቀድሞው ርእስ መስተዳድር አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ባለፉት ስምንት አመታት በክልሉ ልማትና መልካም አስተዳደር እንደዲሰፍ ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋጽኦ የክልሉ ምክር ቤት አባላትና ድርጅቱ እውቅና ሰጥቷቸዋል፡፡ http://www.ena.gov.et/Story.aspx?ID=9613&K=1

Hawassa University graduation ceremony 2005

Image
Hawassa University to hold a graduation ceremony for 2005 E.C. graduates on July 13 & 14,2013 consecutively @ Main Campus.  " Congratulation to all graduating students"

መልካም ሳምንት ለመላው ሲዳማ _ኣዱኛ ዱሞ ሃኖ

Image
ኣዱኝ ዱሞ ሃኖ