Posts

በሃዋሳ ከተማ ከ11 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የትራፊክ ኮምፕሌክስ ህንፃ እየተገነባ ነው

ሃዋሳ ሐምሌ 2/2005 በደቡብ ክልል ሃዋሳ ከተማ ከ11 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የአሽክርካሪ ብቃት ምዘና የሚደረግበት ዘመናዊ የትራፊክ ኮምፕሌክስ ህንፃ ግንባታ ከ85 በመቶ በላይ መጠናቀቁን የክልሉ ትራንስፖርት ቢሮ ገለጸ፡፡ በአርባምንጭ፣ በሆሳዕናና በሚዛን አማን ከተሞች ከ30 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ ተጨማሪ የትራፊክ ኮምፕሌክስ ግንባታ ለማካሄድ አሰፈላጊው ዝግጅት መጠናቀቁም ተገልጿል፡፡ በቢሮ የአሽከርካሪና ተሽከርካሪ ብቃት ማረጋገጫ ዋና የስራ ሂደት አስተባበሪ አቶ ውቤ ለሳ ሰሞኑን ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት የክልሉ መንግስት በመደበው ወጪ የተጀመረው የተቋሙ ግንባታ የትራፊክ አደጋን ለመቀነስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል፡፡ ግንባታው ከሶስት ወር በኋላ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ አገልግሎት ይሰጣል ብለዋል፡፡ በክልሉ በየጊዜው የሚከሰተው የትራፊክ አደጋ በአብዛኛው የአሽክርካሪዎች ብቃት ማነስ ነው ያሉት አስተባባሪው ይህንና የቀድሞውን የመንጃ ፈቃድ አሰጣጥ ችግር በመቅረፍ ቀልጣፋ የአሽከርካሪዎች ምዘናን የሚያረጋግጥ ግልፅና ውጤታማ አሰራር ለመዘርጋት እንደሚያስችል የስራ ሂደቱ ባለቤት ተናግረዋል፡፡ በሃዋሳ ከተማ እየተገነባ የሚገኘው የአሽከርካሪዎች ምዘና የትራፊክ ኮምፕሌክስ ተቋም በኮምፒውተር መረጃ ኔትወርክ የተገናኙ የመቆጣጠሪያ መሳሪያዎችና ዘመናዊና አዲስ የመፈተሻ ቴክኖሎጂ ይገኙበታል ብለዋል፡፡ አሰራሩን በክልሉ ሁሉም አከባቢዎች ተደራሽ ለማድረግ የክልሉ መንግስት በመደበው 30 ሚሊዮን ብር በአርባምንጭ፣ በሆሳዕናና በሚዛን አማን ከተሞች የአሽከርካሪ ብቃት ምዘና የሚደረግባቸው ዘመናዊ የትራፊክ ኮምፕሌክስ ግንባታ ለማስጀመር ዝግጅቱ መጠናቀቁንና በሁለቱ ከተሞች ከያዝነው ወር ጀምሮ ስራው መጀመሩን ጠቁመዋል፡፡

የ121 ዓመት አድሜ ባለጸጋ የሆኑት የአቶ ጠቀቦ ሾታ የቀብር ስነ-ስርዓት ተፈጸመ::

ዲላ ሐምሌ 02/2005 የጌዴኦ አርሶ-አደር በነፍጠኛው ስርዓት ላይ ባካሄደው ትግል ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከቱት እና የ121 ዓመት አድሜ ባለጸጋ ከዚህ አለም በሞት ተለዩ ። የአቶ ጠቀቦ ሾታ ቀብር በጌዴኦ ባህላዊ ስነ-ዓስርዓት በዲላ ዙሪያ ወረዳ ዛሬ ተፈጸመ ። አቶ ጠቀቦ ሾታ ከአስራ ሁለት ሚስቶቻቸው ሰማንያ ሰባት ልጆች እና ከአንድ ሺህ በላይ የልጅ ልጅ ያፈሩ እንደነበሩም በቀብር ስነስረአቱ ላይ በተነበበዉ የህይወት ታሪካቸው ላይ ተገልጿል ። አቶ ጠቀቦ ሾታ በ1884 ዓመተ ምህረት በዲላ ዙሪያ ወረዳ ሚቺሌ ተብሎ በሚጠራው ስፍራ መወለዳቸዉን ቀብር ስነ-ስርዓታቸው ላይ የተነበበው የህይወት ታሪካቸው ያስረዳል ። በጌዴኦ አርሶ አደር ላይ ይደርስ የነበረውን የጭቆና አገዛዘ በጽኑ በመቃወም በ1952 ዓመተ ምህረት በነፍጠኛው ስርዓት ላይ ከፍተኛ ጥቃት በመሰንዘር የሚቺሌን ድል ካስመዘገቡ አባቶች መካከል አንዱ ነበሩ ። አቶ ጠቀቦ ሾታ ከዚህ የትጥቅ ትግል በመለስ በጌዴኦ ብሄርና በአጎራባች ወረዳዎች እና ክልል ህዝቦች መካከል ሰላማዊ ግንኙነት እንዲሰፍን በማድረግና ግጭቶች እንዳይከሰቱ የበኩላቸውን ከመወጣታቸውም ባሻገር የጌዴኦ ባህልን ለማሳደግ የዞኑን ልማት ለማፋጠን ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳበረከቱ ተጠቁሟል ። በህዝባዊ ውይይቶች ህብረተሰቡን በመወከል በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተሳታፊ በመሆን ለጌዴኦ ህዝብ እድገት የበኩላቸውን መወጣታቸውንና ለፈጸሙት መልካም ተግባር በጌዴኦ ባህል ለጀግና የሚሰጠውን የሀይቻነት ማእረግም ማግኘታቸውም ተመልክቷል ። የረጅም እድሜ ባለጸጋ የሆኑት አቶ ጠቀቦ ሾታ የቀብር ስነ-ስርዓት ላይ የደቡብ ብሄር ብሄርሰቦችና ህዝቦች ክልል ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ የጌዴኦ ዞን ካቢኔ አባላት የስድስቱም ወረዳና የሁለቱ ከተማ አስተዳደር አመራሮች እንዲሁ

የቀድሞው የሃዋሳ ከተማ ስራ ኣስኪያጂ የነበሩት እና በኃላ ላይ የመንግስት ቤቶች ኤጀንሲ ዳይሬክተር የሆኑትን ኣቶ ተፈሪ ፍቅሬ ጨምሮ ሌሎች ሁለት ዳይሬክተሮች በኪራይ ሰብሳቢነት ተገምግመው ከስራ ሃላፊነታቸው ተነሱ::

የመንግስት ቤቶች ኤጀንሲ ዋና ዳሬክተር አቶ ተፈሪ ፍቅሬና ሁለት ምክትል ዳይሬክተሮች በኪራይ ሰብሳቢነት ተገምግመው ከስራ ሃላፊነታቸው እንደተነሱ ተገለፀ፡፡ ተጠሪነቱ ለስራና ከተማ ልማት ሚኒስቴር የሆነው የቤቶች ኤጀንሲ ከትላንት በስቲያ ሶስቱን ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ከሥራ ሃላፊነታቸው ያነሳው በተለያየ ደረጃ ግምገማ ከተካሄደ በኋላ እንደሆነ ምንጮቻችን ገልፀዋል፡፡ የፀረ ሙስና ኮሚሽንም ከአንድ ዓመት በላይ በሥራ ሃላፊዎቹ ላይ ምርመራ ሲያደርግ እንደቆየ የጠቀሱ ምንጮች፤ ሃላፊዎቹ በኪራይ ሰብሳቢነትና ሃላፊነትን በአግባቡ ባለመወጣት ተገምግመው ነው ከሥራ ሃላፊነታቸው የተነሱት ብለዋል። http://dezetube.com/article_read.php?a=451

የአቶ ሽፈራው ሽጉጤ ወደ ፌዴራል መንግሥት ሚኒስትርነት መምጣት በደቡብ ክልል ላይ ጊዜያዊ ክፍተት የፈጠረ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ለክልሉ ፕሬዚዳንትነት የስድስት ግለሰቦች ስሞች እየተነሱ ነው፡፡

የአቶ ሽፈራው ሽጉጤ ወደ ፌዴራል መንግሥት ሚኒስትርነት መምጣት በደቡብ ክልል ላይ ጊዜያዊ ክፍተት የፈጠረ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ለክልሉ ፕሬዚዳንትነት የስድስት ግለሰቦች ስሞች እየተነሱ ነው፡፡ ከእነዚህ መካከል ከሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስትርነታቸው በመነሳት በኦሮሚያ ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ወ/ሮ ደሚቱ ሃንቢሳ የተተኩት አቶ ደሴ ዳልኬ አንደኛው ናቸው፡፡ ሌሎቹ በጃፓን የኢትዮጵያ አምባሳደር የሆኑት አምባሳደር ማርቆስ ተክሌና በአሁኑ ወቅት የክልሉ ምክትል ፕሬዚዳንት በመሆን የሚያገለግሉት አራት ግለሰቦች ናቸው፡፡  እነሱም አቶ ታገሰ ጫፎ፣ አቶ ዓለማየሁ አሰፋ፣ አቶ ሳኒ ረዲና አቶ ደበበ አሰፋ ናቸው፡፡ ግምት ከተሰጣቸው መካከል የበለጠ ከፕሬዚዳንትነት ሥልጣኑ ጋር በተደጋጋሚ ስማቸው እየተጠራ የሚገኘው አምባሳደር ማርቆስ ተክሌ ሲሆኑ፣ በሁለተኛ ደረጃ አቶ ደሴ ዳልኬ ሊሆኑ ይችላል የሚል ግምት አለ፡፡ ባለፈው ሐሙስ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ የከፍተኛ መንግሥት ባለሥልጣናትን ሹመት በፓርላማ አፀድቀዋል፡፡ የአሥሩ አዲስ ተሿሚዎች ሹመት የፀደቀው በአንድ ድምፅ ተአቅቦና በአብላጫ ድምፅ ነው፡፡ ተሿሚዎቹ በጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ተገኔ ጌታነህ አማካይነት ቃለ መሃላ ፈጽመዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ባለፈው ረቡዕ አቶ በረከት ስምዖንና አቶ ኩማ ደመቅሳ በሚኒስትር ማዕረግ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የፖሊስ ጉዳዮች አማካሪ ሆነው መመደባቸው ተገልጿል፡፡  በቅርቡ በፓርላማ የትምህርት ሚኒስቴርን የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ሲያቀርቡ በዘርፉ ለሚታዩ ችግሮች ከሚኒስትር ጀምሮ እስከታች ያሉ አመራሮችን የወቀሱት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የትምህርት ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን፣ በአቶ ኃይለ ማርያም አዲስ ሹመትና ሽግሽግ ከትምህርት ሚኒስትርነታቸው ተነስተዋ

የኢትዮጵያ ቡና ከዓለም ገበያ እየራቀ መሆኑ ሥጋት ፈጥሯል

Image
የኢትዮጵያ ቡና ከዓለም አቀፍ ገበያ እየራቀ መጥቶ፣ ከነጭራሹ ሊወጣ የተቃረበበት ጊዜ ላይ እንደሚገኝ ለዘርፉ ቅርብ የሆኑ ተዋንያዎች የሚስማሙበት ሀቅ ነው፡፡  ኢትዮጵያ ለዓለም ቡናን ያበረከተች አገር ከመሆኗ ባሻገር እጅግ ተወዳጅ የሆነ ቡና የምታመርት አገር ናት፡፡ ዓለም አቀፍ የቡና ገዥዎች ይህንኑ የጣዕም ልዩነት በመረዳት የኢትዮጵያን ቡና ለመግዛት ከፍተኛ ፍላጎት ቢኖራቸውም፣ በቢሮክራሲ ውጥንቅጦች ምክንያት ቡናውን ማግኘት እንዳልቻሉ እየተናገሩ ነው፡፡  በቡና ግብይት ላይ ያለው ውጣ ውረድ ከፍተኛና ገዥዎች የማይተማመኑበት ደረጃ ላይ እየደረሰ በመሆኑ፣ በዓለም አቀፍ ገበያ በጣዕሙ ተወዳዳሪ የማይገኝለት የኢትዮጵያ ቡና ዋጋ እያጣ መምጣቱ የሚያስቆጭ ወቅታዊ ጉዳይ ሆኗል፡፡ የችግሩ ምንጮች በዋነኛነት የመንግሥት የቡና ግብይት አቀንቃኞቹ የንግድ ሚኒስቴርና የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ድርጅት እንደሆኑ የዘርፉ ተዋናዮች ያምናሉ፡፡  የቡና ግብይት ተዋናዮች እንደሚሉት፣ የችግሩ ምንጮች በእነዚህ ሁለት መንግሥታዊ ተቋማት የተወለዱ ችግሮች ናቸው፡፡ በመጀመሪያ የንግድ ሚኒስቴር የቡና ግብይት ዘርፍ የሥራ ኃላፊዎች የቡና ግብይት ሁኔታን በሚገባ አለመረዳታቸው ነው፡፡ በሁለተኛ ደረጃ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ የሥራ ኃላፊዎች የግብይት ሁኔታውን ቢያውቁም፣ የመወሰን አቅም የሌላቸው በመሆኑ ነው፡፡ ‹‹እነዚህ አካላት ግን ያሉባቸውን የተወሰኑ ችግሮች ለማረም አልሞከሩም፤›› ይላሉ የተበሳጩት የቡና ግብይት ተዋናዮች፡፡ በምርት ገበያ በኩል አሉ ከሚባሉት ችግሮች መካከል አንዱ የቡና ልኬት (ሚዛን) ችግር ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ቀደም ባሉት ዓመታት በቡና ግዥ ሒደት የቡና ገለፋት በ20 በመቶ ታሳቢ ተደርጎ በግዥ ሒደት ቅናሽ ይደረግ ነበር፡፡ አሁን ባለው የምርት ገበያ