Posts

አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ወላሳ - የትምህርት ሚኒስትር ሆነው ተሾሙ

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 27 ፣ 2005 (ኤፍ ቢ ሲ) የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተለያዩ የመንግስት ሚኒስትሮችን እና የስራ ሃላፊዎችን ሹመት አጸደቀ። ምክር ቤቱ ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባው በኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሰላኝ የቀረቡ እጩዎችን ሹመት በ1 ድምጸ ተዓቅቦ እና በአብላጫ ድምጽ አጽድቆታል። በዚህም መሰረት አቶ ደመቀ መኮንን - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ወላሳ - የትምህርት ሚኒስትር አቶ ሬድዋን ሁሴን ራህመቶ-  የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ሚኒስትር አቶ አህመድ አብተው አስፋው - የኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ ወርቅነህ ገበየሁ ነገዎ - የትራንስፖርት ሚኒስትር ወይዘሮ ሮማን ገብረስላሴ መሸሻ - በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ወይዘሮ ደሚቱ ሃንቢሳ ቦንሳ - የሳይንስ እና ቴክኖሎጅ ሚኒስትር አቶ ጌታቸው አምባዬ በለው - የፍትህ ሚኒስትር አቶ በከር ሻሌ ዱሌ - የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ በለጠ ታፈረ ደስታ - የአካባቢ ጥበቃና የደን ሚኒስትር አቶ መኮንን ማንያዘዋል እንደሻው - የብሄራዊ ፕላን ኮሚሽን ኮሚሽነር በመሆን የተሾሙ ሲሆን ፥ በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ተገኔ ጌታነህ አማካኝነት ቃለ መሃላቸውን ፈጽመዋል።

የስምንት ሚኒስትሮች ሹመት ሰሞኑን ይፀድቃል

የኢህአዴግ ከፍተኛ አመራር ዛሬ ግምገማ ያካሂዳል የኢህአዴግ 36 ከፍተኛ መሪዎችን ያካተተው የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አመታዊ ግምገማ ለማካሄድ ዛሬ የሚሰበሰብ ሲሆን የስምንት ሚኒስትሮች ሹም ሽርና ሽግሽግ በሚቀጥለው ሳምንት ለፓርላማ ቀርቦ እንደሚፀድቅ ይጠበቃል፡፡ ለሹመት የሚቀርቡት ባለስልጣናት፤ የፍትህ ሚኒስትር፣ የከተማና ኮንስትራክሽን ልማት ሚኒስትር፣ የግብርና ሚኒስትር፣ የትራንስፖርት ሚኒስትር፣ የገቢዎች ሚኒስትር የደህንነትና መረጃ ሚኒስትር፣ የደንና አካባቢ ጥበቃ ሚኒስትር እንዲሁም በፓርላማ የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትር ናቸው ተብሏል፡፡ አንዳንዶቹ ሹምሽር እርምጃዎች ሲሆኑ፤ አንዳንዶቹ ደግሞ ወደ አዲስ አበባ አስተዳደር እንዲዛወሩ በተደረጉ ባለስልጣናት ምትክ የሚካሄድ ሽግሽግ ነው፡፡ ይሁን እንጂ የእጩ ተሿሚዎችን ማንነት ለማወቅ ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም፡፡ ዛሬ የሚካሄደው የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ስብሰባ ከሹምሽሩ ጋር የተያያዘ እንደሆነ ቢታሰብም፣ የሰብስባው ዋና ርዕሰ ጉዳይ አመታዊ ግምገማና አመታዊ እቅድ እንደሆነ ተነግሯል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚመሩት አስፈፃሚ አካል የመቆጣጠር ስልጣን ያለው የአገሪቱ ፓርላማ ጠንካራ የቁጥጥር ሃላፊነቱን በተግባር ማሳየት እንደጀመረ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ጭምር ቢናገሩም፤ በሚኒስትሮች ሹመት ዙሪያ ግን የቀድሞው አሰራር አልተሻሻለም፡፡ በተለያዩ ዲሞክራሲያዊ አገራት ውስጥ የእጩ ሚኒስትሮች ማንነት በይፋ ታውቆ ለበርካታ ሳምንታት በፓርላማና በዜጐች ዘንድ ውይይት የሚካሄድበት ቢሆንም፣ በኢትዮጵያ ግን የተሿሚዎች ማንነት የሚገለፀው ሹመታቸው በሚፀድቅበት እለት ነው፡፡ የስራ አስፈፃሚው ኮሚቴ ዛሬ ስብሰባ እንደሚያካሂድ የገለፁት የኢህአዴግ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ሬድዋን ሁሴን፤ የስብሰባው ዓላማ የዓመቱን የስራ አፈፃፀም

በመጪዎቹ 10 ቀናት በርካታ ቦታዎችን የሚሸፍን ዝናብ ይኖራል

Image
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 27/2005 (ዋኢማ)  - በመጪዎቹ አሥር ቀናት በመደበኛ ሁኔታ የክረምት ዝናብ ሰጪ ክስተቶች በአብዛኛው የአገሪቱ አካባቢዎች ላይ ከመጠናከራቸው ጋር ተያይዞ ብዙ ቦታዎችን የሚሸፍን ዝናብ እንደሚኖር ብሔራዊ የሚቲዎሮሎጂ ኤጀንሲ አስታወቀ፡፡  በመጪዎቹ ቀናት ዝናብ ሰጪ ክስተቶች በአብዛኛው የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ አካባቢዎች ላይ ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የትንበያ መረጃዎች እንደሚያሳዩ ገልጿል፡፡  በመሆኑም አብዛኛውን የወቅቱን ዝናብ ተጠቃሚዎች የሚያዳርስ የተስፋፋ ዝናብ እንደሚኖርና አልፎ አልፎም በአንዳንድ ሥፍራዎች ላይ ከባድ ዝናብ ይከሰታል፡፡ በዚሁ መሠረት የትግራይና የአማራ ምዕራባዊ አጋማሽ፣ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ የጋምቤላ፣ የምዕራብና የመካከለኛው ኦሮሚያ፣ የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል አብዛኛው ክፍል መደበኛና ከመደበኛ በላይ ዝናብ ያገኛሉ፡፡  እንዲሁም የምሥራቅ አማራና ትግራይ፣ የአፋር፣ የምሥራቅ ኦሮሚያ፣ የድሬዳዋ፣ የሐረሪና የሰሜን ሶማሌ አካባቢዎች ከመደበኛው ጋር የተቀራረበ ዝናብ ይኖራቸዋል፡፡ በተጨማሪም በአንዳንድ የአገሪቱ አካባቢዎች ላይ በረዶ የቀላቀለና ነጎድጓዳማ ከባድ ዝናብ እንደሚኖር የጠቀሰው የኤጀንሲው መግለጫ ቀሪዎቹ የአገሪቱ አካባቢዎች ደረቅ ሆነው ይሰነብታሉ ብሏል፡፡ በነዚሁ ቀናት መደበኛና ከመደበኛ በላይ ዝናብ እንዲሁም ከመደበኛ ጋር የተቀራረበ ዝናብ በሚጠበቅባቸው የአገሪቱ ምሥራቃዊ አካባቢዎች የሚገኘው ዝናብ ለመኸር እርሻ ሥራ እንቅስቃሴ አመቺ ሁኔታን ስለሚፈጥር የተገኘውን እርጥበት በመጠቀም የወቅቱን እርሻ ለማካሄድ ያስችላል፡፡  በአንዳንድ ሥፍራዎች ላይ የሚጠበቀው ከመደበኛ በላይ የሆነ ዝናብ በተዳፋትና ለጎርፍ ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች እርሻ ማሳዎች ላይ የአፈር መሸርሸርና የውሃ መተኛት ሊያጋጥም

ከ800 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተጀመረው የ15 ከተሞች የውኃ ፕሮጀክት ተቋረጠ

-    ፕሮጀክቱ የተቋረጠው የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ ውሉን በማፍረሱ ነው የውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከዓመታት በፊት ከ800 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የጀመረው የ15 ከተሞች የመጠጥ ውኃ ፕሮጀክት ተቋረጠ፡፡ የፕሮጀክቱን ወጪ ብድር የሰጠው የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ ውሉን ማፍረሱ ለፕሮጀክቱ መቋረጥ ምክንያት መሆኑን ምንጮች ገልጸዋል፡፡ በአማራ፣ በኦሮሚያ፣ በደቡብና በትግራይ ክልሎች ለሚገኙ 15 ከተሞች የመጠጥ ውኃ አቅርቦት ለማሻሻልና 500 ሺሕ ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ ከሦስት ዓመታት በፊት የተጀመረውን ፕሮጀክት በሁለት ዓመታት ውስጥ ለማጠናቀቅ ዕቅድ ተይዞ ነበር፡፡  ፕሮጀክቱ የሚፈጀውን ከ800 ሚሊዮን ብር በላይ ወይም 36 ሚሊዮን ዩሮ በብድር የለገሱት የአውሮፓ ኮሚሽንና የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ በጋራ በመሆን ነበር፡፡  በዚህ ከፍተኛ ገንዘብ ፕሮጀክቱ በ15 ከተሞች ቢጀመርም በተያዘለት ጊዜ መጠናቀቅ ባለመቻሉ፣ የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ የሰጠውን 16 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ውል ለማፍረስ መገደዱን ምንጮች ያስረዳሉ፡፡  በጉዳዩ ላይ የተጠየቁት የውኃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ አቶ ዓለማየሁ ተገኑ ለፕሮጀክቱ መጓተት ኮንትራክተሮችን ወቅሰዋል፡፡ ኮንትራክተሮቹ በባንኩ የጨረታ ሕግ ተገምግመው ሥራው ቢሰጣቸውም ደካማ በመሆናቸው ፕሮጀክቱን በጊዜው መፈጸም አለመቻላቸውን ገልጸዋል፡፡ ከኮንትራክተሮቹ ላይ ለመንጠቅ በባንኩ አሠራር የተነሳ በመቸገሩ ሥራው መጓተቱን፣ በውሉ መሠረት ፕሮጀክቱ በጊዜው ባለመጠናቀቁ ውሉ ሊቋረጥ ምክንያት ሆኗል ብለዋል፡፡ ከዚህ ጉዳት በመነሳትም የውኃ ሥራ ኮንትራክተሮች ከዚህ በኋላ ፈቃዳቸውን ሊያድሱ የሚችሉት ብቃታቸው ተገምግሞ እንደሚሆን፣ በዚህ ፕሮጀክት ላይ ጉዳት ያደረሱትንም

በአቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ላይ ለሙስና ኮሚሽን ጥቆማ ቀረበ ተባለ

ስልጣናቸውን መከታ በማድረግ በደቡክ ክልል ፕሬዚዳንት በነበሩበት ጊዜ በቤተሰቦቻቸው እና በሃዋርያት ቤተክርስቲያን መሪዎች ስም በመሬት ቅርሚያ እና ችብቸባ ስራ ላይ ተሰማርተው ነበር ሲሉ አንድ ከአዋሳ ግለሰብ የመጡ ማስረጃቸውን አያይዘው ለሙስና ኮሚሽን ጥቆማ መስጠታቸውን አንዲት በኮሚሽኑ ውስጥ የሚሰሩ ግለሰብ ለምንሊክ ሳልሳዊ ተናግረዋል::ግለሰቧ እንዳሉት ወደ ኮሚሽኑ የመጡት ሰው የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት አማካሪ የነበሩ ሲሆንጥቆማውን እና ማስረጃቸውን የተቀበሏቸው በቀጠሮ ኮሚሽነር አሊ ሲሆኑ ለረዥም ሰአት ተነጋግረዋል:: በአቶ ሃይለማርያም ላይ የመጣው ጥቆማ እንደሚያመለክተው ብስልጣናቸው ተጠቅመው በኢናታቸው እና በአባታቸው ቤተሰቦች ስም እንዲሁም በቤተ ክርስቲያን መሪዎች ስም ለተለያየ ጊዜ መሬቶችን በመውሰድና በመሸጥ ሰፋፊ እርሻዎችን በመያዝ የቡና እና የፍራፍሬ ተክሎችን ወደ ኬንያ በኮንትሮባንድ በመላክ የኢትዮጵያን ድንበር ተገን በማድረግ በህገወጥ ንግድ እና የመሳሪያ ንግድ ላይ ለተሰማሩ ሰዎች ከለላ በመስጠት የተለያዩ ስኮላርሺፖችን በማስመጣት እና በመሸጥ እንዲሁም ከትግሬ ጄኔራሎች ጋር በመተባበር የሃሰት ሰንዶችን በማዘጋጀት የመንግስት እና የህዝብ ንብረቶችን ዘርፎ በማዘረፍ የሚሉ እና ተመሳሳይነት ያላቸው ጥቆማዎች እንደተሰጡ ግለሰቧ ገልጸዋል:: አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ ቦታዎች በሃዋርያት ቤተክርስቲያን ስም የራሳቸውን ህንጻ ገንብተዋል እየገነቡም ነው ለመገንባትም የታሰቡ ፕሮጀክቶች አሉ የሚል ተደራራቢ የህንጻ ግንባት ጥቆማ ተደርጎባቸዋል:: ከዚሁ ጋር በተያያዘ የሃዋርያት ቤት ክርስቲያን አቶ ሃይለማርያምን እና ሌሎች ባለስልጣናትን ተገን በማድረግ በሙስና መጨማለቋን እኚሁ ግለሰብ ከሰጡት ጥቆማ ጋር የተገለጸ ሲሆን