የዘመን መለወጫ በሲዳማ
በሲዳማ የጊዜ አቆጣጠር መሰረት የሳምንቱ ቀናት በስም አራትናቸው። እነሱም ቃዋዶ፣ ቃዋላንካ፣ ዴላ፣ዲኮ በሚል መጠሪያ ተለይተው የታወቃሉ። እንዲሁም አንድ ወር አጋና (ጨረቃ) እና ቱንሲቾ(ጨለማ) ተብሎ በሁለት ይከፈላል። እያንዳንዱ ወር በቋንቋው ተለይቶ የሚታወቅበት የራሱ መጠሪያ (ሥያሜ) ያለው ሲሆን ፤ ወራቱ አስራ ሁለት ናቸው። በነባሩ የሲዳማ ባህላዊ የጊዜ አቆጣጠር ውስጥ ጷግሜ ፎቃ የሚል ስያሜ ተሰጥቶቷል። በነባሩ የሲዳማ የጊዜ ቀመር አቆጣጠር መሰረት በዓመት ውስጥ ያሉት አስራ ሁለት ወራት በአራት ወቅቶች የተከፈሉ ናቸው። ከዚሁ አንጻር ወቅቶቹ አሮ(በጋ)፣ሀዋዶ(ክረምት)፣በዴሳ (በልግ) እና ቢራ (መኸር) የሚል መጠሪያ አላቸው። በባህሉና በጊዜ ቀመሩ መሰረት ሲዳማ የራሱ ዘመን መለወጫ ቀን አለው።ይህም ፍቼ በሚል መጠሪያ ይታወቃል። የዘመን መለወጫ( ፍቼ) በአል አከባበር ፍቼ በሲዳማ ባህል በዓመት አንዴ በድምቀት የሚከበር የዘመን መለወጫ በዓል ነው። በባህሉ መሰረት አከባበሩ እስከ ሁለት ሳምንት ይዘልቃል። የፍቼ በዓል ቅደም ተከተላዊ የአከባበር ሂደቱ ከመጀመሩ በፊት ለአከባበሩ መነሻና መድረሻ የሚሆኑ ክንውኖች አሉ። ከእነዚህ ክንውኖች የመጀመሪያው ላኦ(ምልከታ) ነው። ላኦ ፍቼ መቼ እንደሚውል አያንቶዎች (የስነክዋክብት ተመልካቾች አረጋውያን) የጨረቃንና የከዋክብትን አካሄድ ጥምረት ተመልክተው የሚለዩት ሲሆን፤ አያንቶዎች ፍቼ ቀኑ መቼ እንደሚውል በከዋክብት ምልከታ ከለዩ በኋላ ለጎሳ መሪዎች ይገልጻሉ። የጎሳ መሪዎች ቀኑ ተገልጾ ለህብረተሰቡ እንዲለፈፍ ሲያዙ በገበያ ስፍራዎች በላላዋ (በልፈፋ) ይገለጻል። ላላዋ (ልፈፋ) የጎሳ መሪዎች ስር ባሉ ስፍራዎች የሚከወን ሲሆን ፤ ለፋፊዎች በገያ ቀን የበግ ቆዳ ረዠም ዘንግ ላይ ሰቅለው በመያዝ