Posts

በጥረት የተገኘ ስኬት

በጥረት የተገኘ ስኬት /ከበለጠ አድነዉ /ሃዋሳ ኢዜአ/ ቁጠባ የግለሰብን ኑሮ ከመቀየር ጀምሮ ለሀገር እድገት የሚኖረው ጠቀሜታ ከፍተኛ ነው፡፡ዛሬ በዓለማችን ላይ አንቱ ተብለው የሚጠቀሱ ባለሀብቶች ምንጫቸው ትንሿን ገንዘብ ብዙ እንድትሆን በተለያዩ የቆጠባ ዘዴዎች ቆጥበው ነው፡፡አሁን አሁን በተለያዩ ተቋማት ውስጥ በሚቋቋሙ የብድርና ቁጠባ ተቋማት፣በባንክ፣በማህበራትና በሌሎችም የቆጠባ ዘዴዎች በመቆጠብ በርካቶች ተጠቃሚ ሆነዋል፡፡በዚህም በርካታ ወገኖች ኑሯችውን ቀይረውበታል፡፡ ወይዘሮ አበባ ዘነበ ይባላሉ፡፡የሐዋሳ ከተማ ነዋሪ ናቸው፡፡ባለቤታቸው ከብድርና ቁጠባ ተቋም ባገኙት 500 ብር መነሻ ካፒታል የጀመሩት ባህላዊ የአልባሳት ጥልፍ ሥራ ስኬታማ አያደረጋቸው ነው፡፡የጥልፍ ሥራው በአጭር ጊዜ ውስጥ ትርፋማ ስላደረጋቸው ዘመናዊ የጠረጴዛና የጥልፍ ስፌት ማሽኖችን ገዝተው የብሄረሰቦችን ልዩ ልዩ አልባሳት በማዘጋጀትና በማስተዋወቅ ተጠቃሚ ሆነዋል፡፡ ወይዘሯዋ በራሳችን ባህላዊ አልባሳት መዋብ እንችላለን ብለው በመነሳሳት ሳይታከቱ በመስራታቸው ዛሬ ከከተማውና ከክልሉ አልፎ በሀገር አቀፍ ደረጃ እውቅና አግኝተው ለተለያዩ ስብሰባዎች፣ ለጉብኝትና ለበአላት የሚውሉ አልባሳት እንዲዘጋጅላቸው በርካታ ጥያቄዎች እየቀረበላቸው ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት አዲስ አበባ የሚገኙ የተለያዩ የአፍሪካ አገራት ኢንባሲዎች ሳይቀሩ የየሀገራቸው የባህል ልበስ እንዲዘጋጅላቸው ጥያቄ እያቀረቡላቸው መሆኑን ይናገራሉ፡፡የአካባቢው አስተዳደር የስራ ውጤታቸውን በማየት የመስሪያ ቦታ፣ የሙያና የምክር ድጋፍ በመስጠት የሚያደርግላቸው እገዛ ለስራቸው መሻሸል ከፍተኛ ብርታት ሆናቸዋል፡፡ ወይዘሮ አበባ በአሁኑ ወቅት ኑሮአቸውን ከመለወጣቸውም በላይ ካፒታላቸው 2 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር ደርሷ

የተምች ትል በሲዳማ ዞን በ ቦርቻ፤ ቦና፤ ዳራ፤ ዳሌ፤ ሃዋሳ ዙሪያ እና በሎካ ኣባያ ወረዳዎች በበቆሎ እና በሌሎች ቡቃያዎች ላይ ጉዳት ማድረሱ እየተነገረ ነው

Image
የተምች ትል በሲዳማ ዞን በ ቦርቻ፤ ቦና፤ ዳራ፤ ዳሌ፤ ሃዋሳ ዙሪያ እና በሎካ ኣባያ ወረዳዎች በመህር ምርት ላይ ጉዳት ማድረሱ እየተነገረ  ነው Army Worm Destroys 8,368ha of Cropland Region Close to 8,368ha of belg cropland was reportedly destroyed by army worms in Wolayita zone of Southern Regional State, an area that suffered from late onset of the 2013 belg rains and subsequent heavy rains that damaged belg crops, a weekly Humanitarian Bulletin, published by UN Office for the Coordination of Humanitarian Affairs revealed. Immediate distribution of spraying containers and chemicals to the farmers is required to prevent further loss of belg crops, according to the Office. The Office also warns the damage caused by the army worms will further reduce the expected harvest this season. Similar incidents were also reported from Boricha, Bona Zuria, Dara, Dale, Hawassa Zuria and Loko Abaya weredas of Sidama zone located in Southern Regional State as well as from drought prone areas of East and West Hararge zones of Oromia Regi

መንግሥት ሕዝቡ ለአገሩ ዘብ እንዲቆም ጥሪ አቀረበ

Image
የግብፅ ፖለቲከኞች ከአፍራሽ ድርጊታቸው ይቆጠቡ ብሏል የግብፅ ፕሬዚዳንት፣ ጠቅላይ ሚኒስትርና ሌሎች የአገሪቱ ከፍተኛ ባለሥልጣናት በተገኙበት ባለፈው ሰኞ በተካሄደው ብሔራዊ የናይል ኮንፈረንስ ላይ ታላቁን የህዳሴ ግድብ በተመለከተ በተንፀባረቀው አፍራሽ መልዕክት የተበሳጨው የኢትዮጵያ መንግሥት፣ “ሕዝቡ ለአገሩ ዘብ እንዲቆም” ሲል ጥሪ አቀረበ፡፡ የግብፅ ፖለቲከኞችም ከአፍራሽ ድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አሳስቧል፡፡ የግብፅ ፕሬዚዳንት መሐመድ ሙርሲ፣ የአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር፣ ሚኒስትሮችና የፀጥታ ባለሥልጣናት በተገኙበት በተካሄደው በዚሁ ስብሰባ፣ “የህዳሴ ግድቡ በግብፅ ላይ አደጋ በመደቀኑ በኢትዮጵያ ላይ በተለያዩ መንገዶች ተፅዕኖ በመፍጠር የግድቡን ሥራ ለማስቆም እንቅስቃሴ እናደርጋለን፤” በማለታቸው የኢትዮጵያ መንግሥት “አፍራሽ ድርጊት” በማለት አጣጥሎታል፡፡  የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ፣ ማክሰኞ አመሻሽ ላይ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ነበር የመንግሥትን አቋም ግልጽ ያደረጉት፡፡ “በህዳሴው ግድብ ሽፋን የውስጥ ችግርን ለማቃለል የሚደረገው ጥረት የግብፅን ዘላቂ ጥቅም አያስጠብቅም፤” ያሉት አምባሳደር ዲና፣ “ጦርነቶችና ሌሎች አፍራሽ ድርጊቶች ያረጁና ያፈጁ የ21ኛው ክፍለ ዘመን አስተሳሰብ የማይሸከማቸው ጤናማ ያልሆኑ አስተሳሰቦች ናቸው፤” በማለት የግብፅ ባለሥልጣናትን ድርጊት አጣጥለውታል፡፡ ኢትዮጵያ በዚህ ቀረርቶ ተደናግጣ ግንባታውን ለአንዲት ሰከንድም ቢሆን እንደማታቆም አረጋግጠዋል፡፡ “የግብፅ ወገኖችም ከዚህ አፍራሽ ድርጊት እንዲቆጠቡ፤” ሲሉ አሳስበዋል፡፡  “የኢትዮጵያ መንግሥት የግብፅ መንግሥት እየያዘው ባለው መንገድ የዲፕሎማሲ ሥራ እየሠራ ነው ወይ?” በሚል ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱ፣ መንግሥት አስፈ

አስገዳጁ የቁጥጥር ደረጃ ጊዜ ገደብ የግል ጤና ተቋማትን ሥጋት ውስጥ ከትቷል

-  ሁኔታውን የሚያጤን ቡድን እየተዋቀረ ነው በኢትዮጵያ የምግብ፣ የመድኃኒትና ጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለሥልጣን ተዘጋጅቶ በኢትዮጵያ ደረጃዎች ኤጀንሲ 2004 ዓ.ም. መጨረሻ ላይ የፀደቀው አስገዳጅ የጤና ተቋማት የቁጥጥር ደረጃ ጊዜ ገደብ እንዳሠጋቸው የግል ክሊኒኮች አስታወቁ፡፡   ለአዳዲስ የጤና ተቋማት ከፀደቀበት ጊዜ ጀምሮ ለነባሮች ደግሞ ከፀደቀ ከአንድ ዓመት ተኩል በኋላ ተግባራዊ እንደሚሆን የተገለጸው የቁጥጥር ደረጃ፣ 39 ዓይነት የጤና ተቋማትን መስፈርት ያስቀምጣል፡፡  በመድኃኒት ቁጥጥርና አስተዳደር ባለሥልጣን የቁጥጥር ደረጃ ዝግጅትና አስተባባሪ የሆኑት ሲስተር የሺዓለም በቀለ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ደረጃው የመንግሥት እንዲሁም የግል ተቋማትንም የሚመለከት ሲሆን ሆስፒታሎች፣ ክሊኒኮች፣ የጤና ጣቢያዎችንና ጤና ኬላዎችን ጭምር ያካትታል፡፡  እሳቸው እንደሚሉት፣ ከፍተኛ ክሊኒክ የሚባሉት ልዩ የሕክምና ማዕከላት (Specialty Center) መሆን የሚችሉ ሲሆን፣ ለዚህ በትንሹ አሥር አልጋዎች፣ ሁለት ስፔሻሊስት ሐኪሞች እንዲሁም ፋርማሲ ሊኖራቸው ይገባል፡፡ ይህን ማሟላት ካልቻሉ ደግሞ ሁለት ወይም ሦስት የተመላላሽ ታካሚ አልጋ ኖሯቸው በአንድ ስፔሻሊስት ሐኪም አጠቃላይ አገልግሎት የሚሰጥ መካከለኛ ጤና ተቋም መሆን ይችላሉ፡፡ እንዲህ እንዲህ እያሉ ማሟላት እንደሚችሉ የመስፈርት አማራጮች ተቀምጠዋል፡፡  ክሊኒኮች የባለሙያ እጥረትን እንዲሁም የቦታ ጥበትን መሠረት ያደረጉ የተለያዩ ቅሬታዎችን ያሰሙ ሲሆን፣ አንድ ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ የከፍተኛ ክሊኒክ ባለቤት “ሁኔታው በጣም አስቸጋሪ ነው፡፡ የቻልነውን ያህል መስፈርቶቹን አሟልተን ለመቀጠል እንሞክራለን ካልሆነ ግን እንዘጋለን፤” በማለት ለሪፖርተር አስተያየታቸውን ሰጥተ

ኢኮኖሚውን ወደ አንድ ትሪሊዮን ብር የሚያሳድገው በጀት ለፓርላማ ቀረበ

- ሚኒስትር ሱፊያን ለመጀመርያ ጊዜ ጠንካራ ቁጥጥር ገጠማቸው -ለመንገድ 29.1 ቢሊዮን ብር ለመከላከያ 7.5 ቢሊዮን ብር ተይዟል የኢትዮጵያን አጠቃላይ የአገር ውስጥ ምርት (ጂዲፒ) ወደ አንድ ትሪሊዮን ብር የሚያደርሰው የ2006 ዓ.ም. ረቂቅ በጀት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀረበ፡፡ በጀቱን ያቀረቡት የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትር አቶ ሱፊያን አህመድ ከፓርላማው ጠንካራ ቁጥጥር ገጥሟቸዋል፡፡  ሚኒስትሩ የአገሪቱን የዓምናና የዘንድሮ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ጥሩና በአስደሳች ሁኔታ ውስጥ መሆኑን፣ እንዲሁም ያሉበትን ፈታኝ ችግሮች በቅድሚያ በመዳሰስ ያለውን በጎ ኢኮኖሚያዊ ሒደት ለማጠናከርና ችግሮችን ለመቅረፍ ለተወጠኑ ግቦች ይረዳል ያሉትን የ2006 ዓ.ም. ረቂቅ በጀት አቅርበዋል፡፡  በዚህም መሠረት የአገሪቱ የቀጣይ ዓመት በጀት 154 ቢሊዮን 903 ሚሊዮን ብር እንደሚሆን ከዚህ ውስጥም 32.53 ቢሊዮን ብር ለመደበኛ ወጪ፣ 64.32 ቢሊዮን ብር ለካፒታል ፕሮጀክቶች፣ 43.05 ቢሊዮን ብሩ ለክልል መንግሥታት ድጎማ፣ እንዲሁም ቀሪው 15 ቢሊዮን ብር ለምዕተ ዓመቱ ግቦች ማጠናከሪያ ወጪዎች መሸፈኛ እንደሚውል አብራርተዋል፡፡  የተጠቀሰው የቀጣይ ዓመት ረቂቅ በጀት ከዘንድሮው ጋር ሲነፃፀር በ12.3 በመቶ ብልጫ ያለው ሲሆን፣ ከረቂቅ በጀቱ ውስጥ ከፍተኛውን የ41.5 በመቶ ድርሻ የያዘው የፌዴራል መንግሥት የካፒታል ፕሮጀክቶች ወጪ ነው፡፡  ለካፒታል ፕሮጀክቶች የተመደበው 64.32 ቢሊዮን ብር ሲሆን፣ ቅድሚያ ትኩረት የተሰጣቸው ነባር ፕሮጀክቶች እንዲሆኑ የተወሰኑ አዳዲስ ፕሮጀክቶች ብቻ እንዲካተቱ በማድረግ፣ ከአገሪቱ የገንዘብ አቅም ጋር እንዲጣጣም መደረጉን ሚኒስትሩ አስረድተዋል፡፡  የተጠቀሰው የካፒታል ፕሮጀክቶች በጀት ከዘንድ