Posts

በሲዳማ ዞን ሸበዲኖ ወረዳ ከ5 ሺህ በላይ ጎልማሶች ተግባር ተኮር የጎልማሶች ትምህርት በመከታተል ላይ ናቸው ተባለ

ሃዋሳ ግንቦት 23/2005 በሲዳማ ዞን ሸበዲኖ ወረዳ በተግባር ተኮር የጎልማሶች ትምህርት ከ5 ሺህ በላይ ጎልማሶች ትምህርታቸውን እየተከታተሉ መሆኑን የወረዳው ትምህርት ጽህፈት ቤት አስታወቀ። የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ አዝመራ አመኑ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት በወረዳው በሚገኙ ከ35 በሚበልጡ ትምህርት ቤቶችና ጊዜያዊ የማሰተማሪያ ስፍራዎች ማንበብና መጻፍ ለማይችሉ ጎልማሶች ትምህርት እየተሰጠ ነው። በወረዳው ማንበብና መጻፍ የማይችሉ ጎልማሶችን በመለየትና ለ96 አመቻቾች የማስተማር ስነዘዴ ስልጠና በመስጠት 5 ሺህ 947 ጎልማሶች ትምህርት እየተሰጠ መሆኑን ተናግረዋል። በደረጃ አንድና ሁለት ትምህርታቸውን በመከታተል ላይ ካሉት ጎልማሶች በተጨማሪ በቀበሌ አመራሮች በልማት ቡድኖችና በአንድ ለአምስት ትስስር አማካኝነት ማንበብና መጻፍ የማይችሉ ጎልማሶች እየተለዩ መሆኑንና በአሁኑ ወቅት በወረዳው የጎልማሶች ትምህርት ሽፋን ከ56 በመቶ በላይ እንደደረሰ አቶ አዝመራ ተናግረዋል። የጎልማሶች ትምህርትን በተጠናከረ መልኩ ለማከናወን የወረዳው አስተዳደር ለአመቻቾች አስፈላጊውን ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝና የማስተማሪያ መጽሀፍት ግዥ በመፈጸም ለሁሉም ጣቢያዎች እንዲዳረስ ማድረጉን አስታውቀዋል። በተጨማሪም አምስትና ስድስት ዓመት የሆናቸው 23 ሺህ 233 ህጻናት በ250 አመቻቾች የቅድመ መደበኛ ትምህርት በትምህርት ቤትና ከትምህርት ቤት ውጪ በተዘጋጁ የማስተማሪያ ስፍራዎች እየተማሩ እንደሚገኙ ገልጸዋል። ልዩ ፍላጎት ያላቸውን አካል ጉዳተኞች በአካቶ የማስተማር ዘዴ ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ 392 መስማትና ማየት የተሳናቸውና የተለያየ የአካል ጉዳት ያለባቸው ህጻናት በሰለጠኑ መምህራን እንዲማሩ መደረጉን አቶ አዝመራ ጠቁመዋል። የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታረቀኝ

የሀዋሳ ዩኒቨርሰቲ የህብረተሰብ አገልግሎትን ለማጠናከር እየሰራ ነው ይላል

Image
አዋሳ ግንቦት 22/2005 የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የህብረተሰብ አገልግሎትን እንደ መደበኛ ፕሮግራሙ በማቀፍ የምርምር ውጤቶችን ተጠቃሚ ለማድረግ ስራውን አሰፋፍቶና አጠናክሮ መቀጠሉን የዩኒቨርስቲው ፕሬዝዳንት ገለጹ፡፡ ዩኒቨርስቲው ለስራ አጥ ወጣቶችና ሴቶች በዘመናዊ የዶሮ እርባታ ዙሪያ ያዘጋጀው ስልጠና ትናንት በሀዋሳ ከተማ ተጀምሯል፡፡ ስልጠናውን የከፈቱት የዩኒቨርሰቲው ፕሬዚደንት ዶክተር ዮሴፍ ማሞ እንደገለጹት የመማር ማስተማር ስራቸውን ከምርምር ጋር አቀናጅተው ያገኟቸውን አዳዲስና ችግር ፈቺ ውጤቶችን ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ ስድስት የቴክኖሎጂ መንደሮች ተቋቁመዋል፡፡ የህብረተሰብ አገልግሎትን እንደ መደበኛ ፕሮግራማቸው በማቀፍ በምርምር የተገኙ የግብርና፣ የጤናና ሌሎችን ውጤቶችን በተለይ ስራ አጥ ወጣቶችንና ሴቶችን ተጠቃሚ ለማድረግ የተለያዩ ስልጠናዎችንና የመስሪያ ግብአቶችን በማሟላት ድጋፍ እየሰጡ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ በቅርቡ ብቻ በደን ልማትና ችግኝ እንዲሁም በእንጉዳይ አመራረትና አጠቃቀም ላይ ከሀዋሳ ከተማና ከሲዳማ ዞን ሁላ ወረዳ ለተወጣጡ በርካታ ወጣቶችና ሴቶችን ተጠቃሚ ማድረጋቸውን አመልክተው አሁንም ለ24 ወጣቶች በዘመናዊ የዶሮ እርባታ ዙሪያ ስልጠና አዘጋጅተው እራሳቸውን ችለው በተመሳሳይ ለሌሎችም የሚበቁበት የአቅም ግንባታ ድጋፍ አያደረጉ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡ ስራ ፈጣሪ ወጣቶችን እናበረታታለን ያሉት ዶክተር ዮሴፍ ዩኒቨርስቲው አጠቃላይ የትምህርት ተቋም እንደመሆኑ ሌሎችንም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸውን የምርምር ውጤቶችን ለህብረተሰቡ በማሸጋገር ተጠቃሚ ለማድረግ ስራቸውን በሁለገብነት አስፋፍተውና አጠናክረው መቀጠላቸውን ገልጸዋል፡፡ በዩኒቨርስቲው የምርምርና ልማት ዳይሬክተር ዶክተር ተስፋዬ አበበ በበኩላቸው ህብረተሰቡ ተጠ

Cooking with traditional crops improves nutrition and boosts women's incomes

Image
Promising pulses in Ethiopia A similar healthy-eating effort is underway in Ethiopia, where about 52% of the country's rural population fails to meet minimum consumption requirements for calories. Researchers at the University of Saskatchewan and Hawassa University are studying how education can increase consumption of pulses, including chickpeas, broad beans, and lentils. They are focusing particularly on the consumption patterns of the most vulnerable: children under five, adolescent girls, and adult females. Studies found a lack of awareness among women of the nutritional value of pulses, and the need to incorporate this high-protein, high-iron crop in everyday meals. "The main staple of the Ethiopian diet is teff (a local cereal grain). People would rather eat that alone than add a little protein, like lentils. Part of our project is showing them the nutritional value of protein combinations. We are also trying to overcome the perception of pulse as 'poor man'

Assessment of drug use pattern using WHO prescribing indicators at Hawassa University teaching and referral hospital, south Ethiopia: a cross-sectional study

Image
To promote rational drug use in developing countries, it is important to assess drug use pattern using the World Health Organization (WHO) drug use indicators. The aim of this study was to assess the drug prescription patterns at the Medical Outpatient Pharmacy of Hawassa University Teaching and Referral Hospital, using some of the WHO core drug use indicators.  Methods: A descriptive, quantitative, and cross-sectional survey was conducted to determine the current prescribing practices at Hawassa University Teaching and Referral Hospital. The sample was selected using systematic random sampling. 1290 patient encounters were reviewed retrospectively for a 2-year period from September 2007 to September 2009. Data were collected from prescriptions and Prescription registration books retained in the pharmacy.Result: The average number of drugs prescribed per encounter or mean was 1.9 (SD 0.91) with a range between 1 and 4. The percentage of encounters in which an antibiotic or injection

ፋና ብሮድ ካስት ኮርፖሬት ሻሸመኔ ኤፍ ኤም 103 ነጥብ 4 በሲዳምኛ ቋንቋ የሬዲዮ ስርጭት መጀመሩንም አብስሯል፡፡

አዋሳ ግንቦት 21/2005 የግንቦት 20 የድል በዓል የሀገሪቱን ታሪክ ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገረ የብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች አኩሪ የትግል ውጤት መሆኑን የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሺፈራው ሽጉጤ ገለጹ፡፡ ፋና ብሮድ ካስት ኮርፖሬት ሻሸመኔ ኤፍ ኤም 103 ነጥብ 4 ከሲዳማ ዞን አስተዳደር ጋር በመተባበር የግንቦት 20ን በዓል ትናንት በሀዋሳ ከተማ በተለያዩ ፕሮግራሞች አክብሯል፤ በሲዳምኛ ቋንቋ የሬዲዮ ስርጭት መጀመሩንም አብስሯል፡፡ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሺፈራው ሽጉጤ በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት የዘንድሮው የግንቦት 20 በዓል ትግሉን በመምራት ለድል ያበቁት ታላቁ መሪ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን በሞት በተለዩን ማግስት የሚከበር በመሆኑ ልዩ ያደርገዋል፡፡ እሳቸውን ብናጣም የሀገራቸንን ታሪክ ወደ አዲስ ምዕራፍ በማሸጋገር ራዕያቸውንና የህዳሴ ጉዞችንን ለማሳካት ጠንካራ መሰረት በመጣል የብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች አኩሪ የትግል ውጤት እንዳለ አስረድተዋል፡፡ ሀገሪቱ ከጨለማው ዘመን በመውጣት በአሁኑ ወቅት የቡድንና የግለሰብ መብት ከመረጋገጡም በላይ በተለይ በትግል ወቅትና ከዚያም ወዲህ እንደሚዲያ የህዝብ ድምጽ በመሆን ሲያገለግል የቆየው የፋና ብሮድ ካስት ኮርፖሬት የግንቦት 20 ሌላው የድል ውጤት መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ፋና የስርጭት አድማሱን በማስፋት ተደራሽ ከሆነባቸው የሀገሪቱ አካባቢዎች በተለይም በሲዳምኛ ቋንቋ አሁን የጀመረው ፕሮግራም ቀጥሎ 17 ሚሊዮን ለሆነው የደቡብ ክልል ህዝብ በተመሳሳይ እንዲሰራ የክልሉ መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍና እገዛ እንሚያደርግ በማረጋገጥ እሰካሁን ላደረገው አስተዋጾኦ አመስግነዋል፡፡ የሲዳማ ዞን ዋና አስተዳደሪ አቶ ሚሊዮን ማቲዎስ የሲዳማ ህዝብ እንደሌላው ጭቁን ኢትዮጵያዊ ሁሉ የግንቦት 20 የድል ውጤ