አርባምንጭ ከነማ በዓመቱ ለመጀመሪያ ጊዜ በሜዳው ሽንፈትን በሲዳማ ከነማ አስተናዷል።
በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ መለስ ዋንጫ የ17ኛው ሳምንት ቀሪ ጨዋታዎች ሚያዝያ 19/2005 ሶስት ጨዋታ የተካሄዱ ሲሆን ሐዋሳ ላይ ሐዋሳ ከነማ ኢትዮጵያ ቡናን አስተናግዶ አንድ አቻ ተለያይተዋል። ውጤቱን ተከትሎ ኢትዮጵያ ቡና በ32 ነጥብ ደደቢት ተከትሎ ፕሪምየር ሊጉ በሁለተኛ ደረጃ ተቀምጧል። ሐዋሳ ከነማ በ30 ነጥብ ሶሰተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። አርባምንጭ ከነማ በዓመቱ ለመጀመሪያ ጊዜ በሜዳው ሽንፈትን በሲዳማ ከነማ አስተናዷል። በሲዳማ ቡና 1 ለ 0 በሆነ ውጤት በመሸነፉ። አዳማ ከነማ አሁንም ከወራጅ ቀጠና መውጣት ሳይችል ቀርቷል በሜዳው በመብራት ኃይል 1 ለ 0 ተሸንፏል። በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ መለስ ዋንጫ ጨዋታ ደደቢት በ36 ነጥብ እየመራ ነው ። http://www.ertagov.com/amharic/index.php/2013-03-11-06-12-23/2013-03-11-07-10-49/item/633-%E1%88%83%E1%8B%8B%E1%88%B3-%E1%8A%A8%E1%8A%90%E1%88%9B-%E1%8A%A2%E1%89%B5%E1%8B%AE%E1%8C%B5%E1%8B%AB-%E1%89%A1%E1%8A%93%E1%8A%95-%E1%8A%A0%E1%88%B5%E1%89%B0%E1%8A%93%E1%8C%8D%E1%8B%B6-%E1%8A%A0%E1%8A%95%E1%8B%B5-%E1%8A%A0%E1%89%BB-%E1%89%B0%E1%88%88%E1%8B%AB%E1%8B%A8