Posts

ባለስልጣኑ የዕቅዱን ከ20 በመቶ በላይ ብልጫ ያለው ገቢ ሰበሰበ

Image
አዋሳ ሚያዝያ 08/2005 ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከተለያዩ የገቢ ምንጮች ከዕቅዱ ከ20 በመቶ በላይ ብልጫ ያለው ግብር በማሰባሰብ የከተማውን አጠቃላይ ወጪ መሸፈን መቻሉን የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ባለስልጣን ገለጸ፡፡ በንግድ ስራ የተሰማሩ ሁሉም ድርጅቶች የሽያጭ መመዝገቢያ መሳሪያ መጠቀም እንዳለባቸው አስጠንቅቋል፡፡ የባለስልጣኑ ስራ አስኪያጅ አቶ ፍቃዱ ፍስሐ ሰሞኑን ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት ከሐምሌ 2004 ወዲህ ባሉት ዘጠኝ ወራት ከ385 ሚሊዮን ብር የሚበልጥ ገቢ ተሰባስቧል፡፡ የመደበኛና ማዘጋጃ ቤት አገልግሎትን ጨምሮ ቀጥታና ቀጥታ ካልሆነ እንዲሁም ታክስ ካልሆኑ ገቢዎች የተሰበሰበው የገቢ ግብር የዕቅዱን ከ20 በመቶ በላይና ካለፈው አመት ተመሳሳይ ጊዜ በከፍተኛ ደረጃ ብልጫ እንዳለው ገልጸዋል፡፡ ከዕቅድ በላይ ማከናወን የተቻለው በከተማ አስተዳደርና በስሩ በሚገኙ ስምንቱ ክፍለ ከተሞች አመራሩና ሰራተኛው ከሙስናና ኪራይ ሰብሳቢነት የጸዳ አሰራር እንዲከተሉ የተጠናከረ ክትትልና ቁጥጥር በመዘርጋት ለግብር ከፋዩ ህብረተሰብ የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት መሰጠርት ግልጽ፣ ፈጣንና ተጠያቂነት የሰፈነበት ስርዓት እንዲኖር በመደረጉ ነው ብለዋል፡፡ የሀዋሳ ከተማ ሰፊ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ የሚካሄድበትና ከዚህ የሚመነጨውን የገቢ ግብር አቅም አሟጦ ለመጠቀም በተደረገ ጥረት አፈጻጸሙ ከምንግዜውም የተሻለ ጥሩና አመርቂ ደረጃ ላይ መድረሱን ስራ አስኪያጁ አስረድተዋል፡፡ በዚህ ገቢ የከተማው አስተዳደር ከመንግስት ይደረግለት የነበረውን ድጎማ በማስቀረት ለካፒታል ፕሮጀክቶችና ሰራተኛ ደመወዝና ስራ ማስኬጃን ጨምሮ የከተማውን አጠቃላይ ወጪ በራሱ ለመሸፈን መቻሉን ገልጸዋል፡፡ የከተማው አሰተዳደር የገቢ ግብር በየአመቱ እየጨመረ ባለፈው በጀት አመት 2

በሴቶች ፕሪምየር ሊግ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ሲዳማ ቡና ድል ቀናቸው

በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የሴቶች ውድድር የምደቡ የመጨረሻ ጨዋታ ሚያዝያ 7/2005 በአዳማ አበበ ቢቂላ ስታድየም ተካሂዷል፡፡ በጨዋታው ሽታየ ሲሳይ 4 ጎል አስመዝግባለች ዘንድሮ በፕሪምየር ሊጉ ያገባችው ጎል 25 በማድረስ መሪነቷን አጠናክራ ቀጥላለች፡፡ አዳማ ከነማ መከላከያን 2 ለ 1 ቢያሸነፍም በግብ ተበልጦ ግማሽ ፍፃሜወን ሳይቀላቀል ቀርቷል፡፡ ከምድቡ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ሲዳማ ቡና ኃላፊ ሆነዋል፡፡ ኃላፊው ክለብ ቀድሞ የተለየበት የምድብ 2 ጨዋታ ደግሞ 8 ሰዓት ላይ እና 12 ሰዓት ላይ ተካሂዷል፡፡ መውደቃቸውን ያረጋገጡት የመድህንና የድሬዳዋ ጨዋታ በመድህን 4 ለ 3 አሸናፊነት ተጠናቋል፡፡ በደደቢት እና ሃዋሳ ከነማ መካከል የተካሄደው ጨዋታ ደግሞ ደደቢት 1 ለ 0 በሆነ ጠባብ ልዩነት አሸንፏል፡፡ ደደቢት እና ሃዋሳ ከነማ ግማሽ ፍፃሜውን ተቀላቅለዋል፡፡ በግማሽ ፍፃሜው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከሃዋሳ ከነማ፣ ደደቢት ከሲዳማ ቡና ይጫወታሉ፡፡

የሲዳማ አርነት ንቅናቄ ራሱን ከምርጫ አገለለ

‹ከ200 በላይ እጩዎቻችንና ታዛቢዎቻችን ታስረው በምርጫ መሳተፍ ይከብደናል - ዶ/ር አየለ አሊቶ ‹‹ቀልዱን ብቻቸውን ይቀልዱ፤ ምርጫ የለም ንጥቂያ ነው›› - ኢንጂነር ሃይሉ ሻወል ‹‹የሲዳማ ዞን ህዝብ ወደ ምርጫው እንድንገባ ገፋፍቶኛል›› በሚል በምርጫው ላለመሳተፍ ከወሰኑት 33ት ፓርቲዎች በመነጠል የምርጫ ምልክት ወስዶ የነበረው የሲዳማ አርነት ንቅናቄ ፓርቲ ራሱን ከምርጫው ማግለሉን ይፋ አደረገ፡፡ ፓርቲው ከ200 በላይ እጩዎቼና ታዛቢዎቼ ታስረውብኛል በሚል ነው ነገ ከሚጀመረው የአዲስ አበባና የአካባቢ ምርጫ ራሱን ያገለለው፡፡ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳውን በመቃወም ፒቲሽን ከፈረሙ 33 ፓርቲዎች መካከል አንዱ የነበረውና በኋላም ‹‹የሲዳማ ዞን ህዝብ ወደ ምርጫው እንድንገባ ገፋፍቶናል›› በሚል አውራ ዶሮ የምርጫ ምልክት ይዞ ወደ ምርጫ መግባቱን ያስታወቀው የሲዳማ አርነት ንቅናቄ ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ ዶ/ር አየለ አሊቶ ለአዲስ አድማስ እንደገለፁት “የሲዳማ ህዝብ ጥያቄ የክልል ጥያቄ ነው፣ ህዝቡ በምርጫው ተሳትፎ በካርዱ መብቱን ሊያስከብር ስለሚፈልግ የፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ ወደ ምርጫው እንዲገባ በመወሰኑ፣ ከአንድ ሺህ ስድስት መቶ በላይ እጩዎችን ለከተማ፣ ለዞንና፣ ለወረዳ አቅርቦ ነበር፡፡ ሆኖም ከ200 በላይ ዕጩዎቻችንና ታዛቢዎቻችን ለእስር በተዳረጉበትና ቅስቀሳ ባላደረግንበት ሁኔታ ወደ ምርጫ መግባት ፋይዳ የለውም፡፡ በእስርና በክልከላ ህዝቡ እየተረረ ነው፡፡ “በደም ያገኘነውን፤ “በደም ብቻ ነው የምንለቀው” ብለው እየቀሰቀሱብን ስለሆነ ራሳችንን ከምርጫ ማግለላችን ተገቢ ነው” ብለዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ሳይሻሻሉና በምርጫው እንደማይሳተፉ ቀደም ብለው ያስታወቁት 33 ፓርቲዎች ባለፈው እሁድ በሰማያዊ ፓርቲ፣ በመድረክ፣ በመኢአድና በ

መለስ ሀዋሳን ክልል ለማድረግ ቃል ገብተው ነበር

Image
መለስ ሀዋሳን ክልል ለማድረግ ቃል ገብተው ነበር የሲዳማ አገር ሽማግሌዎች አቶ መለስ እድሜያቸው አጭር እንደሚሆንና እንደሚቀሰፉ ነግረዋቸው እንደነበር ተሰማ። በክልሉ የአገር ሽማግሌ ከሚባሉት መካከል አንዱን በማነጋገር በተለይ ለጎልጉል የተላከው መረጃ እንደጠቀሰው መለስ እድሜያቸው ሊያጥርና በድንገት ሊቀሰፉ የሚችሉት የሲዳማን ባህላዊ ልብስ ለብሰው ከዋሹ ነበር። እንደመረጃው መለስ በ1997 ዓ ም ምርጫ ውጥረት ውስጥ በነበሩበት ወቅት አራት ተከታታይ ቀናት ሃዋሳ የብሄር ብሄረሰቦች አዳራሽ ውስጥ የብሄረሰቡን ተወላጆች ሰብስበው አነጋግረው ነበር። “አዲስ አበባ ያለው ድንኳናችን ፈርሷል። እዚህም ከፈረሰ በቃን ማለት ነው” በማለት የአገር ሽማግሌዎችን በተማጸኑበት ንግግራቸው መለስ አስቀድሞ ተቃውሞ ገጥሟቸው ነበር። ስብሰባው አዳራሽ ውስጥ ሙሉ ልብስ ለብሰው መድረክ ላይ ተቀምጠው የነበሩትን መለስ “ማን እዛ ላይ አወጣህ? አውርደንሃል” በማለት ሽማግሌዎች ሲናገሩ በወቅቱ የጸጥታ ሃይሎችና የአቶ መለስ ጠባቂዎች ተደናግረው ነበር። ሽማግሌዎቹ አቶ መለስን ከመድረክ አውርደው “አስቀድመህ ያገራችንን የባህል ልብስ ለብሰህ ነው መድረክ ላይ የምትወጣው” በማለት ከመድረክ አውርደው ጓዳ በማስገባት “ሴማ” የሚባለውን የባህል ቡሉኮ አለበሱዋቸው። “ይህንን የሚለብስ እውነት የሚናገር ብቻ ነው” በማለት አቶ መለስ መዋሸት እንደማይገባቸው ሽማግሌዎቹ አሳስበው እንደነበር የጠቆመው መረጃ፣ “ይህንን የሚለብስ መሪ የሆነ፣ እውነት የሚናገር ብቻ ነው። የሚዋሽ ይሞታል። እድሜው ያጥራል። ይቀሰፋል” በማለት በሲዳምኛ ደጋግመው መናገራቸውንና አቶ መለስም የተባሉትን ለማድረግ ተስማምተው እንደነበር አመልክቷል። በዚሁ መሰረት አቶ መለስ በ1997 ምርጫ ተከትሎ ካጋጠማቸው ቀው

ኑሮ እየተባባሰ ነው! መፍትሔውስ?

Image
ኑሮ እየከበደ ነው፡፡ ገቢና ወጪ አልጣጣም እያለ ነው፡፡ ኑሮ እየከበደና እየተወደደ እየመጣ ለመሆኑ ልዩ ጥናትና ምርምር አያስፈልገውም፡፡ ግልጽና ግልጽ ሆኖ በየቀኑ በአደባባይ ኅብረተሰብን እየኮረኮመ ያለ ነውና፡፡ ምን እየኮረኮመ እንዲያውም እየደበደበና እየቀጠቀጠ እንጂ፡፡  ስለቅንጦት ዕቃ አይደለም እያወራን ያለነው፡፡ እጅግ በጣም መሠረታዊና አስፈላጊ ስለሆኑ ዕቃዎችና ሸቀጦች እንጂ፡፡ ጤፍ፣ ስንዴ፣ በቆሎ፣ ስኳር፣ ልብስ፣ ትራንስፖርት፣ የጽሕፈት መሣሪያ፣ ወዘተ፡፡  የመንግሥት ሠራተኞችም ሆኑ የግል ድርጅት ሠራተኞች የሚያገኙት ደመወዝና ገበያው እየጠየቀው ያለው የገንዘብ መጠን በእጅጉ እየተራራቀ ነው፡፡ በቅጡ መመገብ፣ መልበስ፣ መጓጓዝ፣ መማርና መኖር አስቸጋሪ እየሆነ ነው፡፡ ኑሮ እየከበደ ነው፡፡  ይህ ችግር አስቸኳይ መፍትሔ ያስፈልገዋል፡፡  ከመፍትሔዎቹ አንዱ መነጋገርና መመካከር ነው፡፡ መንግሥት ወደ ሕዝብ ቀረብ ብሎ ስለአጠቃላዩ የኑሮ ሁኔታ መነጋገር አለበት፡፡ የሕዝቡን ሁኔታና ስሜት በትክክል መገንዘብ አለበት፡፡ ኑሮ እንደተወደደ መንግሥት አያውቅም ማለት አይቻልም፡፡ ነገር ግን በሪፖርት በተዋረድ ማግኘትና በቀጥታ ከሕዝብ ጋር ተገናኝቶ ችግሩን ማወቅ ከፍተኛ ልዩነት አለው፡፡  እያነሳን ያለነው ተራ የዋጋ ጭማሪን አይደለም፡፡ የቢዝነስ መቀዛቀዝም እየተስተዋለ ነው፡፡ የባንክ ብድር ማግኘት ዕድል ቁልፍልፍ ሲል፣ ኤልሲ የመክፈት ዕድል እየጠበበ ሲመጣ የሥራ ዕድልንም ያጠባል፡፡ እንቅስቃሴን በመቀነስ ገቢና ክፍያም እንዲቀንስ ያደርጋል፡፡ በተጨባጭም አድርጓል፡፡  ስለሆነም ለኑሮ ክብደቱ መፍትሔ ለማግኘት መንግሥት በኢኮኖሚውና በቢዝነስ እንቅስቃሴው ላይ ምን ዕርምጃ ልውሰድ ብሎ ማሰብ አለበት፡፡ መንግሥት ራሱ