Posts

የሲዳማ አርነት ንቅናቄ ራሱን ከምርጫ አገለለ

‹ከ200 በላይ እጩዎቻችንና ታዛቢዎቻችን ታስረው በምርጫ መሳተፍ ይከብደናል - ዶ/ር አየለ አሊቶ ‹‹ቀልዱን ብቻቸውን ይቀልዱ፤ ምርጫ የለም ንጥቂያ ነው›› - ኢንጂነር ሃይሉ ሻወል ‹‹የሲዳማ ዞን ህዝብ ወደ ምርጫው እንድንገባ ገፋፍቶኛል›› በሚል በምርጫው ላለመሳተፍ ከወሰኑት 33ት ፓርቲዎች በመነጠል የምርጫ ምልክት ወስዶ የነበረው የሲዳማ አርነት ንቅናቄ ፓርቲ ራሱን ከምርጫው ማግለሉን ይፋ አደረገ፡፡ ፓርቲው ከ200 በላይ እጩዎቼና ታዛቢዎቼ ታስረውብኛል በሚል ነው ነገ ከሚጀመረው የአዲስ አበባና የአካባቢ ምርጫ ራሱን ያገለለው፡፡ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳውን በመቃወም ፒቲሽን ከፈረሙ 33 ፓርቲዎች መካከል አንዱ የነበረውና በኋላም ‹‹የሲዳማ ዞን ህዝብ ወደ ምርጫው እንድንገባ ገፋፍቶናል›› በሚል አውራ ዶሮ የምርጫ ምልክት ይዞ ወደ ምርጫ መግባቱን ያስታወቀው የሲዳማ አርነት ንቅናቄ ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ ዶ/ር አየለ አሊቶ ለአዲስ አድማስ እንደገለፁት “የሲዳማ ህዝብ ጥያቄ የክልል ጥያቄ ነው፣ ህዝቡ በምርጫው ተሳትፎ በካርዱ መብቱን ሊያስከብር ስለሚፈልግ የፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ ወደ ምርጫው እንዲገባ በመወሰኑ፣ ከአንድ ሺህ ስድስት መቶ በላይ እጩዎችን ለከተማ፣ ለዞንና፣ ለወረዳ አቅርቦ ነበር፡፡ ሆኖም ከ200 በላይ ዕጩዎቻችንና ታዛቢዎቻችን ለእስር በተዳረጉበትና ቅስቀሳ ባላደረግንበት ሁኔታ ወደ ምርጫ መግባት ፋይዳ የለውም፡፡ በእስርና በክልከላ ህዝቡ እየተረረ ነው፡፡ “በደም ያገኘነውን፤ “በደም ብቻ ነው የምንለቀው” ብለው እየቀሰቀሱብን ስለሆነ ራሳችንን ከምርጫ ማግለላችን ተገቢ ነው” ብለዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ሳይሻሻሉና በምርጫው እንደማይሳተፉ ቀደም ብለው ያስታወቁት 33 ፓርቲዎች ባለፈው እሁድ በሰማያዊ ፓርቲ፣ በመድረክ፣ በመኢአድና በ

መለስ ሀዋሳን ክልል ለማድረግ ቃል ገብተው ነበር

Image
መለስ ሀዋሳን ክልል ለማድረግ ቃል ገብተው ነበር የሲዳማ አገር ሽማግሌዎች አቶ መለስ እድሜያቸው አጭር እንደሚሆንና እንደሚቀሰፉ ነግረዋቸው እንደነበር ተሰማ። በክልሉ የአገር ሽማግሌ ከሚባሉት መካከል አንዱን በማነጋገር በተለይ ለጎልጉል የተላከው መረጃ እንደጠቀሰው መለስ እድሜያቸው ሊያጥርና በድንገት ሊቀሰፉ የሚችሉት የሲዳማን ባህላዊ ልብስ ለብሰው ከዋሹ ነበር። እንደመረጃው መለስ በ1997 ዓ ም ምርጫ ውጥረት ውስጥ በነበሩበት ወቅት አራት ተከታታይ ቀናት ሃዋሳ የብሄር ብሄረሰቦች አዳራሽ ውስጥ የብሄረሰቡን ተወላጆች ሰብስበው አነጋግረው ነበር። “አዲስ አበባ ያለው ድንኳናችን ፈርሷል። እዚህም ከፈረሰ በቃን ማለት ነው” በማለት የአገር ሽማግሌዎችን በተማጸኑበት ንግግራቸው መለስ አስቀድሞ ተቃውሞ ገጥሟቸው ነበር። ስብሰባው አዳራሽ ውስጥ ሙሉ ልብስ ለብሰው መድረክ ላይ ተቀምጠው የነበሩትን መለስ “ማን እዛ ላይ አወጣህ? አውርደንሃል” በማለት ሽማግሌዎች ሲናገሩ በወቅቱ የጸጥታ ሃይሎችና የአቶ መለስ ጠባቂዎች ተደናግረው ነበር። ሽማግሌዎቹ አቶ መለስን ከመድረክ አውርደው “አስቀድመህ ያገራችንን የባህል ልብስ ለብሰህ ነው መድረክ ላይ የምትወጣው” በማለት ከመድረክ አውርደው ጓዳ በማስገባት “ሴማ” የሚባለውን የባህል ቡሉኮ አለበሱዋቸው። “ይህንን የሚለብስ እውነት የሚናገር ብቻ ነው” በማለት አቶ መለስ መዋሸት እንደማይገባቸው ሽማግሌዎቹ አሳስበው እንደነበር የጠቆመው መረጃ፣ “ይህንን የሚለብስ መሪ የሆነ፣ እውነት የሚናገር ብቻ ነው። የሚዋሽ ይሞታል። እድሜው ያጥራል። ይቀሰፋል” በማለት በሲዳምኛ ደጋግመው መናገራቸውንና አቶ መለስም የተባሉትን ለማድረግ ተስማምተው እንደነበር አመልክቷል። በዚሁ መሰረት አቶ መለስ በ1997 ምርጫ ተከትሎ ካጋጠማቸው ቀው

ኑሮ እየተባባሰ ነው! መፍትሔውስ?

Image
ኑሮ እየከበደ ነው፡፡ ገቢና ወጪ አልጣጣም እያለ ነው፡፡ ኑሮ እየከበደና እየተወደደ እየመጣ ለመሆኑ ልዩ ጥናትና ምርምር አያስፈልገውም፡፡ ግልጽና ግልጽ ሆኖ በየቀኑ በአደባባይ ኅብረተሰብን እየኮረኮመ ያለ ነውና፡፡ ምን እየኮረኮመ እንዲያውም እየደበደበና እየቀጠቀጠ እንጂ፡፡  ስለቅንጦት ዕቃ አይደለም እያወራን ያለነው፡፡ እጅግ በጣም መሠረታዊና አስፈላጊ ስለሆኑ ዕቃዎችና ሸቀጦች እንጂ፡፡ ጤፍ፣ ስንዴ፣ በቆሎ፣ ስኳር፣ ልብስ፣ ትራንስፖርት፣ የጽሕፈት መሣሪያ፣ ወዘተ፡፡  የመንግሥት ሠራተኞችም ሆኑ የግል ድርጅት ሠራተኞች የሚያገኙት ደመወዝና ገበያው እየጠየቀው ያለው የገንዘብ መጠን በእጅጉ እየተራራቀ ነው፡፡ በቅጡ መመገብ፣ መልበስ፣ መጓጓዝ፣ መማርና መኖር አስቸጋሪ እየሆነ ነው፡፡ ኑሮ እየከበደ ነው፡፡  ይህ ችግር አስቸኳይ መፍትሔ ያስፈልገዋል፡፡  ከመፍትሔዎቹ አንዱ መነጋገርና መመካከር ነው፡፡ መንግሥት ወደ ሕዝብ ቀረብ ብሎ ስለአጠቃላዩ የኑሮ ሁኔታ መነጋገር አለበት፡፡ የሕዝቡን ሁኔታና ስሜት በትክክል መገንዘብ አለበት፡፡ ኑሮ እንደተወደደ መንግሥት አያውቅም ማለት አይቻልም፡፡ ነገር ግን በሪፖርት በተዋረድ ማግኘትና በቀጥታ ከሕዝብ ጋር ተገናኝቶ ችግሩን ማወቅ ከፍተኛ ልዩነት አለው፡፡  እያነሳን ያለነው ተራ የዋጋ ጭማሪን አይደለም፡፡ የቢዝነስ መቀዛቀዝም እየተስተዋለ ነው፡፡ የባንክ ብድር ማግኘት ዕድል ቁልፍልፍ ሲል፣ ኤልሲ የመክፈት ዕድል እየጠበበ ሲመጣ የሥራ ዕድልንም ያጠባል፡፡ እንቅስቃሴን በመቀነስ ገቢና ክፍያም እንዲቀንስ ያደርጋል፡፡ በተጨባጭም አድርጓል፡፡  ስለሆነም ለኑሮ ክብደቱ መፍትሔ ለማግኘት መንግሥት በኢኮኖሚውና በቢዝነስ እንቅስቃሴው ላይ ምን ዕርምጃ ልውሰድ ብሎ ማሰብ አለበት፡፡ መንግሥት ራሱ

THE SIDAMA LIBERATION MOVEMENT WITHDRAWS FROM THE ETHIOPIAN LOCAL ELECTIONS AMID WIDESPREAD RIGHTS ABUSES

Image
ፎቶ ኣገሬሰላም ኣሮሬሳ(ፌስቡክ) Press Release United Sidama Parties for Freedom and Justice 14 April 2013 The 14 April 2013 local government elections in Ethiopia have been marred by widespread abuses of the representatives and supporters of the Sidama Liberation Movement (SLM), which remains the main opposition political movement in the Sidama region. The SLM accuses the regional and Sidama EPRDF cadres of continued intimidation, harassment and persecution of its representatives and supporters during the period leading up to the elections.  The SLM members in all 19 districts of the Sidama administration who were nominated to contest in the stated elections have often been arrested and imprisoned for prolonged period of time to intimidate them and deter them from contesting the elections. The elected SLM representatives were barred from freely campaigning in the Sidama region. To the astonishment of the Sidama people and in an outright contempt to any democratic principles,  Duka’l

በሲዳማ ብሔር ላይ እየደረሱ ያሉ ጭካኔ የተሞላባቸው አረሜናዊና ኢ-ሰብአዊ ድርጊቶች እንዲቆሙ የአለም-አቀፉ ማህበረሰብ ድጋፊ እንዲያደግርልን እንማፀናለን!!

Image
ከማህበራዊ መረብ ላይ የተገኝ ጽሁፍ በ  Sidaamaho Maganu No በሲዳማ ብሔር ላይ እየደረሱ ያሉ ጭካኔ የተሞላባቸው አረሜናዊና ኢ-ሰብአዊ ድርጊቶች እንዲቆሙ የአለም-አቀፉ ማህበረሰብ ድጋፊ እንዲያደግርልን እንማፀናለን!! በኢትዮጲያ ውስጥ የሕወኃት/ኢህአደግ ግፈኛና ቅኝ አገዛዝ ከተጀመረበት ከወረሐ ግንቦት 1983ዓ.ም እስከ ሚያዚያ 2005 ዓ.ም ድረስ ምርጫ ሳይሆን በየአምሰት አመት አንዴ ብዛት ያለው ወረቀት በአዲስ አበባ በሕወኃት ንግድ ድርጅቶች ታትሞ በካርቶኖች ታሽጎ በየክልሎች ከተከፋፈለ በኋላ የእለት ጉርስ ተሰፈሮላቸው ካድሬዎች ባቀረቡትና ማታ ላይ ይዘው በሚሸሹት ቦርሳ ውስጥ የሚከቱ ተቀጥሬው ምርጫ ቦርድ ወደሚባለው እሳት የላሱ የታጠቅ ካድሬዎች በየደረጃው በተሰገሰጉ መንጋ እየተላከ አራት ዙሪ ምርጫ መሳይ የእቃ እቃ ጨዋታ ሲጫወቱ አሳለፉ፡፡  በሦስተኛው ዙሪ ታፍኖ በብሶት ውስጥ ሆዱ እያረሬ የኖረው የኢትዮጲያ ሕዝብ ከዳር እስከ ዳር ተነቃንቆ አይቀጡ ቅጣት ሲቀጣው እራሱን ስዩሜ-እግዚአብሔር አድርጎ ሲንቀባረር የከረመው ዘረኛና ከፋፋይ የሕወኃት ባንዳ ቡድን ከረፈደ ባነነና በባዶ ጥላቻ በመነሳሳት በአዲስ አበባና በክልሎች ከትምህርት ቤት የሚመለሱ ጨቅላ ህጻናትን ጨምሮ ቁጥር ስፊር የሌላቸውን ህዝብ ህይወት አልባ አደረገ፡፡ "ጅራፍ እራሱ ገርፎ እራሱ ይጮሃል " እንዲሉ ሕዝብ የመረጣቸውን ተወካዮቹንና የህዝብ አይንና ጆሮ የሆኑ ጋዜጠኞችን ህገ-ወጥ በሆነ አካሄድ አስሮ አሰቃያቸው፤ ከሚወዱት ቤተሰባቸውና ህዝባቸው ለያቸው፤ የብዙዎቹን ቤተሰብ ለጎዳና ሕይወት ዳረጋቸው፤ የድራማ ድርሰት ተጻፈና የሀገር ሽማሌዎች የሚባሉ ገጸ-ባህሪያት በፕሮፌሰር ይስሃቅ ዋና ገጸ-ባህርነት ድራማው ለህዝብ ታዬና ብዙዎቹ አናዶ፤ ብዙዎቹ