የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ መለስ ዋንጫ ሀዋሳ ከነማ መሪነቱን ያዘ
ሚያዝያ 3/2005 በአዲስ አባባ ስታዲየም ከኢትዮጵያ መድህን ያካሄደው ሐዋሳ ከነማ መሪነቱን ከደደቢት ተረክቧል። በሌላ ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከአዳማ ከነማ ባካሄዱት ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 3 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል። ፕሪምየር ሊጉን ሐዋሳ ከነማ በ28 ነጥብ እየመራ ሲሆን አንድ ቀሪ ጨዋታ እያለው በ27 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃ የሚገኘው ደደቢት ሚያዝያ 4/2005 ዓ.ም በ12 ሰዓት ከሲዳማ ቡና ወሳኝ ጨዋታ ያደርጋል። በተመሳሳይ ዜና የደደቢት አሰልጣኝ አብርሃም ተክለሃይማኖት ከኃላፊነታቸው ለቀዋል።