Posts

የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ መለስ ዋንጫ ሀዋሳ ከነማ መሪነቱን ያዘ

ሚያዝያ 3/2005 በአዲስ አባባ ስታዲየም ከኢትዮጵያ መድህን ያካሄደው ሐዋሳ ከነማ መሪነቱን ከደደቢት ተረክቧል። በሌላ ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከአዳማ ከነማ ባካሄዱት ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 3 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል። ፕሪምየር ሊጉን ሐዋሳ ከነማ  በ28 ነጥብ እየመራ ሲሆን አንድ ቀሪ ጨዋታ እያለው በ27 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃ የሚገኘው ደደቢት ሚያዝያ 4/2005 ዓ.ም በ12 ሰዓት ከሲዳማ ቡና ወሳኝ ጨዋታ ያደርጋል። በተመሳሳይ ዜና የደደቢት አሰልጣኝ አብርሃም ተክለሃይማኖት ከኃላፊነታቸው ለቀዋል።

19 ቁጥርና የሐዋሳው ልጅ

Image
አዳነ ግርማ ከምርጥ አስር አፍሪካዊ ተጫዋቾች ውስጥ በመካተት የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ተጫዋች ነው፤   ጆሴፍ ፔፕ ጋርዲዮላ የባርሴሎናን ክለብ ማሠልጠን እንደጀመረ የመጀመሪያ ስራው ያደረገው የክለቡን ነባር ተጫዋቾች በማሰናበት በምትካቸው በዝነኛው የክለቡ ማሠልጠኛ ማዕከል ( ላሜሲያ ) ያደጉ ተጫዋቾችን በዘመቻ መልክ ማሰባሰብን ነበር። ከነዚህ ተመላሽ ካታሎናውያን መካከል በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በፈረንሳዊው አርሴን ቬንገር ለሚሰለጥነው አርሴናል አምበልና የመሃል ሜዳ አንቀሳቃሽ የነበረው ሴስክ ፋብሪጋስ ቀዳሚው ነበር። አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ ተጫዋቹን ከሰሜን ለንደኑ ክለብ ለማስኮብለል ከተጠቀመባቸው አማራጮች መካከል አንዱ ራሱ በባርሴሎናና በስፔን ብሔራዊ ቡድን ሲጫወት ይለብሰው የነበረውን የማሊያ ቁጥር ( አራት ቁጥር ) እንደሚሰጠው ቃል መግባት ይገኝበታል። ሜክሲኮአዊው ራፋኤል ማርኬዝ ከባርሴሎና ጋር የነበረውን ኮንትራት አጠናቆ ወደ አሜሪካው ሜጄር ሶከር ሊግ ማምራቱን ተከትሎ ተሰቅሎ የቆየውን ማሊያ አውርዶ ለወጣቱ ጨዋታ አቀጣጣይ ሲሰጠው ተጫዋቹም በተደረገለት እንክብካቤ ከፍተኛ ደስታ ይሰማው ጀመር። ምክንያቱ ደግሞ በአርሴናል ይለብሰው የነበረውን አራት ቁጥር ማሊያ በአዲሱ ክለቡ ባርሴሎናም ለብሶ መጫወት ፍላጎቱ ስለነበር ነው። ከላይ የገለጽኩት ሐሳብ ለዕለቱ መጣጥፌ መግቢያ ይሆን ዘንድ የተጠቀምኩት ሐሳብ ነው። የዛሬው ጽሑፌ ማጠንጠኛ የሆነው ተጫዋች ተወልዶ ያደገው በደቡብ ክልል ዋና ከተማ ውቢቷ ሐዋሳ ሲሆን የመጀመሪያ ክለቡም የከተማዋ ተወካይ የሆነው ሐዋሳ ከነማ እግር ኳስ ክለብ ነው። በዚሁ ክለብ ከተከላካይነት እስከ አማካይ መስመር ባሉት ቦታዎች ላይ የተሰጡትን ሚናዎች በሚገባ እየተወጣ ማደጉ ለአሁኑ ሁ

የሀዋሳ ከተማ የባሀል ማዕከል ግንባታ የመጀመሪያው ምዕራፍ በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል

Image
ሀዋሳ ሚያዚያ 2/2005 በሀዋሳ ከተማ 70 ሚሊዮን ብር በሚጠጋ ወጪ የሚካሄደው የባህል ማዕከል ግንባታ የመጀመሪያው ምዕራፍ በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ የከተማ ማዘጋጃ ቤት ገለጸ፡፡ በማዘጋጃ ቤቱ የመሰረተ ልማት ማስፋፊያ ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ መብራቴ መለሰ ትናንት ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት በሀዋሳ መስቀል አደባባይ በ2003 ሀምሌ የተጀመረው የማዕከሉ ግንባታ ሁለገብ አዳራሽ፣ አንፊ ቲያትር ቤትና ሙዚየም አካቶ የሚይዝ ነው፡፡ በተለይ ቲያትር ቤቱን ይዞ 1500 መቀመጫ የሚኖረውና ለሁለገብ የስብሰባ አገልገሎት የሚውለው አዳራሽ የመጀመሪያው ምዕራፍ ግንባታ ሲሆን በእስካሁን እንቅስቃሴ ከአጠቃላይ ስራው 80 በመቶው መጠናቀቁን ተናግረዋል፡፡ የቀሩት ጥቃቅን ስራዎችና የውሰጥ ድርጅት ማሟላት እስከ መጪው ሰኔ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንደሚበቃ አመልከተው ሁለተኛው ምዕራፍ የሆነውና በ30 ሚሊዮን ብር ወጪ የሚካሄደው የሙዚየሙን ግንባታ ለመጀመር ዝግጅት መጠናቀቁንና ስራው እሰከ መጪው አመት መግቢያ ድረስ እንደሚጠናቀቅ አስረድተዋል፡፡ የባህል ማዕከሉ መገንባት ሀዋሳ የቱሪዝም ከተማ እንደመሆኗ በኢንተርናሽናልና በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚካሄዱ ስብሰባዎችን በብቃት በማስተናገድ የቱሪዝም ኮንፍራስ ከተማናቷን ከማሳደግ በሻገር የክልሉ ባህላዊ ቅርሶችና እሴቶችን አሰባስቦ ፣ ጠብቆና ተንከባክቦ ለማቆየት ከፍተኛ አስተዋጾኦ እንደሚኖረው አስተባባሪው ገልጸዋል፡፡ ማዕከሉ የቢዝነስና ማንጅመንት ፕላን ይኖሩታል ብለዋል፡፡  Source: http://www.ena.gov.et/Story.aspx?ID=6846&K=1

የደቡብ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን ኪሳራው እንዲከፈለው ጠየቀ

Image
አለመግባባት የሚያጦዘው የኢትዮጵያ እግር ኳስ -    የደቡብ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን ኪሳራው እንዲከፈለው ጠየቀ -    ‹‹ነገሩ ግልፅ እንዲሆንልኝ መነጋገር እፈልጋለሁ›› እግር ኳስ ፌዴሬሽን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ከእንቅልፉ ተነሳ ሲባል መልሶ እያንቀላፋ፣ ተነቃቃ ሲባል እየደከመው ከረጅም ዓመታት በኋላ የለውጥ ጭላንጭል የታየበት ቢመስልም፣ ጊዜና ወቅት እየጠበቀ በሚፈጠር አለመግባባት እንደገና ወደ ጡዘት የሚያስገባ ምልክት እየተስተዋለበት ነው፡፡ የእግር ኳሱን ፋና የሚያጨልም ሰው (ጓዳ) ሠራሽ ቢሮክራሲ የበላይነት፣ የሥልጣን ማሳያ ሽኩቻ፣ ያለመግባባት ፍጥጫ ቀዝቃዛ ውኃ ሲቸልስበት ኖሯል፡፡ እነዚህ ጉዳዮች አሁንም እግር ኳሱ ቀና ቀና ማለት በጀመረበት ቅጽበት እንኳ የተቀየሩና የቀሩ አልመስል እያሉ ጉዞውን አስቸጋሪ እያደረጉበት ይገኛል፡፡ ከሰሞኑ የሚታየው ውዝግብም ኳሱ ከተለያዩ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ የውድድር መድረኮች ለዓመታት ተገልሎ የቆየበት ምክንየት ምን ነበር? የነበረውን ችግር ከሥር መሠረቱ ለመፍታት የተደረገው ጥረት ምንድነው? ዛሬስ ከዓመታት መገለል በኋላ ምን ዓይነት ለውጥና ዕድገት አምጥቶ ነው መድረኩን የተቀላቀለው? በሚሉትና ሌሎችም ተመሳሳይ የችግር አፈታት ሒደቶች ላይ የተመሠረተ ሳይሆን፣ የሥልጣን ድርሻና የበላይነት ላይ የተመሠረተ ሆኖ መታየቱ መንግሥትንም የሚያስተቸው መሆኑ አልቀረም፡፡ መንግሥት ‹‹ዘርፉ ከፖለቲካው ጨዋታ ውጭ እስከሆነ ድረስ ምንም ቢፈጠር ዝምታን ይመርጣል›› የሚለው የብዙዎች ትችት ወደ ኳሱም አካባቢ እየተዛመተ ስለመሆኑ እየተነገረ ይገኛል፡፡ እነዚሁ አካላት መንግሥት በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ እያከናወነ ካለው ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ክንውኖች ስፖርቱን

በሃዋሳ ከተማ ሲካሄድ የቆየው የባህል ፌስቲቫልና የኢንዱስትሪ ሳምንት ተጠናቀቀ

Image
ተፈጥሮአዊ መስህቦችና ባህላዊ ቅርሶች ለሀገሪቱና ለዓለም ህዝቦች በማሳወቅ ለገፅታ ግንባታው ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዲኖራቸው  እየሰራ መሆኑን የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ በሃዋሳ ከተማ ለአምስት ቀናት   ሲካሄድ የቆየው የባህል ፌስቲቫልና የኢንዱስትሪ ሳምንት መጋቢት 30/2005 ተጠናቋል፡፡ በባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር የባህል ኢንዱስትሪ የልማትና የትብብር ዳይሬክቶሬት ጊዜያዊ አስተባባሪ አቶ ተስፋዮ ኦታንጎ በፌስትቫሉ መዝጊያ ላይ እንደገለጹት የብዝሃ ባህል፣ የቅርስና የተፈጥሮ መስህቦችን ቀጣይነት ባለው መልኩ በመጠበቅና በማልማት የህዝቡን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማጎልበት እየተሰራ ነው፡፡ የሀገሪቱን ዕምቅ የባህል፣ የተፈጥሮ ቅርሶችና ዕሴቶችን በተገቢው መንገድ በማልማት ለሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ዕድገት ጉልህ ድርሻ እንዲኖራቸው ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ አቶ ተስፋዬ ለሁለተኛ ጊዜ ከመጋብት 25   እስከ መጋቢት 30 ቀን 2005 ዓ.ም በሃዋሳ ከተማ በተካሄደው የባህል ፌትቫልና የኢንዱስትሪ ሳምንት ሁለቱ የከተማ አስተዳደሮችን ጨምሮ ከዘጠኙም ክልሎች የመጡ የባህል ቡድኖች የየአከባቢያቸውን ባህልና እሴቶችን በአደባባይ በማሳየት ባህል ለአንድነት፣ ለሰላም፣ ለልማት፣ ለዕውቀትና ለመልካም ገፅታ ግንባታ ያለውን ጠቀሜታ አጉልተው ያሳዩበት መድረክ ነበር ብለዋል፡፡ ከትግራይ፣ ከኦሮሚያ፣ ከአማራና ከአዲስ አባባ የመጡ አንዳንድ የባህል ልዑካን ቡድን አባላት በሰጡት አስተያየት ፌስትቫሉ የእርስ በርስ ግንኙነትን የሚያጠናክር፣ ለዕውቀት ሽግግር ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያበረክት ከመሆኑም ባሻገር ክልሎች የየራሳቸውን ዕምቅ የባህል ሃብቶቻቸውን ለማስተዋወቅና መልካም ተሞክሮዎችን ለመለዋወጥ እንደረዳቸው ተ