Posts

የደቡብ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን ኪሳራው እንዲከፈለው ጠየቀ

Image
አለመግባባት የሚያጦዘው የኢትዮጵያ እግር ኳስ -    የደቡብ ክልል እግር ኳስ ፌዴሬሽን ኪሳራው እንዲከፈለው ጠየቀ -    ‹‹ነገሩ ግልፅ እንዲሆንልኝ መነጋገር እፈልጋለሁ›› እግር ኳስ ፌዴሬሽን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ከእንቅልፉ ተነሳ ሲባል መልሶ እያንቀላፋ፣ ተነቃቃ ሲባል እየደከመው ከረጅም ዓመታት በኋላ የለውጥ ጭላንጭል የታየበት ቢመስልም፣ ጊዜና ወቅት እየጠበቀ በሚፈጠር አለመግባባት እንደገና ወደ ጡዘት የሚያስገባ ምልክት እየተስተዋለበት ነው፡፡ የእግር ኳሱን ፋና የሚያጨልም ሰው (ጓዳ) ሠራሽ ቢሮክራሲ የበላይነት፣ የሥልጣን ማሳያ ሽኩቻ፣ ያለመግባባት ፍጥጫ ቀዝቃዛ ውኃ ሲቸልስበት ኖሯል፡፡ እነዚህ ጉዳዮች አሁንም እግር ኳሱ ቀና ቀና ማለት በጀመረበት ቅጽበት እንኳ የተቀየሩና የቀሩ አልመስል እያሉ ጉዞውን አስቸጋሪ እያደረጉበት ይገኛል፡፡ ከሰሞኑ የሚታየው ውዝግብም ኳሱ ከተለያዩ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ የውድድር መድረኮች ለዓመታት ተገልሎ የቆየበት ምክንየት ምን ነበር? የነበረውን ችግር ከሥር መሠረቱ ለመፍታት የተደረገው ጥረት ምንድነው? ዛሬስ ከዓመታት መገለል በኋላ ምን ዓይነት ለውጥና ዕድገት አምጥቶ ነው መድረኩን የተቀላቀለው? በሚሉትና ሌሎችም ተመሳሳይ የችግር አፈታት ሒደቶች ላይ የተመሠረተ ሳይሆን፣ የሥልጣን ድርሻና የበላይነት ላይ የተመሠረተ ሆኖ መታየቱ መንግሥትንም የሚያስተቸው መሆኑ አልቀረም፡፡ መንግሥት ‹‹ዘርፉ ከፖለቲካው ጨዋታ ውጭ እስከሆነ ድረስ ምንም ቢፈጠር ዝምታን ይመርጣል›› የሚለው የብዙዎች ትችት ወደ ኳሱም አካባቢ እየተዛመተ ስለመሆኑ እየተነገረ ይገኛል፡፡ እነዚሁ አካላት መንግሥት በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ እያከናወነ ካለው ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ክንውኖች ስፖርቱን

በሃዋሳ ከተማ ሲካሄድ የቆየው የባህል ፌስቲቫልና የኢንዱስትሪ ሳምንት ተጠናቀቀ

Image
ተፈጥሮአዊ መስህቦችና ባህላዊ ቅርሶች ለሀገሪቱና ለዓለም ህዝቦች በማሳወቅ ለገፅታ ግንባታው ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዲኖራቸው  እየሰራ መሆኑን የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ በሃዋሳ ከተማ ለአምስት ቀናት   ሲካሄድ የቆየው የባህል ፌስቲቫልና የኢንዱስትሪ ሳምንት መጋቢት 30/2005 ተጠናቋል፡፡ በባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር የባህል ኢንዱስትሪ የልማትና የትብብር ዳይሬክቶሬት ጊዜያዊ አስተባባሪ አቶ ተስፋዮ ኦታንጎ በፌስትቫሉ መዝጊያ ላይ እንደገለጹት የብዝሃ ባህል፣ የቅርስና የተፈጥሮ መስህቦችን ቀጣይነት ባለው መልኩ በመጠበቅና በማልማት የህዝቡን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማጎልበት እየተሰራ ነው፡፡ የሀገሪቱን ዕምቅ የባህል፣ የተፈጥሮ ቅርሶችና ዕሴቶችን በተገቢው መንገድ በማልማት ለሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ዕድገት ጉልህ ድርሻ እንዲኖራቸው ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ አቶ ተስፋዬ ለሁለተኛ ጊዜ ከመጋብት 25   እስከ መጋቢት 30 ቀን 2005 ዓ.ም በሃዋሳ ከተማ በተካሄደው የባህል ፌትቫልና የኢንዱስትሪ ሳምንት ሁለቱ የከተማ አስተዳደሮችን ጨምሮ ከዘጠኙም ክልሎች የመጡ የባህል ቡድኖች የየአከባቢያቸውን ባህልና እሴቶችን በአደባባይ በማሳየት ባህል ለአንድነት፣ ለሰላም፣ ለልማት፣ ለዕውቀትና ለመልካም ገፅታ ግንባታ ያለውን ጠቀሜታ አጉልተው ያሳዩበት መድረክ ነበር ብለዋል፡፡ ከትግራይ፣ ከኦሮሚያ፣ ከአማራና ከአዲስ አባባ የመጡ አንዳንድ የባህል ልዑካን ቡድን አባላት በሰጡት አስተያየት ፌስትቫሉ የእርስ በርስ ግንኙነትን የሚያጠናክር፣ ለዕውቀት ሽግግር ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያበረክት ከመሆኑም ባሻገር ክልሎች የየራሳቸውን ዕምቅ የባህል ሃብቶቻቸውን ለማስተዋወቅና መልካም ተሞክሮዎችን ለመለዋወጥ እንደረዳቸው ተ

በኢትዮጽያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ መለስ ዋንጫ አዳማ ከነማናሲዳማ ቡና አንድ አቻ ተለያዩ

Image
በአዳማ ከተማ እየተካየደ ያለው የኢትዮጽያ  ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ መለስ ዋንጫ  ውድድር ዛሬ ሚያዝያ 2/2005ዓ.ም  አዳማ ከነማናሲዳማ ቡና ተጫውተው አንድ አቻ ተለያዩ።  ዛሬ  በ10 ሰአት ኢትዮጽያ ንግድ ባንክ ከመከላከያ ነገ ማያዝያ 3/2005ዓ/ም ደግሞ ድሬዳዋ ከነማ ከደደቢት፤ ሃዋሳ ከነማከኢትዮጽያ መድህን ይጫወታሉ።

‹‹በሕዝብ የተመረጥኩ ነኝ›› ብሎ የሚያምን መንግሥት ‹‹ሕዝብ አለቃዬ ነው›› ብሎ ማመንም አለበት

Image
ሕገ መንግሥታችን ሥልጣን የሚይዝ መንግሥት በሕዝብ ድምፅ ብልጫ የተመረጠ መሆን አለበት ይላል፡፡ እንዲህ ዓይነት ጉድለት አለው እንዲህ መሰል ችግር ነበረው ቢባልም፣ በተግባር ምርጫ የሚካሄድበት አገርና ሕዝብ ሆነናል፡፡ ምርጫ በማካሄድ መንግሥትን ሥልጣን ላይ ማስቀመጥ ማለትና ለገዥው ፓርቲ ሕዝባዊ ድምፅ ሰጥቶ በአመራር ላይ ማስቀመጥ ማለት ግን በመንግሥት ላይ ከፍተኛ ኃላፊነት የማኖር ተግባር ነው፡፡ ኃላፊነቱም ሕዝብን በግዴታም በውዴታም የማገልገል ጉዳይ ነው፡፡ ምክንያቱም ሕዝብ መንግሥትን የሚመርጠው፣ አመራርን የሚመርጠው፣ አስተዳደርን የሚመርጠው ‹‹አገልግለኝ›› ብሎ ነው፡፡ ስለሆነም በሕዝብ ተመርጦ ሥልጣን ላይ የተቀመጥኩ መንግሥት ነኝ የሚል ገዥ ፓርቲ አለቃዬ የመረጠኝ ሕዝብ ነው በማለት ማመን አለበት፡፡ በሕዝብ መመረጥ መብቴ ነው የሚል ገዥ ፓርቲ ሕዝብን ማገልገል ግዴታዬ ነው ብሎም ማመን አለበት፡፡ ሕገ መንግሥታችንም ያስገድደዋል፡፡ ሕዝብ አለቃዬ ነው፣ ሕዝብን ማገልገል ግዴታዬ ነው ብሎ የሚያምን መንግሥት ደግሞ የሕዝብን ጥያቄ ይመልሳል ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ኢሕአዴግ እንደ ገዥ ፓርቲ ራሱን መጠየቅ፣ መፈተሽና መገምገም ያለበት በእውነት የሕዝብን ጥያቄ እየመለስኩ ነው ወይ? ብሎ ነው፡፡ ሕዝብ መልካም አስተዳደር እንዲኖር እየጠየቀ ነው፡፡ ሕዝብ እንደ አለቃ መንግሥትን ሥልጣን ላይ ያስቀመጥኩህ መልካም አስተዳደር እንድታመጣልኝ ነው፡፡ የት አለ መልካም አስተዳደሩ እያለ ነው፡፡ ኢሕአዴግ ደፈር ብሎ አዎን ሕዝብ ሆይ የሚገባኝን መልካም አስተዳደር ስላልሰጠሁህ ይቅርታ እጠይቃለሁ፤ አሁን ግን አሟላለሁ ማለት አለበት፡፡ የት አቤት እንደሚባል እየጠፋ ነው፡፡ መልስ ሰጪ እየታጣ ነው፡፡ እንባ ሲፈስ እንጂ ሲታበስ አይ

የመለስ ዜናዊ ፋውንዴሽን መሥራች ጉባዔ በተደበላለቀ ስሜት ተካሄደ

Image
-    ፋውንዴሽኑ የሚገነባበት ቦታ ቢለይም ዲዛይኑ አልተጠናቀቀም -    ፋውንዴሽኑ ከ50 ሚሊዮን ብር በላይ ስጦታ አግኝቷል -    ለቤተሰቦቻቸው መኖሪያ ቤት ለመገንባት ዲዛይኑ እስከሚፀድቅ እየተጠበቀ ነው ከሰባት ወራት በፊት በሞት የተለዩት የቀድሞው የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ መታሰቢያ “መለስ ዜናዊ ፋውንዴሽን” መሥራች ጉባዔ መጋቢት 29 ቀን 2005 ዓ.ም. በአፍሪካ ኅብረት የመሰብሰቢያ አዳራሽ በተደበላለቀ ስሜት ተካሄደ፡፡ ፋውንዴሽኑ የአቶ መለስ ዜናዊ እሴቶችና መርሆዎች፣ በቀጣይነት ከትውልድ ትውልድ ይሰርፁ ዘንድና ቀጣይነት እንዲኖራቸው፣ ሐሳቦችና ፕሮግራሞች የሚፈልቁበት ህያው ማዕከል ሆኖ እንዲያገለግል “መለስ ዜናዊ ፋውንዴሽን” በሚል ስያሜ፣ በተወካዮች ምክር ቤት ጥር 17 ቀን 2005 ዓ.ም. በአዋጅ እንዲቋቋም መደረጉ ይታወሳል፡፡ በመሆኑም ፋውንዴሽኑን በአዋጅ ለማቋቋም ላለፉት ሰባት ወራት ሒደቱን የሚመራና የሚያስተባብር የሌጋሲ ኮሚቴ እንዲቋቋም ተደርጎ፣ የተለያዩ ሥራዎችን በመሥራት፣ አዋጁ ከፀደቀ በኋላ መሥራች ጉባዔውን ለማካሄድ መቻሉን የገለጹት፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔና የሌጋሲው ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ካሣ ተክለብርሃን ናቸው፡፡ በአጭር ጊዜና ዝግጅት፣ በአገር ውስጥ ከአርሶ አደር እስከ ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣ እንዲሁም ከአፍሪካ እስከ ዓለም ድረስ ላሉ የአቶ መለስ ወዳጆችና አድናቂዎች፣ የተደረገላቸውን ጥሪ አክብረው በፋውንዴሽኑ መሥራች ጉባዔ ላይ በመገኘታቸው ምሥጋናቸውን የገለጹት አቶ ካሣ፣ አቶ መለስ በሥራቸው በአኅጉር አቀፍና በዓለም አቀፍ ደረጃ ሲታወሱ እንደሚኖሩ ገልጸዋል፡፡ በእሳቸው የሕይወት ዘመን በአመራር ቦታ ላይ ለመድረስ የቻሉ ሰዎች ልብ ሊሉት የሚገባው ነገር እሳቸው በዘፈ