Posts

‹‹በሕዝብ የተመረጥኩ ነኝ›› ብሎ የሚያምን መንግሥት ‹‹ሕዝብ አለቃዬ ነው›› ብሎ ማመንም አለበት

Image
ሕገ መንግሥታችን ሥልጣን የሚይዝ መንግሥት በሕዝብ ድምፅ ብልጫ የተመረጠ መሆን አለበት ይላል፡፡ እንዲህ ዓይነት ጉድለት አለው እንዲህ መሰል ችግር ነበረው ቢባልም፣ በተግባር ምርጫ የሚካሄድበት አገርና ሕዝብ ሆነናል፡፡ ምርጫ በማካሄድ መንግሥትን ሥልጣን ላይ ማስቀመጥ ማለትና ለገዥው ፓርቲ ሕዝባዊ ድምፅ ሰጥቶ በአመራር ላይ ማስቀመጥ ማለት ግን በመንግሥት ላይ ከፍተኛ ኃላፊነት የማኖር ተግባር ነው፡፡ ኃላፊነቱም ሕዝብን በግዴታም በውዴታም የማገልገል ጉዳይ ነው፡፡ ምክንያቱም ሕዝብ መንግሥትን የሚመርጠው፣ አመራርን የሚመርጠው፣ አስተዳደርን የሚመርጠው ‹‹አገልግለኝ›› ብሎ ነው፡፡ ስለሆነም በሕዝብ ተመርጦ ሥልጣን ላይ የተቀመጥኩ መንግሥት ነኝ የሚል ገዥ ፓርቲ አለቃዬ የመረጠኝ ሕዝብ ነው በማለት ማመን አለበት፡፡ በሕዝብ መመረጥ መብቴ ነው የሚል ገዥ ፓርቲ ሕዝብን ማገልገል ግዴታዬ ነው ብሎም ማመን አለበት፡፡ ሕገ መንግሥታችንም ያስገድደዋል፡፡ ሕዝብ አለቃዬ ነው፣ ሕዝብን ማገልገል ግዴታዬ ነው ብሎ የሚያምን መንግሥት ደግሞ የሕዝብን ጥያቄ ይመልሳል ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ኢሕአዴግ እንደ ገዥ ፓርቲ ራሱን መጠየቅ፣ መፈተሽና መገምገም ያለበት በእውነት የሕዝብን ጥያቄ እየመለስኩ ነው ወይ? ብሎ ነው፡፡ ሕዝብ መልካም አስተዳደር እንዲኖር እየጠየቀ ነው፡፡ ሕዝብ እንደ አለቃ መንግሥትን ሥልጣን ላይ ያስቀመጥኩህ መልካም አስተዳደር እንድታመጣልኝ ነው፡፡ የት አለ መልካም አስተዳደሩ እያለ ነው፡፡ ኢሕአዴግ ደፈር ብሎ አዎን ሕዝብ ሆይ የሚገባኝን መልካም አስተዳደር ስላልሰጠሁህ ይቅርታ እጠይቃለሁ፤ አሁን ግን አሟላለሁ ማለት አለበት፡፡ የት አቤት እንደሚባል እየጠፋ ነው፡፡ መልስ ሰጪ እየታጣ ነው፡፡ እንባ ሲፈስ እንጂ ሲታበስ አይ

የመለስ ዜናዊ ፋውንዴሽን መሥራች ጉባዔ በተደበላለቀ ስሜት ተካሄደ

Image
-    ፋውንዴሽኑ የሚገነባበት ቦታ ቢለይም ዲዛይኑ አልተጠናቀቀም -    ፋውንዴሽኑ ከ50 ሚሊዮን ብር በላይ ስጦታ አግኝቷል -    ለቤተሰቦቻቸው መኖሪያ ቤት ለመገንባት ዲዛይኑ እስከሚፀድቅ እየተጠበቀ ነው ከሰባት ወራት በፊት በሞት የተለዩት የቀድሞው የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ መታሰቢያ “መለስ ዜናዊ ፋውንዴሽን” መሥራች ጉባዔ መጋቢት 29 ቀን 2005 ዓ.ም. በአፍሪካ ኅብረት የመሰብሰቢያ አዳራሽ በተደበላለቀ ስሜት ተካሄደ፡፡ ፋውንዴሽኑ የአቶ መለስ ዜናዊ እሴቶችና መርሆዎች፣ በቀጣይነት ከትውልድ ትውልድ ይሰርፁ ዘንድና ቀጣይነት እንዲኖራቸው፣ ሐሳቦችና ፕሮግራሞች የሚፈልቁበት ህያው ማዕከል ሆኖ እንዲያገለግል “መለስ ዜናዊ ፋውንዴሽን” በሚል ስያሜ፣ በተወካዮች ምክር ቤት ጥር 17 ቀን 2005 ዓ.ም. በአዋጅ እንዲቋቋም መደረጉ ይታወሳል፡፡ በመሆኑም ፋውንዴሽኑን በአዋጅ ለማቋቋም ላለፉት ሰባት ወራት ሒደቱን የሚመራና የሚያስተባብር የሌጋሲ ኮሚቴ እንዲቋቋም ተደርጎ፣ የተለያዩ ሥራዎችን በመሥራት፣ አዋጁ ከፀደቀ በኋላ መሥራች ጉባዔውን ለማካሄድ መቻሉን የገለጹት፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔና የሌጋሲው ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ካሣ ተክለብርሃን ናቸው፡፡ በአጭር ጊዜና ዝግጅት፣ በአገር ውስጥ ከአርሶ አደር እስከ ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣ እንዲሁም ከአፍሪካ እስከ ዓለም ድረስ ላሉ የአቶ መለስ ወዳጆችና አድናቂዎች፣ የተደረገላቸውን ጥሪ አክብረው በፋውንዴሽኑ መሥራች ጉባዔ ላይ በመገኘታቸው ምሥጋናቸውን የገለጹት አቶ ካሣ፣ አቶ መለስ በሥራቸው በአኅጉር አቀፍና በዓለም አቀፍ ደረጃ ሲታወሱ እንደሚኖሩ ገልጸዋል፡፡ በእሳቸው የሕይወት ዘመን በአመራር ቦታ ላይ ለመድረስ የቻሉ ሰዎች ልብ ሊሉት የሚገባው ነገር እሳቸው በዘፈ

በኢትዮጵያ የሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ሲዳማ ቡና እና ሃዋሳ ከነማ ተጋጣሚዎቻቸውን ኣሸነፉ

Image
አዳማ ላይ እየተካሄደ ያለው የሴቶች ፕሪሚየር ሊግ በደማቅ ሁኔታ በብርቱ ፉክክር ታጅቦ መከናወኑን ቀጥሎ መጋቢት 29/2005 ሶስት ጨዋታዎች ተደርገዋል፡፡ በውድድሩ ስኬታማ ይሆናሉ ተብለው ቀዳሚ ግምት ከተሰጣቸው መሐል አንዱ የሆነው መከላከያ በሲዳማ ቡና ሳይጠበቅ 3ለ1 ተሸንፏል፡፡ ትብለጥ ሁለቱን ተራማጅ ቀሪዋን ጎል ለሲዳማ ቡና አስቆጥረዋል፡፡ የአዲስ አበባዎቹ ደደቢትና መድህን ባደረጉት ጨዋታም ደደቢት 3ለ0 አሸንፏል፡፡ ሰናይት ባሩዳ ሁለቱን ብርቱካን ገ/ክርስቶስ ደግሞ አንዷን ጎል ከመረብ አገናኝተዋል፡፡ በሌላው ጨዋታ ሐዋሳ ከነማ ድሬዳዋ ከነማን 3ለ1 ረቷል፡፡ እስከዳር አብዲ፣ ሮዛ ከድርና ዝናሽ የድል ጎሎቹን አስቆጥረዋል፡፡ የፕሪሚየር ሊጉ መርሃ ግብር ሐሙስ ሲቀጥል ጠዋት 3፡00 ሰዓት አዳማ ከነማ ከሲዳማ ቡና ከሰዓት 10፡00 ሰዓት ላይ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከመከላከያ ይጫወታሉ፡፡ http://www.ertagov.com/amharic/index.php/2013-03-11-06-12-23/item/402-%E1%8B%A8%E1%88%B4%E1%89%B6%E1%89%BD-%E1%8D%95%E1%88%AA%E1%88%9A%E1%8B%A8%E1%88%AD-%E1%88%8A%E1%8C%8D-%E1%89%A0%E1%89%A5%E1%88%AD%E1%89%B1-%E1%8D%89%E1%8A%AD%E1%8A%AD%E1%88%AD-%E1%89%B3%E1%8C%85%E1%89%A6-%E1%8A%A5%E1%8A%95%E1%8B%B0%E1%89%80%E1%8C%A0%E1%88%88-%E1%8A%90%E1%8B%8D

ለኢቴቪ ዓመቱን ሙሉ “April the fool” ነው!

ሰሞኑን የተከሰተ ዜና ነው - እዚህ ሳይሆን ፈረንጆቹ አገር፡፡ ሁለት ታዳጊ ፍቅረኛሞች ናቸው አሉ፡፡ የፍቅር ጓደኝነት ከመሰረቱ ብዙ አልቆዩም፡፡ ግን ሲዋደዱ ለጉድ ነው፡፡ (እንደ ኢህአዴግና ተቃዋሚዎች እንዳትሉኝ!) ባለፈው ሰኞ ግን በጨዋታ መሃል በተፈጠረ አለመግባባት እሷ እሱን አንገቱ ላይ በስለት ወግታው ወህኒ ወረደች አሉ (የአፍሪካ ፖለቲካ አይመስልም?) አያችሁ እንዲህ በጨዋታ መሃል ያልተጠበቀ አደጋ ሊከሰት ይችላል፡፡ አንዳንዴ ዓይን ሊጠፋ ወይም እግር ሊሰበር ይችላል፡፡ ባስ ሲል ህይወትም ይጠፋል፡፡ በፍቅር ጨዋታ እንዲህ ካጋጠመ በፖለቲካ ጨዋታ ምን ሊያጋጥም እንደሚችል አስቡት፡፡ እቺን እቺንማ ከእኛ በላይ ማን ያውቃታል? ምንም ቢሆን እኮ የአፍሪካ ልጆች ነን! (የአራዳ ልጅ እንዲሉ) የጨዋታው አባቶች የአፍሪካ አምባገነን መሪዎች ከሆኑ ደግሞ ነገርዬው የከፋ ይሆናል - የመረረ!! ለምን መሰላችሁ? መቼ እንደሚያመሩ፤ መቼ ከፍቅር ወደ ጥላቻ እንደሚሸጋገሩ ፈጽሞ አታውቁም፡፡ ኳስ ይዞ የነበረው እጃቸው በምን ቅጽበት ጠብመንጃውን አፈፍ እንዳደረገ ፈጣሪያቸው ብቻ ነው (የራሳቸው ፈጣሪ ይኖራቸዋል ብዬ እኮ ነው!) የሚያውቀው (“አድነነ ከመዓቱ” ማለት ይሄኔ ነው!) ይኸውላችሁ የእኔ ነገር የፍቅረኞቹን ሳልጨርስላችሁ ፖለቲካ ውስጥ መሰስ ብዬ ገባሁላችሁ፡፡ (ፖለቲካ አሳሳች እኮ ነው!) እናላችሁ.. ሁለቱ ፍቅረኛሞች ሲገናኙ ሁሉም ነገር አማን ነበር፡፡ በተለይ እሱ ፍቅር እንጂ ሌላ አልጠበቀም፡፡ እሷም ብትሆን ያለወትሮዋ ቀልድና ጨዋታ አምሯታል እንጂ ሌላ ነገር አላሰበችም፡፡ በጨዋታቸው መሃል ግን አንድ ዱብዕዳ ዜና ጣል አደረገችበት - እንደዘበት! “አርግዣለሁ” አለችው፡፡ “What?” (ምን? ትቀልጃለሽ? አብደሻል? ወዘተ… ሊል እንደሚችል ገምቱ!) ፍቅረ

“ኢህአዴግ ጠንካራ የተቃዋሚ ፓርቲ ለማግኘት አልታደለም”

Image
በግጥም ምሽቶች መታደም ትልቅ ደስታ ይሰጠኛል------ ኢህአዴግ ለተቃዋሚዎች ድጋፍ ነፍጓል ብዬ አላስብም----- ኢትዮጵያ ከፓርቲዎች ፖለቲካ በላይ ልትወሰድ ይገባል----- አቶ ህላዌ ዮሴፍ በብአዴን መስራችነታቸው፣ በትጥቅ ትግሉ ወቅት ድርጅቱ ለቅስቀሳ ይጠቀምባቸው የነበሩትን መዝሙሮች ግጥምና ዜማ በመድረስ እንዲሁም በበርካታ ቀስቃሽና ወቅታዊ የግጥም ሥራዎቻቸው ይታወቃሉ፡፡ የአማራ ልማት ማህበርን (አልማ) ለሃያ አመታት በሥራ አስኪያጅነትና በቦርድ ሊቀመንበርነት አገልግለዋል፡፡ በአምባሳደርነት ተመድበው ከሚሰሩበት እሥራኤል አገር ፤ ለብአዴን ድርጅታዊ ስብሰባና ለዘጠነኛው የኢህአዴግ ጉባዔ ወደ አገራቸው በመጡበት ወቅት ከጋዜጠኛ መታሰቢያ ካሳዬ ጋር በባህርዳር ከተማ ቃለምልልስ አድርገዋል፡፡ ብአዴን በቅርቡ ባካሄደው ድርጅታዊ ስብሰባ ወቅት ያደረገው መሰረታዊ ለውጥ አለ? በድርጅቱ ውስጥ በፖሊሲ፣ በፖለቲካ አቋምና መስመሮች ዙሪያ የተደረገ ለውጥ የለም፡፡ በአመራር ደረጃ ከነበሩት 65 የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት መካከል 20 የሚሆኑትን ቀይረናል፡፡ ይህ ደግሞ ሁሌም በጉባኤው ወቅት የሚከናወን ጉዳይ ነው፡፡ በተረፈ ድርጅቱ በሥራ አፈፃፀሙና አባላቱን በማጠናከሩ ረገድ ራሱን እያሻሻለ መሄዱንና በአስተማማኝ ጥንካሬ ላይ መድረሱን አረጋግጠናል፡፡ በአንዳንድ ጉዳዮች ዙሪያ መሻሻልና መስተካከል ይገባቸዋል ያልናቸውን ጉዳዮችም አንስተን ተወያይተናል፡፡ በመልካም አስተዳደር ረገድ በፌደራል ደረጃ በተደጋጋሚ እንደሚነሳው፣ በአማራ ክልልም አንዳንድ ትኩረት ሰጥተን ልናያቸው የሚገቡ ጉዳዮች እንዳሉም አይተናል፡፡ በእኔ አስተያየት ድርጅቱ በጤናማ አቅጣጫ እየተጓዘ ነው፡፡ ስለመጪው ምርጫ ምን አስተያየት አለዎት? ኢህአዴግ ምርጫውን ህዝብ የሚያምንበት ምርጫ ያደርገዋል