የመለስ ዜናዊ ፋውንዴሽን መሥራች ጉባዔ በተደበላለቀ ስሜት ተካሄደ
- ፋውንዴሽኑ የሚገነባበት ቦታ ቢለይም ዲዛይኑ አልተጠናቀቀም - ፋውንዴሽኑ ከ50 ሚሊዮን ብር በላይ ስጦታ አግኝቷል - ለቤተሰቦቻቸው መኖሪያ ቤት ለመገንባት ዲዛይኑ እስከሚፀድቅ እየተጠበቀ ነው ከሰባት ወራት በፊት በሞት የተለዩት የቀድሞው የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ መታሰቢያ “መለስ ዜናዊ ፋውንዴሽን” መሥራች ጉባዔ መጋቢት 29 ቀን 2005 ዓ.ም. በአፍሪካ ኅብረት የመሰብሰቢያ አዳራሽ በተደበላለቀ ስሜት ተካሄደ፡፡ ፋውንዴሽኑ የአቶ መለስ ዜናዊ እሴቶችና መርሆዎች፣ በቀጣይነት ከትውልድ ትውልድ ይሰርፁ ዘንድና ቀጣይነት እንዲኖራቸው፣ ሐሳቦችና ፕሮግራሞች የሚፈልቁበት ህያው ማዕከል ሆኖ እንዲያገለግል “መለስ ዜናዊ ፋውንዴሽን” በሚል ስያሜ፣ በተወካዮች ምክር ቤት ጥር 17 ቀን 2005 ዓ.ም. በአዋጅ እንዲቋቋም መደረጉ ይታወሳል፡፡ በመሆኑም ፋውንዴሽኑን በአዋጅ ለማቋቋም ላለፉት ሰባት ወራት ሒደቱን የሚመራና የሚያስተባብር የሌጋሲ ኮሚቴ እንዲቋቋም ተደርጎ፣ የተለያዩ ሥራዎችን በመሥራት፣ አዋጁ ከፀደቀ በኋላ መሥራች ጉባዔውን ለማካሄድ መቻሉን የገለጹት፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔና የሌጋሲው ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ካሣ ተክለብርሃን ናቸው፡፡ በአጭር ጊዜና ዝግጅት፣ በአገር ውስጥ ከአርሶ አደር እስከ ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣ እንዲሁም ከአፍሪካ እስከ ዓለም ድረስ ላሉ የአቶ መለስ ወዳጆችና አድናቂዎች፣ የተደረገላቸውን ጥሪ አክብረው በፋውንዴሽኑ መሥራች ጉባዔ ላይ በመገኘታቸው ምሥጋናቸውን የገለጹት አቶ ካሣ፣ አቶ መለስ በሥራቸው በአኅጉር አቀፍና በዓለም አቀፍ ደረጃ ሲታወሱ እንደሚኖሩ ገልጸዋል፡፡ በእሳቸው የሕይወት ዘመን በአመራር ቦታ ላይ ለመድረስ የቻሉ ሰዎች ልብ ሊሉት የሚገባው ነገር እሳቸው በዘፈ