Posts

ወደ አዋሳ ከተማ የሚገቡ ሰዎች በጥብቅ የተፈተሹ ነው

Image
የኢህአዴግ አባል ድርጅቶችን ስብሰባ ተከትሎ በአዋሳ፣ አዳማ እና ባህርዳር ጥብቅ ፍተሻ መካሄዱን የአይን እማኞች ገለጹ በተለይ በአዳማ እና በአዋሳ ከዚህ በፊት ታይቶ የማይታወቅ ፍተሻ ከቅዳሜ ከሰአት ጀምሮ እስከ ዛሬ መካሄዱ ታውቋል። ወደ አዋሳ ከተማ የሚገቡ ሰዎች በጥብቅ የተፈተሹ ሲሆን፣  በከተማዋ ውስጥም በአንዳንድ ቦታዎችም ፍተሻዎች ተደርገዋል። በአዋሳ የተለያዩ ቦታዎች ድንኳኖች ተተክለው የኢህአዴግ ደጋፊዎች ሲበሉና ሲጠጡ፣ ሲጨፍሩ የታዩ ሲሆን፣ ከ30 እሰከ አርባ የሚደርሱ ሰዎች በድንኳኖች ዙሪያ ይታዩ ነበር።   በአዳማ ደግሞ ኢህዴድን  እንዲደግፉ የተጠሩ ሰዎች ሳይቀር ጥብቅ ፍተሻ ተደርጎባቸዋል። ጥሪ የተደረገላቸው የቀበሌ ሰዎች ባለመገኘታቸው የኦህዴድ ካድሬዎች በእጅጉ መበሳጨታቸውን ከአባለቱ የተገኘው መረጃ ያስረዳል። በትግራይ መቀሌ በተደረገው የድጋፍ ሰልፍ ደግሞ የህወሀት ኩባንያ ንብረት የሆነው ኢፈርት መኪኖች ሰልፉን አድምቀውት ውለዋል። ነዋሪዎች የሰልፉ አላማ ግራ ሲያጋባቸው ታይቷል። ኢህአዴግ ከዚህ በፊት ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ህዝቡ እንዲደግፈው ጥሪ ማቅረቡ ድርጅቱ የገባበትን የውስጥ ፍርሀት የሚያሳይ መሆኑን አንዳንድ አባላት ለኢሳት ዘጋቢ ገልጸዋል። ኢህአዴግ በውስጥ የተፈጠረውን ሽኩቻ በመጪው ጉባኤ እንዲፈታ የስርአቱ ደጋፊዎች እየተማጸኑ ነው። አሁን በደረሰን ዜና ደግሞ የባህር ዳር ከተማ ነዳጅ ማደያ ቦታዎች በሙሉ በል ዩ ት ዛ ዝ ካልሆነ በስተቀር ለማ ንም ነዳጅ እንዳይሸጡ ታዘዙ!!! በዚህም ምክንያት በከተማው ውስጥ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ እጅግ ከፍተኝ የሆነ የ ትራንስፖርት እጥረት ተከስቱዋል ትቂት ባጃጆች በስራ ላይ ያሉ ሲሆን በሊትር ሃያ ብር የሚሸተወን ቤንዚን በሃያ አምስት ብር ከ አትራፊ ቸርቻሪዎች ለመ

Tree species diversity, topsoil conditions and arbuscular mycorrhizal association in the Sidama traditional agroforestry land use, southern Ethiopia

Image
Zebene , Asfaw (2003). Tree species diversity, topsoil conditions and arbuscular mycorrhizal association in the Sidama traditional agroforestry land use, southern Ethiopia. Diss. ( sammanfattning /summary) Uppsala : Sveriges lantbruksuniv ., Acta Universitatis agriculturae Sueciae . Silvestria , 1401- 6230 ; 263 ISBN 91-576-6347-5 [Doctoral thesis] Abstract Sidama farmers cultivate trees to meet their food, wood, fodder and other service needs. Tree cultivation intensity has increased during the past three decades. Significant positive correlation was found between farm size and number of species, and number of stems per farm. The number of tree species per farm averaged 16 and ranged from 4 to 28. Within farms, about ten different field types were identified of which enset fields contain the highest number of species. Wealthy households have more tree species than poor households. In general the largest number of tree species, the largest nu

እኛ የኢህአዴግን ጠመንጃ እንፈራለን፤ ኢህአዴግ ደግሞ 97 ላይ የመጣበትን የህዝብ ጎርፍ ይፈራል ‹‹ኢህአዴግን በሁለት ሳምንት ስራ በዝረራ በአንዳንድ አካባቢዎች ማሸነፍ ይቻላል፤ በአዲስ አበባ ግን ሁለት ቀን በቂ ነው››

ያለማመንታት ፕ/ር መረራ ‹‹ፖለቲከኛ ናቸው›› ማለት ይቻላል፡፡ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ጉዞአቸውም እንደ ፖለቲካ ሳይንስ ምሁርነታቸውና እንደፖለቲከኛነታቸው በሚያደርጉት ተሳትፎአቸው ይታወቃሉ፡፡ በኢትዮጵያ ህዝብ ዘንድ ደግሞ በፓርላማ በነበራቸው ቆይታ በግልፅነታቸውና በቀልድ እያዋዙ ተናጋሪነታቸው ነው የሚታወቁት፡፡ በፖለቲካ የተሳትፎ ህይወታቸው የሚጀምረው አምቦ የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪ እያሉ ነበር፡፡ የንጉሱን አገዛዝ ለመጣል ከተንቀሳቀሱት አፍላ ወጣቶችም አንዱ ናቸው፡ ፡ በወቅቱ የ66ቱ አብዮት እውን ቢሆንም አብዮቱ ብዙዎቹን ሲበላ እሳቸው ‹‹በዕድል›› በሚሉት ከበርካታ የሞት አጋጣሚዎች አምልጠዋል፡ ፡ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ ተማሪ ሆነው ግን ከደርግ ጨካኝ የብረት መዳፍ አላመለጡም፡፡ ለበርካታ ዓመታት ያለክስ በፖለቲካ እስረኝነት አሳልፈዋል፡፡ ባለፈው ዓመት አውራምባ ታይምስ ጋዜጣ ‹‹እርስዎ በግልዎ መታሰርን ይፈራሉ?›› ሲል ላቀረበላቸው ጥያቄ ‹‹መታሰር… እእእ… ለመታሰር አልፈልግም፡፡ በደርግ ጊዜ ወደ ሰባት ዓመታት ስለታሰርኩኝ፤ እስር ምን እንደሆነ ስለማወቅ እስር መፍራት አለብኝ፡፡ ፍርሃቴ ግን ገደብ አለው›› ሲሉ ነበር የመለሱት፡፡ የ7 ዓመት እስራታቸው ደግሞ ዛሬ በብዙዎች ዘንድ ለሚታወቁበት በግልፅና በቀልድ እያዋዙ ተናጋሪነታቸው የህይወት ለውጥ ምክንያት እንደሆናቸው ነው ለኢትዮ-ቻናል የገለፁት፡፡ ‹‹የማክረር ፖለቲካን›› ያኔ ነው የተውኩት በማለት፡፡ ኢህአዴግ በ1983 አዲስ አበባን ከተቆጣጠረ በኋላ የኦሮሞን ህዝብ ጥያቄን ለማሳካት ፓርቲ አቋቁመው በሀገር ውስጥ ፖለቲካውን ትግል ተቀላቅለዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህር ሲሆኑ በተቃዋሚ ፓርቲዎች ልዩ ሁነት የነበረው በ97 ምርጫ

በደኢህዴን መሪነት የክልሉ ህዝቦች አንድነት ዴሞክራሲያዊ ብሔርተኝነት ጎልብቷል

Image
አዋሳ፤ መጋቢት 10/2005/ዋኢማ/ - በደኢህዴን መሪነት የደቡብ ክልል ሕዝቦች በፈቃዳቸው የመሰረቱት ክልላዊ መስተጋብርና አንድነት በሀገሪቱ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና ማህበራዊ ልማት መስክ ዲሞክራሲያዊ ብሔርተኝነት እንዲጎለብት ጠንካራ መሰረት መጣሉን የደኢህዴንና ኢህአዴግ ሊቀመንበር ገለጹ። የደኢህዴንና ኢህአዴግ ሊቀመንበር አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ የደኢህዴን 8ኛ ጉባኤ ትናንት በሀዋሳ ከተማ ሲጀመር እንደገለጹት፤ በክልሉ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች መካከል የነበረው መስተጋብር በጋራ መልማትና አስተማማኝ ሰላም የማረጋገጥ ፍላጎት በመሆኑ ጠንካራ ክልል እንዲመሰርቱ አስችሏል። ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ባሏቸው የታሪክ የስነ-ልቦናና የተለያዩ መስተጋብሮቻቸው በአንድነት በመሰረቱት ክልል በደኢህዴን አመራር ልዩነታችን ውበታችን አንድነታችን ጥንካሬያችን ሆኖ በተሃድሶ መስመር ላገኘነው ድልና ለተመዘገበው ፈጣን ልማት መሰረት መሆኑን ተናግረዋል። እስከ ደኢህዴን ሰባተኛ ጉባኤ በክልሉ ለሰባት ተከታታይ ዓመታት የባለ ሁለት አሃዝ የኢኮኖሚ ዕድገት መመዝገቡ 7ኛው የድርጅቱ ጉባኤ ተከታታይ ፈጣን ዕድገት ማስመዝገብ ብቻውን በቂ ባለመሆኑ ይህንን ዕድገት በማስቀጠል የኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን ማምጣት እንዳለበት ወስኖ ወደ ተግባር መገባቱን ገልጸዋል። ደኢህዴን የተከተለው መስመር ተከታታይና ፈጣን ልማትን ከማረጋገጥ ባሻገር የክልሉ ህዝቦች ከልማቱ በየደረጃው ተጠቃሚ የሚሆንበትና ፍትሃዊ የሀብት ክፍፍል የሚያረጋግጥ መሆኑን በተግባር እንዳስመሰከረ አቶ ኃይለማሪያም አስታውቀዋል። ደኢህዴን የክልሉን ህዝቦች ከዳር እስከዳር የማንቀሳቀስ ብቃቱን በመጠቀም ልማትን ብቻ ሳይሆን ዴሞክራሲ በህዝቡ ቀጥተኛ ተሳትፎ ላይ የተመሰረተ እንዲሆን ማድረጉን አስረድተዋል። ንቅናቄው በ

የአለታ ወንዶ ወረዳ ሴቶች ለምርጫው መዘጋጀታቸውን ገለጹ

አዋሳ መጋቢት 09/2005 በመጪው ሚያዚያ ወር በሚካሄደው የዞን፣ የወረዳና ቀበሌ ምክር ቤቶች አባላት ምርጫ በንቃት ለመሳተፍ መጋጀታቸውን በሲዳማ ዞን የአለታ ወንዶ ወረዳ ሴቶች ገለጹ፡፡ ከወረዳው ሴቶች መካከል አንዳንዶቹ ሰሞኑን ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት በምርጫው መብትና ጥቅማቸውን የሚያስከብርላቸውን ለመምረጥ ከወዲሁ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል፡፡ በተለይ የወረዳው ሴቶች፣ ህጻናትና ወጣቶች ጽሕፈት ቤት ሀላፊ ወይዘሮ አዛለች ካያሞ እንዳስረዱት በአለታ ወንዶ 29 የገጠርና ከተማ ቀበሌዎች ለምርጫው ከተመዘገበው 59ሺህ ያህል ህዝብ ግማሽ ሴቶች ናቸው፡፡ በተመራጭ፣በአስመራጭና ታዛቢነት ከወንዶች እኩል ስብጥርና ተሳትፎ እንዳላቸው አስታውቀው በመራጭነትና በተመራጭነት የተመዘገቡት ሴቶች በስርዓቱ ያገኙትን ተጠቃሚነት ዘላቂ ለማድረግ ሰርተው የሚሰሩ ተወካዮቻቸውን ለመምረጥ እለቱን በጉጉት እየተጠባበቁ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡ በድርጅት ለወረዳ ምክር ቤት በዕጩነት ከቀረቡት መካከል ወይዘሮ አልማዝ ዲንጋሞ ቢመረጡ ሴቶች ከወንዶች እኩል ሆነው በማህበራዊ ፣ በኢኮኖሚና ፓለቲካ ያላቸውን ተሳታፊነትና ተጠቃሚነታቸውን ይበልጥ ለማጠናከር ጠንክረው ለመስራት መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል፡፡ በድርጅታቸው ተወክለው ለምርጫው ተሳታፊ በመሆናቸው መደሰታቸውን ተናግረዋል፡፡ በመራጭነት ከተመዘገቡት መካከል ወጣት አሰለፈች በቀለና እመቤት ተሰማ ሴቶች ለዘመናት ሲደረስባቸው ከነበረው የጾታ ተጽዕኖናና ጭቆና ተላቀው ባገኙት መብት ተጠቃሚ መሆናቸውን አስታውቀው በቀጣዩ ምርጫ በንቃት በመሳተፍ ጥቅሞቻቸውን የሚስጠብቁላቸውን ለመምረጥ መዘጋጀታቸውን አስረድተዋል፡፡